08/02/2026
ቅዱስ መንፈስህን ከእኔ አትውሰድበኝ።
ይህ አነጋገር ዳዊት በፀሎት መንፈስ ከአምላኩ ጋር የተነጋገረበት ቃላት በመሆኑ ይታወቃል እኛም ዛሬ እንዲህ እንላለን:- ከፊትህ አትጣለኝ፥ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ።
መዝሙር 51:11
የሃማኖት ዋናው ክፍፍል አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ አካል ናቸው የሚል እና አንድ ነው የሚል ስሆን የተለያዩ ናቸው የሚሉት መንፈስ ቅዱስ ራሱ እግዚአብሔር ነው የራሱ አካል አለ የሚል አቋም ያላቸው ናቸው።
በዚህ ክፍል ዳዊት :-ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ። ስል
1ኛ ማነው የመንፈሱ ባለቤት የምወስደው ?
2ኛ እግዚአብሔር እግዚአብሔርን ይወስዳል ?
መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ሁለተኛ ከእግዚአብሔር የተለየ አካል የያዘ አምላክ አይደለም።
ከሁሉ በላይ የሆነው የመንፈሱም የልጁም ባለቤት የሆነው አንድ አምላክ አብ አለን ፤የእግዚአብሔር መንፈስ የእግዚአብሔር ልጅ በመባል መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው ምክንያት #የ የሚል ቅጥያ ባለቤትነት ገላጭ ሆኖ ይገኛል።
ለእግዚአብሔር መንፈስ ያለው አመለካከት በትክክል በመረዳት እስከ ኢየሩሳሌም እንደ ዳዊት ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ እያለን እንኑር።
የእግዚአብሔር ቃል እንደሚናገረው በ ቅንነት ቃሉን በመማር እና በማወቅ እንድንኖር ያ የእሥራኤል አምላኩ አንዱ ይርዳን።
አሜን
ወንድማችሁ ነኝ