Cape Town Ethiopian Orthodox Church ደብረ ምህረት መድኃኔዓለምና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን

  • Home
  • South Africa
  • Bellville
  • Cape Town Ethiopian Orthodox Church ደብረ ምህረት መድኃኔዓለምና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን

Cape Town Ethiopian Orthodox Church ደብረ ምህረት መድኃኔዓለምና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን Debre Mihret Medhanealem & St Gabriel Ethiopian Orthodox Church started as a congregation in 2006. With God's grace it has now grown to a church in Feb, 13

06/09/2025

ጳጉሜ 1/2017

👉በስመ አሐዱ አምላክ አሜን ብለን በማመን በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ከነሐሴ ወር መጨረሻ በኋላ ጳጉሜ የምትባል አምስት ወይም ስድስት ቀን አለች እንኳን አደረሰን

👉ጳጉሜን ወር እንዳንላት 25 ቀን ይጎላታል ሳምንትም እንዳንላት 2 ቀን ያንሳታል ለወርም ለሳምንትም አቅም የሚያንሳት #ጳጉሜ በአመቱ መጨረሿ ላይ ትገኛለች

👉ጳጉሜ የሚለው ስያሜ #ኤፓጉሜኒ 'ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጓሜው "ተጨማሪ" ማለት ነው በመሆኑም ጳጉሜ የአመቱ ምራቂ ቀናት እንጂ ወር ወይም ሳምንት አትባልም

👉አውሮፓውያን በአመቱ ወራት ውስጥ በታትነዋታል ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ሊቃውንት ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ሳያደርጉ በማድረግ የአመቱን ቀን 365 ወይም 366 ቀን ብለው ደምረውታል

👉ጳጉሜ በየአመቱ አምስት ወይም ስድስት ቀን ሆና የምትመጣ ናት አንዴ ጳጉሜ ስድስት ሆና ትመጣለች በዚህም የአመቱ በዓላት ቀናትን ትቀይረዋለች ለምሳሌ የገና በዓል በአራት አመት አንዴ ታህሳስ 28 ቀን ሲውል ሌላውን ግን 29ኝ አይለቅም

👉በዚህም ኢትዮጵያ የ13 ወር ፀጋ ባለቤት እና ከአፍሪካም ከአለም ብቸኛ የሯሷ አቆጣጠር ያላት ሀገር ያደርጋታል እስካሁን ሳይንስ ያልደረሰበት ነገር ግን የቤተክርስቲያን ሊቃውንት በሚገባ የሚያውቁት ጳጉሜ ትሆናለች ለዚህም ብቸኛዋ ማስረጃ ተዋህዶ ሐይማኖትና ስንዱዋ እመቤት ቅድስት ቤተክርስቲያን ናት

👉የጳጉሜ ፆም ይህች ፆም ከሁለቱ የፈቃድ ፆም አንዷ ናት አንዱ ፆመ ፅጌ ሲሆን ሁለተኛዋ ይህች የጳጉሜ ፆም ናት በብዙሀን ዘንድ ባትታወቅም ታላቅ የበረከት እና እራስን የም
ናድስባት ጾም ነች

👉የጳጉሜ ፆም ፆመ ዮዲት በመባልም ትታወቃለች ይህም
ዮዲት እራሷ #ስለፆመችው ነው ዮዲት ስላችሁ የቤተክርስቲያን አጥፊ የሆነችው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነ አስምሩልኝ

👉ዮዲት ጠላቷን ማጥፋት የቻለችው በፆም እና በፀሎት #ከእግዚአብሔር አምላክ ሀይልን አግኝታ ነው ሙሉ ታሪኩን መፅሐፍ ቅዱስ ላይ መፅሐፈ ዮዲት ላይ ይመልከቱ

👉ሌላው ይቺ ጳጉሜ መታሰቢያ ቀን ነች
እርሱም በደብረ ዘይት ሳለ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው ንገረን ይህ መቼ ይሆናል የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድ ነው አሉት ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ ብዙዎችንም ያስታሉ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ

👉አትደንግጡ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው ሕዝብ በሕዝብ ላይ ላይ ይነሣልና ራብሞ ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል እነዚህም ሁሉ መጀመሪያ ናቸው ማቴ.24 ሙሉዉ ይነበብ

👉ጳጉሜ የአመቱ መገባደጃና መሸጋገሪያ እንደመሆኗ መጠን እጅግ ድንቅ ቀን ናት ይህች ወር መታሰቢያ ናት የዘመነ ፍዳ መገባደጃ ከቁር ብርዱ መላቀቂያ በመሆኗ ብዙ እና አያሌ ጥቅም አላት

👉ስለዚህ ምዕመናን በየአመቱ #ጳጉሜን የቻለ በመፆም በመፀለይ መጪውን አመት የተሻለ እንዲሆን እራስን በማዘጋጀት ፀበል በመጠመቅ በልዩ ዝግጅት ያሳልፋሉ

👉እኛም ይቺን በዓመት አንዴ የምትገኝ ዕለት ስለ #ሐገራችንና ሠላም ስለ #ህዝባችን ፍቅርና አንድነት እየፀለይን ለመሪዎቻችንንም ህዝቡን የሚመሩበትን ጥበብ እንዲሠጥልን የቻልን እየፆምን ስለ እራሳችን ሀጢአት እያለቀስን ንስሀ ገብተን ከሀጢአት የፀዳ አዲስ አመት ለመቀበል ፈጣሪ ይፈቀድልን ዘንድ እየተማፀንን መጪዉ አዲስ አመትም ሆና የምታርፍበት አዲስ አመት እንዲሆንልን የቅዱሣኑ ሁሉ ፀሎት ከኛ ጋር ይሁን "አሜን" ✝️ 💒 ✝️

👉 ጳጉሜ 1/2017 ዓ/ም
ከሊቀ መዘምራን ይልማ ሐይሉ

06/09/2025

ወርኃ ጳጉሜን

የሰው ልጅ እግዚአብሔር አምላኩ ባደለው ሥጦታ ‹ጊዜ› በሕይወት ዘመኑ በበጎ ምግባር እንዲኖርና በጸሎት በጾም እንዲተጋ በዓመታት፣ በወራት እና በቀናት ምልልስ በሚያገኘው ዕድል ዘወትር ፈጣሪውን ደስ የሚያሰኝ ሥራ ሊሠራ እንዲገባ የጊዜ ጭማሪ ተደረገለት፡፡ ይህችም የጭማሮ ጊዜ እስከ ዕድሜው(ዘመኑ) መጨረሻ ከኃጢአት በሙሉ ይነጻ እንዲሁም ጸጋ በረከትን ያገኝ ዘንድ የቀናት ምርቃት ሆነችለት፤ ‹የጳጉሜን ወር› (ወርኃ ጳጉሜን) ተብላም ተሰየመች፡፡

ወርኃ ጳጉሜን እንደሌሎቹ ወራት ፴ ቀናት ሳይሆን በአራት ዓመት አንዴ ማለትም በዘመነ ዮሐንስ ስድስት ቀናት ሲኖራት በዘመነ ማርቆስ፣ በዘመነ ሉቃስና በዘመነ በማቴዎስ ደግሞ አምስት ቀናት ብቻ ይኖራታል፤ ነገር ግን የዓመቱ ዐሥራ ሦስተኛ ወር ተደርጋ ትቆጠራለች፡፡

ጳጉሜ የሚለው ስያሜ ‹‹ኤፓጉሜኔ›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ‹‹ጭማሪ›› ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭)

ወርኃ ጳጉሜን ካሳለፍነው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት፣ ከዘመነ ክረምት ወደ ጸደይ መሸጋገሪያ በመሆኗ የዓለም ፍጻሜ መታሰቢያ ተደርጋም ትታሰባለች፡፡ ዳግም ምጽአት ከምድራዊ ሕይወት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት መሸጋገሪያ ናትና፡፡ ጳጉሜን የክረምት ማብቂያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም እንዲሁም የዚህ ዓለም ኑሮ ማብቂያ ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜን አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ጻድቃን አዲሲቷን ምድር (መንግሥተ ሰማያትን) ለመውረስ የበቁትን ‹‹እናንተ በ የአባቴ ብሩካን ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ›› የሚባሉባት ዕለት ናት፡፡ በዚህም የተነሣ ብዙ ምእመናን በወርኃ ጳጉሜን በጾምና በጸሎት ይተጋሉ፡፡ የጳጉሜ ጾም ከሌሎቹ የዓመቱ አጽዋማታችን መካከልና የዓመቱ መደምደሚያ ጾማችን በመሆኗ ብዙዎች በዚህ ወቅት ሱባኤ ይገባሉ፡፡ (ማቴ.፳፭፥፴፬)

ከዚህም ጋር ተያይዞ በቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል በጳጉሜን ሦስት ሰማያት የሚከፈቱበት (ርኅዎተ ሰማይ) በመሆኑ በዚህች በተከበረችው ዕለት ምእመናን ጸሎታቸው ያርግላቸው ዘንድ ከምን ጊዜውም በበለጠ ተግተው ይጸልያሉ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን የእኛም ጸሎታችንን በምልጃቸው የሚያሳርጉልን ቅዱሳን መላእክትም መሥዋዕቱን የሚያሳርጉበትና የአምላካችንን ምሕረት ቸርነት ለሰው ልጆች የሚያወርዱበት ዕለት ነው፡፡

ከፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ የሆነውም ‹ጾመ ዮዲት (የዮዲት ጾም)› በዚህ በጳጉሜን ወር የምንጾመው ነው፡፡ ዮዲት በናቡከደነጾር ዘመነ መንግሥት ትኖር የነበረች ስትሆን በንጽሕና ተጠብቃ፣ በጸሎትና በሕገ እግዚአብሔር የምትኖር ሴት ነበረች፡፡ የፋርስ ንጉሥ ናቡከደነጾር በሠራዊቱ ተመክቶ ጠላት አጥፋ ድንበር አስፋ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልህ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር አበጋዙ ሆሎፎርኒስ ትእዛዝ ሰጠ፡፡ እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ ፲፪ ሺህ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡ ፲፪ ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሄድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ፤ በዚህም ብዙ ጥፋት በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡ በዚያን ጊዜ ንጉሡ ሥልጣኑን መከታ በማድረግ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በግድ እያስገደደ እጅ መንሻ ይቀበል ነበር፡፡ የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበለውንም እየገደለ፣ ጭፍሮቹ ኃያልነቱንና ገናናነቱን በአዋጅ በጦር አዛዦች ጭምር እያሳወጀ፣ በርካታ የጦር ሠራዊቶችን አሰልፎ ከአይሁድ ከተማ ገባ፡፡ በዚያም ነዋሪዎችን በማስፈራራት የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበሉትን ሁሉ እያሳደደ ስላስጨነቃቸው ማቅ ለብሰው፣ አመድ ነስንሰውና ድንጋይ ተንተርሰው ወደ ፈጣሪያቸው በመጮህ መለመን ጀመሩ። በጭካኔ የተሞላው የጦር አበጋዙ ሆሎፎርኒስም ይበልጥ እጅግ እንዲሠቃዩ ውኃ የሚቀዱበትን ስፍራ ተቆጣጠረው፤ በግዴታ ማርኮም እጅ እንዲሰጡ እንዳደረጋቸው በመጽሐፈ ዮዲት ላይ ተጽፏል፡፡ በአካባቢው ይኖር የነበረ ዖዝያን የተባለ አንድ ሰው የአባቶቻቸው አምላክ ጸሎታቸውን እንዲሰማቸው ለአምስት ቀናት በትዕግሥት ይጾሙና ይጸልዩ ዘንድ ሕዝቡን መከራቸው፤ እነርሱም በትዕግሥት ሊጠብቁ ተስማሙ፡፡ (ዮዲ. ፪፥፪-፳፰፣፬፥፲፫)

ሕዝበ እስራኤል የናቡከደነጾርን ጦር ተዋግተው ለመርታት ካልሆነ ግን እጅ ለመስጠት ተመካከሩ። ነገር ግን ዮዲት እግዚአብሔርን የምትፈራ ብቸኛዋ ሴት እርሷ ነበረችና ምክክራቸውን ስትሰማ ለምን «እግዚአብሔር ያድነናል አትሉም» ብላ ገሠጸቻቸው፡፡ ማቅ በመልበስ፣ አመድ በመነስነስና ድንጋይ በመንተራስም ሱባኤ ገባች። በሦስተኛው ቀንም እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቧን የምታድንበትን ጥበብ ገለጸላት፤ ዮዲትም እግዚአብሔር የሰጣትን ውበት ተጠቅማ ሕዝቧን ከጥፋት የምትታደግበትን ጥበብ ተረዳች። (ዮዲ. ፱፥፲፫)

በአልባሳትም ተሸልማ፣ ሽቱ ተቀብታና ተውባ የጠላት ሠራዊት ወዳሉበት የጦር ሰፈር በድፍረት ተጓዘች፡፡ ሠራዊቱም ውበቷን አይተው እጅግ በመደነቅ «ይህችስ ለአለቃችን ትገባለች» ተባብለው ከጦር መሪያቸው ዘንድ ወሰዷት። ዮዲትም ቀድማ ከጠላቷ ማምለጫ መንገድ አዘጋጅታ ስለነበር የሠራዊቱ አለቃ ወደ ነበረበት ሥፍራ ከገባች በኋላ «ክቡር ጌታዬ ሆይ ርስት ተወስዶብኛል፤ እንድትመልስልኝ አስቀድሜ ደጅ ልጠና መጥቻለውና ርዳኝ፤ ትብብርህ አይለየኝ» ብላ ጠየቀችው፡፡ የሠራዊቶቹ አዛዥም በዝሙት መንፈስ ታውሮ ስለነበር የጠየቀችውን እንደሚፈጽምላት ነገራት። ዮዲትም ባማረ ድንካን አስቀመጣት፤ በእግዚአብሔር ረዳትነትም ጥበቧንም ተጠቅማ ማምለጫዋን አዘጋጀች፡፡ (ዮዲ. ፲፥፳፫፣፲፩፥፳፫)

ዮዲትም ለቀናት በድንኳኑ ከተቀመጠች በኃላ የሠራዊቱ አበጋዝ የምሳ ግብዣ አዘጋጅቶ ከጎኑ አስቀመጣት፤ ከበሉና ከጠጡ በኋላም ሁሉን ሰው አስወጥቶ እልፍኙን በመዝጋት ከእርሷ ጋር ብቻውን ቀረ፤ ነገር ግን እንቅልፍ ጣለው፡፡ በዚያን ጊዜም ዮዲት ወደ አምላኳ በመጸለይ ፈጣሪዋ እንዲረዳት ለመነች። ከዚህ በኋላ የሠራዊቱን አለቃ ከራስጌው ሰይፉን በማንሣት አንገቱን ቀላችው፤ በድኑንም ከመሬት ጣለችው። የሆሎፎርኒስን ሞት ሠራዊቱ በሰሙ ጊዜም በያሉበት ተበተኑ። እስራኤላውያንም ከሞት ተርፈው በእግዚአብሔር ኃይል ድል አደረጉ፤ በደስታም ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ። (ዮዲ. ፲፪፥፪፣፲፫፥፳)

ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት በመትጋት እንዲሁም በእግዚአብሔር አምላክም ኃይልና ብርታት ነው፡፡ ስለዚህ እኛም ሰዎች ጥንተ ጠላቶታችንን ለማሸነፍ በወርኃ ጳጉሜን ፈጣሪያችንን በጾም በጾሎት ተግተን ልንማጸነው በፈቃድ እንጾማለን፡፡

ጠንካራዋ ሴት ዮዲት ጠላቶቿን ድል ያደረገችው ሱባኤ በመግባት በጸሎትና በጾም በመትጋት በመሆኑ ይህንን ታሳቢ በማድረግ እንደ እርሷ ሱባኤ ገብተን፣ ማቅ ለብሰን፣ አመድ ነስንሰንና ድንጋይ ተንተርሰን አብዝተን ልንጾምና ልንጸልይ ይገባል፡፡ ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ ሰላም፣ ፍቅርና አንድነትን አሳጥቶ፣ እርስ በርስ አጣልቶ እንዲሁም ከክብራችን አዋርዶ ወደ ዘለዓለማዊ እሳት ሊጥለን ዘወትር ይቃጣልና ሳንታክት መጸለይና መጾም ይገባናል፡፡

ወርኃ ጳጉሜን በመልካም ሥነ ምግባር ታንጸን በሃይማኖት ጸንተን፣ ለዘመነ ማርቆስ እንድንደርስ አምላካችን እግዚአብሔር ይርዳን፤ አሜን።

06/09/2025
23/05/2024
ታላቅ የምስራች!ለኬፕታዎንና አከባቢዋ ምእመናን*****************ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ...
13/05/2024

ታላቅ የምስራች!
ለኬፕታዎንና አከባቢዋ ምእመናን
*****************

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት ታጅበው እሁድ ግንቦት 11/2016ዓም እኛን ለመባረክ ኬፕታዎን ይመጣሉ።
የቅዱስ አባታችንና የብፁአን አባቶችን በረከት ለማግኘት እሁድ ከቀኑ 10 ሰዓት(4PM)በኬፕታዎን አለም አቀፍ አየር ማረፊያ የአቀባበል መርሃግብር የሚደረግ፤ እንዲሁም ከ11:00ሰዓት (5PM)ጀምሮ በኬፕታዎን ደብረ ምህረት መድኃኔዓለምና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በሚደረገው መርሃግብር ላይ እንድትሳተፉ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም በጤና አደረሳችህ አደረሰን።"በፍሰሐ ወበሰላም ወረደ ወልድ ውስተ ምጥማቃት"
18/01/2024

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም በጤና አደረሳችህ አደረሰን።

"በፍሰሐ ወበሰላም ወረደ ወልድ ውስተ ምጥማቃት"

የእግዚአብሔር ቤተስቦች የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የቃልኪዳን ልጆች የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ግብርኤል ባለሟሎች በያላችሁበት ታህሳስ 19/2016  ለሚከበረው ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገ...
26/12/2023

የእግዚአብሔር ቤተስቦች የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የቃልኪዳን ልጆች የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ግብርኤል ባለሟሎች በያላችሁበት ታህሳስ 19/2016 ለሚከበረው ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልን።
የኬፕታዎን ደብረ ምህረት መድኃኔዓለምና ቅዱሰ ገበርኤል ቤተ ክርስቲያን የታላቁን ሊቀ መልአክ የቅዱስ ገብርኤልን አመታዊ ክብረ በዓል እሁድ ታህሳስ 21/2016(December 31/2023)በታላቅ ድምቀት ይከበራል። በአሉ ልሶስት ተከታታይ ቀናት አርብ በቅዳሴ ዋዜማው ቅዳሜ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ከመላው ደቡብ አፍሪካ በተጋበዙ አባቶች ካህናት መምህራንና የሰንበት ትቤት ዘማርያንና ምዕመናን በጋራ በመሆን በስብከተ ወንጌል በመዝሙርና በማህሌት አገልግሎት መርሃግብር የሚከበር ሲሆን እርሶዎም በዚህ በፈረንጆች ዘመን መለወጫ ዋዜማ በውቧ ኬፕታዎን የታላቁን ሊቀ መልአክ ታላቅ አመታዊ ክብረ በዓል ከዋዜማው ቅዳሜ ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን በመገኘት ከበዓሉ በረከት ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ ቤተ ክርስቲያናችን በመላው ደቡብ አፍሪካ ላሉ የተዋህዶ ልጆች መንፍሳዊ ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

Address

2 Small Street
Bellville
7530

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Cape Town Ethiopian Orthodox Church ደብረ ምህረት መድኃኔዓለምና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Cape Town Ethiopian Orthodox Church ደብረ ምህረት መድኃኔዓለምና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን:

Share