08/29/2016
ሰላም!
ትላንት በየቤተክርስቲያችን ብዙ ነቢያት በፊታችን ሲቀቡና:የት እንደሚደርሱ ሲነገር ሰምተናል። ዛሬ ግን ያን ሁሉ ረስተን እነሱ የተባሉት ቦታ ደርሰው ሲታዩ:ትላልቅ ሚኒስትሪ ከፍተው ሲንቀሳቀሱ ከየት መጣችሁ በሚመስል ጥያቄ ሁላችንም ተቃውሞና ትችት ጀመርን። ለወንጌል መሰናክል በሚሆን መንገድ በየሶሻል ሚዲያው የቤተክርስቲያንን ጉድለትና ችግር:የአገልጋዮችን ድካምና ጉድለት ሰባኪዮች ሆንን። ይህንን ሁሉ በቦታው ላይ ሆኖ ማስተካከልና መፍታት ስንችል። እንደ እኔ ሶሻል ሚዲያ የወንጌል ማሰራጫ ቢሆን ጥሩ ነው። ያኔ ብዙዎች ወደ ጌ ይመጣሉ። ወንጌል ይሰፋል። በውጪ ላሉት ጥያቄ አይሆንም። ይህን ሁሉ ስል ግን:ችግር የለም ሁሉም መልካም ነው ልክ ነው ማለቴ እንዳልሆነ ተረዱኝ። እንኳን ነብይ ትንቢትን እራሱ እንድንመረምር እግዚአብሄር ፈቅዶልናል። ስለዚህ ስራችን ወንጌል ብቻ ይሁን። እስካሁን በጠቀስኳቸው ነገሮች ላይ አብያተክርስትያናት ብዙ መስራት እንዳለባቸው ይሰማኛል።
አመሰግናለው! ተባረኩ።