10/06/2026
ዛሬም መንፈስ ቅዱስ....መንፈስ ቅዱስ 🔥🔥🔥🙏
ትላንት ከእርሻ መጥቶ ያለ ውጊያ ልምድ በሬዎችን ቆራርጦ ለጦርነት ነጋሪት ጎስሞ ጠላትን ድባቅ መትቶ ከተማይቱን ያዳነው ብንያማዊው ሳኦል ዛሬ ከቤተመንግስት ወጥቶ፣ ተደራጅቶ፣ ልምድ ዝና እያለው በፍርሃት የራደው አልፎም ጠላትን የሚጥልለትን ማፈላለግ የተያያዘው ለምንድነው?
ካልን መልሱ ቀላል ነው ያኔ ያጀገነው የወረደበት መንፈስ ዛሬ ስለራቀው እንደሆነ በእነዚህ ክፍሎች መረዳት እንችላለን። (1ሳሙ 11:6፣ 16:14 ምዕ 17)
የትላንቱን ድል ዛሬም ለመድገም በመንፈስ ከመሞላት ውጪ ምን አማራጭ አለን? እንደ ሳኦል የሚጥልላችሁን በማፈላለግ እደጅ እደጁን የምታዩ ወዳጆቼ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ነውና በእኛ ለእኛ እኛን እንዲሠራ ዕድል እንስጠው።
ሌላኛው ብንያማዊው ሳውል ሐዋርያዊ ተልዕኮውን "ሀ"ብሎ ከአንጾኪያ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት አብያተ ክርስቲያናትን ከተከለ፣ "አማልክት ሰዎችን መስለው ወርደዋል" እስኪባሉ ምልክትና ድንቅ በእጆቹ ከተደረገ በኋላ
እንደ ቀድሞው የመንፈስ ቅዱስን ድምፅ ለመስማት፣ ለመመራት የተዘጋጀ ልብ ነበረው።
በሁለተኛውም ሐዋርያዊ ጉዞ ላይ ወደ እስያና ወደ ቢታንያ መንፈስ ቅዱስ እንዳይሄዱ ሲከለክላቸው ወደ ሜቅዶንያ እንዲሄዱ ሲልካቸው ለእርሱ ለመታዘዝ አልተቸገሩም።(ሐዋ 13 እና ሐዋ 16)። ከብዙ ስኬትና ድል በኋላም ያኔ ውጤታማ ባደረጋቸው በመንፈስ ቅዱስ ላይ እንጂ በልምምዳቸው አይታመኑም ነበር።
አደጉለት እንጂ አላደጉበትም። ልጅ ሲጎረምስ ለያዥ ለገራዥ የሚያስቸግርበት ጊዜ ይኖራል ልክ ከአባቱ ባገኘው ነገር ያለአባቱ መኖር እንደሚችል አስቦ ከስሮ እንደመጣው የጠፋው ልጅ (ጎረምሳው)
አለችኝ በምንላት ነገር ማካበዱን ትተን ለመንፈስ ቅዱስ ቀለል ብለን ለመላክ እንደግለት እንጂ አንጎርምስ ለማለት ነው።