Eotc south and west Africa Dioceses

Eotc south and west Africa Dioceses Ethiopian Orthodox Tewahido

የብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ የሀድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መልእክት"ምንተ ተኀሥሣሁ ለሕያው ምስለ ምውታን""ሕያውን ከሙታን ጋራ ስለምን ትፈልጉታላችሁ"ሉቃስ ...
19/04/2025

የብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ የሀድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መልእክት

"ምንተ ተኀሥሣሁ ለሕያው ምስለ ምውታን"
"ሕያውን ከሙታን ጋራ ስለምን ትፈልጉታላችሁ"
ሉቃስ 24÷5

በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ በሀድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት እንዲሁም በመላው ዓለም የምትገኙ የመንፈስ ልጆቻችን እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ።

የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ከሲኦል ወደ ገነት ይመልሰው ዘንድ ደግሞም መከራ ነፍሳችንን ያጠፋ ዘንድ በዓውደ ቀራንዮ ከተሰቀለ በኋላ ክቡራን ዮሴፍና ኒቆዲሞስ በሐዲስ መቃብር በቀበሩት ጊዜ የእውነት ጠላቶች አይሁድ "እውነትን ቀበርነው" ብለው ቢደሰቱም እውነት የሆነውን ክርስቶስን መቃብር እንደማያሸንፈው ስለሚያውቁ ግን ጠባቂዎችን አኑረው ነበር።

ሞትና መቃብር የማያሸንፈው ጠባቂ የማያቆመው ኃያሉ ክርስቶስ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ተነሳ። የኛ ተስፋ ትንሣኤም በትንሣኤው ተረጋገጠ። ሟቾች ሳይሆን ሕያዋን መሆናችንን ሰበከልን። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ "ፋሲካ ብሂል ማዕዶት ብሂል በዘቦቱ አዶነ እሞት ውስተ ሕይወት" እንዳለው ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት ፣ ከግዞት ወደ ነጻነት የመሸጋገራችን ብርሀነ ትንሣኤው በዓለም ሁሉ ተንቦገቦገ።

ውድ የመንፈስ ልጆቻችን

መልአኩ በመቃብሩ ሽቱ ሊቀቡ ለመጡት ሴቶች "ሕያውን ከሙታን ጋር ለምን ትፈልጉታላችሁ?" እንዳላቸው እኛም ዛሬ ይህን የትንሣኤ ጌታ ወዴት እየፈለግነው ነው? ተስፋ ትንሣኤን ተስፋ በማድረግና በመልካም ሥራ ወይስ በዓለም ባለ ሁካታና ጫጫታ? ነዳያንን በማሰብ ወይስ ቁሳዊ ምቾትን በመፈለግ? ሥጋ ወደሙን በመቀበል ወይስ ምድራዊ መብል መጠጥን በማብዛት? በዓለማዊ ነገር ውስጥ ትንሣኤውን ማክበር ሕያዉን ከሙታን መንደር መፈለግ ነውና ትንሣኤን በትንሣኤው ንጉስ መንገድ በመጓዝ ልናከብረው ይገባናል።

ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል፤ መቃብሩ ባዶ ነው፤ ሕይወትን የሚሰጥ አምላክ በኃይልና በሥልጣን ሞትን ገድሎ በሞት ላይ አሸናፊዎች እንድንሆን ያደረገን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሰገነ ይሁን።

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ።
አባ ሕርያቆስ
የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ የሀድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

የስቅለት በዓል በጆሀንስበርግ ጽርሐ ጽዮን መንበረ ጵጵስና መድኃኔዓለም የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማዕምራን ብርሀኑ ተክለያሬድ በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።
18/04/2025

የስቅለት በዓል በጆሀንስበርግ ጽርሐ ጽዮን መንበረ ጵጵስና መድኃኔዓለም የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማዕምራን ብርሀኑ ተክለያሬድ በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።

በዓለ መድኃኔዓለም በጆሐንስበርግ ጽርሐ ጽዮን መንበረ ጵጵስና ካቴድራል
06/04/2025

በዓለ መድኃኔዓለም በጆሐንስበርግ ጽርሐ ጽዮን መንበረ ጵጵስና ካቴድራል

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የብሕንሳ ሚዲያ የበላይ ጠባቂ፣ ከአርባ ምንጭ ዚጊቲ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ...
16/03/2025

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የብሕንሳ ሚዲያ የበላይ ጠባቂ፣ ከአርባ ምንጭ ዚጊቲ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን የንግሥ በዓል አክብረው ሲመለሱ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ሕይወታቸውን ባጡና በተጎዱ ምዕመናን የተሰማቸውን ጥልቅ ኃዘን ገለጹ።

++++++++++++++++++++++
መጋቢት 7ቀን 2017 ዓ.ም
++++++++++++++++++++++

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የብሕንሳ ሚዲያ የበላይ ጠባቂ፣ከአርባምንጭ ዚጊቲ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን የጻድቁን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል አክብረው ወደ ሻሸመኔ ለመመለስ በጉዞ ባሉ ምእመናን ላይ በወላይታ ዞን በዳሞት ወይዴ ወረዳ በዴሣ ከተማ በደረሰ የትራፊክ የመኪና መገልበጥ አደጋ ሕይወታቸው እንዳለፈና እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን በጥልቀት ማዘናቸውን ገልጸዋል ።

በመጨረሻም ብፁዕነታቸውን በደረሰው የትራፊክ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች እግዚአብሔር አምላክ በቅዱሳኑ አጠገብ ነፍሳቸውን በአብርሃም በይስሐቅና በያዕቆብ አጠገብ ዕረፍተ ነብስን እንዲሰጣቸው በመመኘት በአደጋው ጉዳት ደርሶባቸው በሕክምና ላይ ለሚገኙ ተጎጂዎችም እግዚአብሔር ምሕረትን እንዲያወርድላቸው ተመኝተዋል ።

©ብሕንሳ ሚዲያ

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የሆሣዕና ካህናት ማሠልጠኛ ተቋም የ2017 ዓ/ም የ3ኛ ዙር 30 ደቀ መዘሙርትን ተቀብሎ ማሠልጠን ጀምሯል።በመክፈቻ መርሐ ግብር ላይ የማሠልጠኛው አስተዳደር ሰራ...
05/03/2025

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የሆሣዕና ካህናት ማሠልጠኛ ተቋም የ2017 ዓ/ም የ3ኛ ዙር 30 ደቀ መዘሙርትን ተቀብሎ ማሠልጠን ጀምሯል።

በመክፈቻ መርሐ ግብር ላይ የማሠልጠኛው አስተዳደር ሰራተኞች የሀገረ ስብከቱ የየክፍሉ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን የማሠልጠኛው ርዕሰ መምህር መጋቤ ሠናያት ፍስሐ ሀብተ ወልድ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል::

በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ዋና ጸሀፊ ክቡር መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ወርቁ ተክሌ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው ይህ የካህናት ማሰልጠኛ በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ አርቆ አሳቢነትና ከፍተኛ ጥረት በቅዱስ ሲኖዶስ ድጋፍ የተከፈተና ወደፊትም ወደ ኮሌጅነት ለማሳደግ በማሰብ ፕሮጀክት የሚቀርጹ የስልጠናውን ሒደት የሚቆጣጠሩ የራሱ አስተዳደር ሠራተኞች እንዲኖሩት ቋሚ ሠራተኞችን ለማሟላት በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ እየተመደቡ መሆኑን በመግለጽ ማሠልጠኛውን በሁለት ዕግሩ ለማቆምና ራሱን ለማስቻል ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውን በማሳሰብ ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ በመሆናቸው ሁላችንም ከሀገረ ስብከቱ የየክፍል ኃላፊዎች ጀምሮ የማሠልጠኛው አስዳደር ሠራተኞች በፍጥነት መሮጥ ይጠበቅብናል ብለዋል::

አያይዘውም የዚህ 3ኛ ዙር ሰልጣኞች ስልጠና በብፁዕነታቸው መመሪያ ሰጪነት በደቡብ አፍሪካ ሊምፖፖ ፕሮቪየንስ የመሲናና አካባቢው አገልጋዮችና ምእመናን ድጋፍ አድራጊነት የተገኘ ዕድል መሆኑን በመግለጽ ይህንን ድጋፍ ላደረጉት በደቡብ አፍሪካ ሊምፖፖ ፕሮቪየንስ የመሲናና አካባቢው አገልጋዮችና ምእመናን በሀገረ ስብከቱ ስም ምስጋና አቅርበው ለደ ቀመዛሙርቱ "መጠራታችሁን ተመልከቱ" በማለት በቆይታቸው የተጠሩበትን የቤተ ክርስቲያኒቱን ዓላማ እንዲረዱና ጠንክረው እንዲማሩ በማሳሰብ በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ መመሪያ ሰጪነት የ3ኛ ዙር ስልጠና በይፋ መጀመሩን አብስረዋል::

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲበረቱ ኃላፊነት እንዲሸከሙ ያስተላለፉትን መልእክት አንስተው የብፁዕነታቸውን ሸክም ማገዝ ይገባል እሳቸው እሄንን ያህል ጥረት ካደረጉ ከእኛ የሚጠበቀውን ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባልም ብለዋል::
በማስጀመሪያው መርሐ ግብሩ ላይም የሀገረ ስብከቱ ስብከተ-ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀ ስዩማን ቀሲስ አፈወርቅ ኃይሌ፣ የሀገረስብከቱ የቁጥጥር ክፍል ኃላፊው መ/ት ቀሲስ ዳዊት አብርሃምን ጨምሮ የካህናት ማሠልጠኛ ም/ ርዕሰ መምህር በኩ/ወ ፍራንሲስ ማዶሬ እና የማሠልጠኛ መጋቢ ላ/ወ ወገኑ ባደግ ተገኝተዋል::

በመጨረሻም ሰልጣኝ ደቀመዛሙርትም በአስተያየቶቻቸው ይህንን በማየታችን እድለኞች ነን በቆይታችን ከመምህራን የሚሰጠንን ትምህርት ተቀብለን የጠፉትን ወንድሞቻችንን ለመፈለግ ቁርጠኞች ነን ያሉ ሲሆን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ በጸሎት ፍጻሜውን አግኝቷል።

©ብሕንሳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሀይማኖት 12ተኛ በዓለ ሢመት በዛሬው እለት በመንበረ ፀባዖት ቅድስ...
03/03/2025

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሀይማኖት 12ተኛ በዓለ ሢመት በዛሬው እለት በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናውኗል፡፡

በዚህ ሥነ ሥርዓት ላይ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር የሆኑት ኖንቺባ ሎሲ አንዷ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያን የሀገር ባህል ልብስ ለብሰውና ፀጉራቸውን በሻሽ ሸፍነው በስፍራው የተገኙት አምባሳደሯ ቅዱስነታቸውን አግኝተው ለማነጋገር በመቻላቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል፡፡ አምባሳደር ሎሲ በኤክስ ገፃቸው ላይ ‹‹ይህ እምብዛም የማይገኝ እድል ነው›› ብለዋል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይም ብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ የሀድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተዋል።

ምንጭ-ዘሐበሻ

በሀዲያ እና ስልጤ ሀገረ ስብከት በአንሌሞ ወረዳ ቤተክህነት የፎንቆ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የካቲት 02/2017 ዓ/ም ከቀኑ 07:00 ሰዓት ላይ ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎ ደርሶበታል ።የ...
09/02/2025

በሀዲያ እና ስልጤ ሀገረ ስብከት በአንሌሞ ወረዳ ቤተክህነት የፎንቆ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የካቲት 02/2017 ዓ/ም ከቀኑ 07:00 ሰዓት ላይ ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎ ደርሶበታል ።

የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ የሀዲያ እና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ በቦታው ተገኝተው ምዕመኑን አፅናንተውና ከራሳቸው እና ከሀገረ ስብከቱ ጭምር ድጋፍ አድርገው ተመልሰዋል ::

09/02/2025

የወጎ ወጌላ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ምረቃት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ክቡር መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ባወቀ ፤ የሀገረስብከቱ የየመምሪያው ክፍል ኃላፊዎች የወረዳ ቤተክህነት ስራ አስኪያጆች ፣በተገኙበት እየተከበረ ይገኛል።

በሀዲያና ስልጤ ሀገረስብከት በአናሌሞ ወረዳ ቤተክህነት  በወጎ ወጌላ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ...
09/02/2025

በሀዲያና ስልጤ ሀገረስብከት በአናሌሞ ወረዳ ቤተክህነት በወጎ ወጌላ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 50 ኢ አማንያን ተጠመቁ !!

++++++++++++++++++++++++++++++
የካቲት 1ቀን 2017 ዓ.ም (ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና )
++++++++++++++++++++++++++++++++

08/02/2025

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በዱና ወረዳ ቤተክህነት የኦቶሮ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያ እና ስልጤ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ቡራኬ እየተመረቀ ይገኛል።

©ብሕንሳ ሚዲያ

በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት በማንፍሬይ ቅዱስ ገብርኤል ጉባኤና በኡምታታ ቅድስት ልደታ ለማርያም ጉባኤ ቤት ሐዋርያዊ ጉዞ ተከናወነ። ጥር 19/2017 ዓ/ም (ደቡብ አፍሪካ) ብጹዕ...
27/01/2025

በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት በማንፍሬይ ቅዱስ ገብርኤል ጉባኤና በኡምታታ ቅድስት ልደታ ለማርያም ጉባኤ ቤት ሐዋርያዊ ጉዞ ተከናወነ።

ጥር 19/2017 ዓ/ም (ደቡብ አፍሪካ)

ብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ የሀድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥር 16 እና 17 በማንፍሬና ኡምታታ አብያተ ጉባኤያት ሐዋርያዊ ጉዞ አከናውነዋል።

ብጹዕነታቸው ቅዳሜ ጥር 17/2017 ዓ/ም በማንፍሬ ቤተ ጉባኤ እየተገነባ የሚገኘውን የሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የጎበኙ ሲሆን በቀጣይ የሕንጻ ቤተክርስቲያኑን መጠናቀቅና በአገልግሎት ዙሪያ መመሪያ ሰጥተዋል።

በመቀጠልም እሁድ ጥር 18/2017 ዓ/ም በኡምታታ ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ጉባኤ በመገኘት ለሕንጻ ቤተክርስቲያን መገንቢያ ይሆን ዘንድ በ4.8 ሚሊየን ራንድ በተገዛው ቦታ ላይ የመሠረት ድንጋይ አኑረዋል።

በሐዋርያዊ ጉዞው የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማዕምራን ብርሀኑ ተክለያሬድ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ ሊቀ ሥዩማን ሰሎሞን ተገኝተዋል።

የከተራ በዓል በጆሐንስበርግ ከተማ ጽርሐ ጽዮን መንበረ ጵጵስና መድኃኔዓለም ካቴድራል በድምቀት ሲከበር"ወረደ ወልድ እምሰማያት ውስተ ምጥማቃት"ወልድ ከሰማያት ወደ መጠመቂያ ወረደ"
18/01/2025

የከተራ በዓል በጆሐንስበርግ ከተማ ጽርሐ ጽዮን መንበረ ጵጵስና መድኃኔዓለም ካቴድራል በድምቀት ሲከበር

"ወረደ ወልድ እምሰማያት ውስተ ምጥማቃት"
ወልድ ከሰማያት ወደ መጠመቂያ ወረደ"

Address

74 Tudhope Avenue, Berea
Johannesburg
2198

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Eotc south and west Africa Dioceses posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Eotc south and west Africa Dioceses:

Share