Tigistu Beyene

Tigistu Beyene Gospel Singer

በዚህ ዘመን ብዙዎች ቅንነታቸውን ጥለው ሌላው እንዳያገለግል ስልክ ቁጥርህን እያወቁ እንኳ አላውቀውም! እያሉ በክፉትና ስር በሰደደ ተንኮል እግዚአብሔር የከፈተውን በር ለማዘጋት በሚታገሉበት ...
05/06/2026

በዚህ ዘመን ብዙዎች ቅንነታቸውን ጥለው ሌላው እንዳያገለግል ስልክ ቁጥርህን እያወቁ እንኳ አላውቀውም! እያሉ በክፉትና ስር በሰደደ ተንኮል እግዚአብሔር የከፈተውን በር ለማዘጋት በሚታገሉበት ጊዜ…….

ለብዙ ወጣት ዘማሪያን ድልድይ ስለሆነው ዘማሪ ይስሐቅ ሰዲቅ ትንሽ የማውቀውን ልንገራችሁ።

ካወቅሁት ጊዜ ጀምሮ ከእርሱ አልፎ ጥሩ ፀጋና የአገልግሎት ጥሪ ያላቸውን ወጣቶች በማበረታታትና በማገዝ እኔን ጨምሮ ለብዙ ወጣት ዘማሪያን መልካም ምስክርነት በመስጠት አብረውት እንዲያገለግሉ በተለያዩ ቤተክርስቲያናት፣ በሰርግና በተለያዩ ፕሮግራሞች ላይ እድል እየሰጠ እገዛ የሚያደርግ፣ ቅን የሆነ ሰው ነው። ዛሬም ይሄ ቅንነቱ እንዳልተወሰደበት ከብዙ ወጣቶች ሰምቻለሁ።

መልካም የሚያደርግ ሰው ምስጋና ይገባዋልና፣ ይሱ እግዚአብሔር ያደረግሀውን የሚረሳ እንደ ሰው ያልሆነ አምላክ ስላልሆነ እየባረከ ይባርክህ።🙏

ልበ ቅኖች እስቲ አብረን እግዚአብሔር በብዙ ፀጋና ሞገስ ይባርክህ እንበለው።

Zekariyas tadesse

01/06/2026

#እገሰግሳለው

01/06/2026

#አሜን

የቤተክርስቲያን ጉዳይ ግድ ይለኛል!በቤተክርስቲያን ጉዳይ የልጆቼም የትውልዴም ነገ ያሳስበኛል!በአህዛብ ዘንድ እንኳን የማይሰማ ግፍና አመፅ በእምነት ካባ ስር ድር ሲያደራ ያሳምመኛል!ሰሞቶ እ...
29/05/2026

የቤተክርስቲያን ጉዳይ ግድ ይለኛል!
በቤተክርስቲያን ጉዳይ የልጆቼም የትውልዴም ነገ ያሳስበኛል!
በአህዛብ ዘንድ እንኳን የማይሰማ ግፍና አመፅ በእምነት ካባ ስር ድር ሲያደራ ያሳምመኛል!
ሰሞቶ እንዳልሰማ አይቶ እንዳላየ ሁሌ ማለፍ ያታክታል!አንድላይ መጨ'ፍለቅም ይበቃል!ሚናም ሰፈርም መለየት ግድ ይላል!
የእናት ቤተክርስቲያኔ ቃለህይወት መሪዎች ትውልዱን ለመታደግ እያደረጋችሁት ስላለው የእረኝነት ተግባርና ብርቱ ትግል በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ አላችሁ ትውልድ ያመሰግናችኃል!

13/05/2026
01/05/2026

 #ይድረስ ለዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ጥላሁን ጉግሳበቅድሚያ የከበረ ሰላምታዬ ይድረስዎትበአንድ የእርስዎ ንግግር ላይ ስለዘፈን የተናገሩትን ሰምቼ እጅግ ተገርሜያለሁ “ግጥሙ ምንም ይሁን ምንም ለማ...
30/04/2026

#ይድረስ ለዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥላሁን ጉግሳ

በቅድሚያ የከበረ ሰላምታዬ ይድረስዎት
በአንድ የእርስዎ ንግግር ላይ ስለዘፈን
የተናገሩትን ሰምቼ እጅግ ተገርሜያለሁ “ግጥሙ ምንም ይሁን ምንም ለማንም ለምንም ተዘፈነ ዘፈን ሃጢአት ነው፡፡ አንድ መዝሙር ብቻ ይቻላል እሱም የኢትዮ ሕዝብ መዝሙር ነው “ ያሉትን ሰምቼ ምንም እንኳን ይሄኛው ይቻላል ያኛው አይቻልም የምልበት እውቀቱ ባይኖረኝም እርስዎ ስለተናገሩት ሀሳብና መልዕክትዎ ግን የከበረ አድናቆት እንዳለኝ ልገልጽሎትና ላመሰግኖት ወደድኩ፡፡
በዚህ ያልተነካካ እና ከወንጌል ጋር ብቻ ለወገነ መልዕክትዎ፤ ድንቅ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መምህር እንድሎት ይፈቀድልኝ፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየቸገረህ ያለው ብትሉኝ አቋም በሚፈልጉ ግልጽ ጉዳዮች ላይ ሆነ ብለው አቋም ላለመያዝ አቋም የያዙ ሰዎች! እጃቸውን ዘርግተው ማትጨብጧቸው Ghost የሆኑ፤ መስመር የሌላቸ...
23/04/2026

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየቸገረህ ያለው ብትሉኝ አቋም በሚፈልጉ ግልጽ ጉዳዮች ላይ ሆነ ብለው አቋም ላለመያዝ አቋም የያዙ ሰዎች! እጃቸውን ዘርግተው ማትጨብጧቸው Ghost የሆኑ፤ መስመር የሌላቸው ሰዎች አሉ።

ከቅርብ ጊዜ የመጣው አዲሱ ስትራቴጂ፤ አቋም ሳይይዙ መንሳፈፍ ነው። ለምን? ሁሉም ቤት ጣሪያ ላይ ማረፍ ያስችላል። ለዛ አዋጭ ነው። A ም ነኝ ደግሞም Z ም ነኝ። ከዚህ ከ A ጋር ፀብ የለም ከ Z ም ጋር ፀብ የለም፤ የሁሉም ወዳጅ ሆናችሁ መሄድ ከፈለጋችሁ፤ መንገዱ ውስብስብ አይደለም፤ አቋም አይኑራችሁ። በሁሉም ቤት አባወራ ላይ ዘፍ የሚል አሞራ ነው ምትሆኑት።

መንፈሳዊ ብስለት ወንድሞቼ እህቶቼ፤ ተንሳፋፊ አያደርግም። በዶክትሪን ግንባታ ውስጥ አልፎ ማደግ አቋም የለሽ አማኝ አያደርግም። ተፍገምጋሚ ተንገዋላይ አያደርግም። እንደዛ የሚያደርግም አስተምህሮአዊ ምክር ቅዱሳት መጻሕፍት የላቸውም። የእግዚአብሔር ቃል ምክር የሐዋርያት ትምህርት እርስ በእርስ ፈጽሞ የማይጣጣሙ የተቃረኑ ስድስት እና ሰባት አቋሞች ውስጥ እንዲሁ እየፈሰሳችሁ እንድትሄዱ የሚፈቅድ ምክር የላቸውም። ጤናማ ዶክትሪን እንደ መልህቅ ይይዛል። አንዴ ወደ ፊት አንዴ ወደ ኋላ አያስኬድም። ወዲያና ወዲህ አቅጣጫ የለም! ፖዚሽን የለም! ግራውንድ የለም! እንደሱ የሚያደርግ የአስተምህሮ አቀራረጽ የለም። ጤናማ ዶክትሪን እንደዚህ አያደርግም።

በአስተምህሮ መሬት የረገጠ ሰው ጽኑ ነው። ሀሰት ከየትም ይምጣ ከየትም አያፍገመግመውም። ከሁሉም ጋር ጎረቤት አይደለም! ቢቻላችሁ ነው ከሰው ጋር በሰላም ኑሩ የተባለው ስለማይቻል ነው። ከቻላችሁ ጥሩ፤ ግን አይቻልም። ሐዋርያትን ወንጌል ከሁሉም ሰው ጋር ሲያወዳጃቸው አናይም ። ዘመዳቸው ከቃሉ ጋር ዘመድ የሆነ ሰው ነው። ከቃሉ ጋር በግልጽ ጠብ የወጣን ሰው ጎረቤት የሚያደርግ አስተምህሮ ቀረጻ ብሎ ታሪክ የለም። ለምን የሰማይ ስባሪ አያክሉም። ከመላእክት ጋር ቡና እየጠጡ የሚወርዱ ሰዎች ለምን አይሆኑም! እሚፍገመገሙ ከሆነ ተንሳፋፊዎች ናቸው! ተጠበቋቸው። ጤናማውን አስተምህሮ፤ ከሀሰት ትምህርት ለይቶ ማወቅ የመንፈሳዊ ብስለት ምልክት ነው። በእግዚአብሔር ቃል ተኮትኩቶ የማደግ ምልክት ነው።ይሄ ሀሰት ነው! ይሄ እውነት ነው ማለት። ይሄ ጨለማ ነው ይሄ ብርሃን ነው ማለት። ሰኞን ሰኞ እንደምንል፤ ማክሰኞንም ማክሰኞ እንደምንል፤ አንዳንዱን ትምህርት አንዳንዱን እንቅስቃሴ አንዳንዱን ጎራ፤ አንዳንዱን ስብስብ ይሄ ከሰይጣን ነው፤ ይሄ ከክርስቶስ ነው ማለት ይጠበቅብናል።

ስለዚህ በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ከንግዲህ ህጻናት መሆን አይገባም። ይሄ የሐዋርያው የጳውሎስ ምክር፤ ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ፤ ከዘመናት በኋላ የኤፌሶንን ቤተ ክርስቲያን ጠቅሟት ነው ያየነው።

ሐዋርያት ሳይሆኑ ሐዋርያት ነን የሚሉትን መርምረህ ሐዋርያ እንዳልሆኑ ደርሰህባቸዋል። ይህንን አደንቅልሃለው ብሏቸዋል ጌታችን። ይሄ ሐዋርያዊ ትምህርት ተጽፎ ስለተሰጣቸው፤ እንዲህ ባለ አስደናቂ ምክር ተገርተው ስላደጉ፤ ሐዋርያ ያልሆነውን ሐዋርያ አይደለህም ብለው ዞር ያደርጉት ነበር።

መንፈሳዊ መደባለቅ፤ ጎራ መደባለቅ በበዛበት የትምህርት አውራቂስ፤ የሀሰት ማዕበል፤ የብዙዎችን ታንኳ እየመታበት ባለበት በዚህ ዘመን ውስጥ፤ ሰዎችን ከእውነት መንገድ ዞር የሚያደርጉ፤ መጽሐፍ እንደሚል የአንዳንዶችን እምነት የሚገለብጡ፤ እምነት ገልባጮች እውነቱን ከላይ አሳይተው ሀሰትንና መርዝን ከታች አስርገው፤ አሽሉከው የሚያስገቡ በበዙበት በዚህ ዘመን፤ የመስቀሉ ስር ቁማርተኞች gamblers በረቂቅ ተንኮል እንደወጣ ቁማርተኛ፤ በወንጌል ላይ ቁማር ለመስራት የወጡ ሰዎች የመድረክ ላይ አፈ ቀላጤነትና ጮሌነታቸውን ተጠቅመው ብዙ የዋሆችን በእግዚአብሔር ቃል ያላደጉትን የሚያስቱ ሰዎች፤ በጾታ በቀለም በበዙበት በዚህ ዘመን ውስጥ እንደ ህጻናት መሆን አያስፈልገንም።

በአስተምህሮ ንፋስ ወዲያና ወዲህ መፍገምገም አያስፈልገንም። በማዕበል ወደ ፊት ወደ ኋላ መሄድ አያስፈልገንም። ከመንፈሳዊ ሕፃንነት መውጣት አለብን። በእግዚአብሔር ቃል በሐዋርያቱ ምክር በተቀበልነው በዚያ አንድ ሃይማኖት እስከመጨረሻ ጸንቶ የመቆም ቁርጠኝነት እያንዳንዳችን ይጠበቅብናል። እግዚአብሔር በሰማያዊ ስፍራ እግዚአብሔር በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ ከባረካችሁ በፊቱ ቅዱሳንና አለ ነውር ትሆኑ ዘንድ አለም ሳይፈጠር በክርስቶስ ኢየሱስ በፍቅር ከመረጣችሁ እንደ በጎ ፈቃዱ አስቀድሞ ከወሰነን በክርስቶስ ኢየሱስ ህያዋን ካደረገን በሐዋርያትና በነቢያት መሰረት ላይ የታነጽን ከሆንን እንደ አካል ደግሞ እየተገነባን ሙሉ ሰው እንድንሆንለት የአገልግሎት ስራም እንዲበዛልን መልእክተኞችን ነቢያትን እረኞችን አስተማሪዎችን ከሰጠን ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስጦታዎችን ከሰጠን እንደዚህ ያሉ ነገሮች ደግሞ የበዛላቸው አማኞች ከሆንን ከንግዲህ በማዕበል ወደ ፊትና ወደ ኋላ እየተነዳን በልዩ ልዩ አይነት የትምህርት ንፋስ በሰዎችም ረቂቅ ተንኮልና ማታለል ወዲያና ወዲህ እየተንገዋለልን ህጻናት መሆን አይገባንም።

#አገልጋይ ሳሚ ቱራ

23/04/2026

ሰምቼ ነበር በጆሮዬ
አሁን ግን አየችህ አይኔ

Address

Durban

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tigistu Beyene posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Tigistu Beyene:

Share