12/06/2026
Zechariah 1 አማ - ዘካርያስ
18: ዓይኖቼንም አንሥቼ እነሆ፥ አራት ቀንዶች አየሁ።
19: ከእኔም ጋር ይነጋገር የነበረውን መልአክ፦ “እነዚህ ምንድር ናቸው?” አልሁት። እርሱም፦ “እነዚህ ይሁዳንና እስራኤልን ኢየሩሳሌምንም የበተኑ ቀንዶች ናቸው፡” ብሎ መለሰልኝ።
20: እግዚአብሔርም አራት ጠራቢዎች አሳየኝ።
21: እኔም፦ “እነዚህ የመጡት ምን ሊሠሩ ነው?” አልሁ። እርሱም፦ “አንድ ሰው ራሱን እስከማያነሣ ድረስ እነዚህ ቀንዶች ይሁዳን የበተኑ ናቸው፤ እነዚህ ግን ሊያስፈራሩአቸው፥ የይሁዳንም አገር ይበትኑ ዘንድ ቀንዳቸውን ያነሡትን የአሕዛብን ቀንዶች ሊጥሉ መጥተዋል፡” ብሎ ተናገረ።