05/06/2026
በዚህ ዘመን ብዙዎች ቅንነታቸውን ጥለው ሌላው እንዳያገለግል ስልክ ቁጥርህን እያወቁ እንኳ አላውቀውም! እያሉ በክፉትና ስር በሰደደ ተንኮል እግዚአብሔር የከፈተውን በር ለማዘጋት በሚታገሉበት ጊዜ…….
ለብዙ ወጣት ዘማሪያን ድልድይ ስለሆነው ዘማሪ ይስሐቅ ሰዲቅ ትንሽ የማውቀውን ልንገራችሁ።
ካወቅሁት ጊዜ ጀምሮ ከእርሱ አልፎ ጥሩ ፀጋና የአገልግሎት ጥሪ ያላቸውን ወጣቶች በማበረታታትና በማገዝ እኔን ጨምሮ ለብዙ ወጣት ዘማሪያን መልካም ምስክርነት በመስጠት አብረውት እንዲያገለግሉ በተለያዩ ቤተክርስቲያናት፣ በሰርግና በተለያዩ ፕሮግራሞች ላይ እድል እየሰጠ እገዛ የሚያደርግ፣ ቅን የሆነ ሰው ነው። ዛሬም ይሄ ቅንነቱ እንዳልተወሰደበት ከብዙ ወጣቶች ሰምቻለሁ።
መልካም የሚያደርግ ሰው ምስጋና ይገባዋልና፣ ይሱ እግዚአብሔር ያደረግሀውን የሚረሳ እንደ ሰው ያልሆነ አምላክ ስላልሆነ እየባረከ ይባርክህ።🙏
ልበ ቅኖች እስቲ አብረን እግዚአብሔር በብዙ ፀጋና ሞገስ ይባርክህ እንበለው።
Zekariyas tadesse