AmlekoTube - አምልኮቲዩብ

AmlekoTube - አምልኮቲዩብ ቤተክርስቲያንን መሰረት ያደረጉ መንፈሳዊ መዝሙሮች,ስብከቶች እና ዜናዎች የሚቀርብበት ገፅ።
Ethiopian Christian Gospel songs, preaching and News page (Mark 16:15)
(877)

"እንዲህም አላቸው፡- ‹ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፡፡" (የማርቆስ ወንጌል 16፡15)

"And he said unto them, Go ye into all the world, and preach the gospel to every creature."

በህንድ በክርስቲያኖች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እየጨመረ መሆኑ ተገለጸበህንድ በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ጥቃት፣ ማስፈራራትና መድሎ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን የህንድ ወንጌላዊ ፌሎውሺፕ የሃይማ...
05/28/2026

በህንድ በክርስቲያኖች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ

በህንድ በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ጥቃት፣ ማስፈራራትና መድሎ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን የህንድ ወንጌላዊ ፌሎውሺፕ የሃይማኖት ነፃነት ኮሚሽን (EFIRLC) ባወጣው አመታዊ ሪፖርት ገልጿል።

ሪፖርቱ በ2025 ብቻ 747 የጥቃትና የጥላቻ ክስተቶች መመዝገባቸውን ያሳያል። ይህም በ2024 ከተመዘገቡት 640 ጉዳዮች በላይ ሲሆን፣ በ2014 ከነበሩት 147 ጉዳዮች ጋር ሲነጻጸር ከአምስት እጥፍ በላይ ጭማሪ መኖሩን ያመለክታል።

ኮሚሽኑ በዓመቱ 915 በላይ ሪፖርቶችን ቢቀበልም፣ 747ቱ ብቻ ከበርካታ ገለልተኛ ምንጮች በተደረገ ጥብቅ ማረጋገጫ የተረጋገጡ መሆናቸው ተገልጿል።

የህንድ ወንጌላዊ ፌሎውሺፕ ዋና ጸሃፊ ቄስ ቪጃዬሽ ላል፣ “የሕሊና ነፃነትና የሕግ እኩልነት ለሁሉም ዜጎች መከበሩን ማረጋገጥ አስፈላጊ ነው” ሲሉ ገልጸዋል።

ሪፖርቱ በህንድ ያሉ አናሳ ክርስቲያኖች በቀጣይነት ከግፍ፣ ከጥቃትና ከማስፈራራት ጋር እየተጋፈጡ መሆናቸውን በግልጽ አመላክቷል።

በዳንኤል አንተነህ

ዘገባው፤ የክርስቲያን ክርስቲያን ኮንሰርን ነው።

ዶ/ር ወንድማገኝ አስፋው የGFC የምስራቅ አፍሪካ ዋና አስተባባሪ ሆነው ተሾሙዶ/ር ወንድማገኝ አስፋው በGlobal Fellowship of Churches (GFC) የምስራቅ አፍሪካ ዋና አስተባ...
05/28/2026

ዶ/ር ወንድማገኝ አስፋው የGFC የምስራቅ አፍሪካ ዋና አስተባባሪ ሆነው ተሾሙ

ዶ/ር ወንድማገኝ አስፋው በGlobal Fellowship of Churches (GFC) የምስራቅ አፍሪካ ዋና አስተባባሪ ሆነው በይፋ ተሾሙ። ህብረቱ በቀጠናው የቤተክርስቲያን አንድነትን ለማጠናከርና የወንጌል ተልዕኮን ለማስፋፋት ያለመ አስፈላጊ ሹመት መሆኑን ገልጿል።

በምሁራዊ ብቃታቸው፣ በክርስቲያናዊ አመራር ችሎታቸው እና በሰላም ግንባታ ዘርፍ ባላቸው ልምድ የሚታወቁት ዶ/ር ወንድማገኝ፣ በምስራቅ አፍሪካ ያሉ አብያተ ክርስቲያናትን በአንድነት ለማስተሳሰር፣ የወንጌል ስርጭትን ለማጠናከር እና ለሰላም ግንባታ የተለየ ሚና እንደሚጫወቱ ተገልጿል።

ሹመቱ በህብረቱ የቦርድ ዳይሬክተሮች፣ በአፍሪካ አህጉር አስተባባሪዎች እና በቢሾፕ ጄምስ ኦዲሃምቦ ልዋንዴ ሙሉ እምነት የተሰጠ መሆኑ ታውቋል። በዚህም መሠረት ዶ/ር ወንድማገኝ በቀጠናው ያሉ አገራት መካከል የጠነከረ ትብብር በመፍጠር ለቤተክርስቲያን አንድነትና ለህብረተሰብ ሰላም ለመስራት ይጠበቅባቸዋል።

መረጃውን፤ አገልጋይ ካሌብ ለማ አደረሰን

"ይቅርታ እጠይቃለሁ ‼️ " በቅርቡ ከሰዶማውያን ወይም ሰዶማዊነትን ከሚደግፉ ሰዎች እርዳታ መቀበልን በተመለከተ በጻፈውና ከባድ ውዝግብ ባስነሳው ጉዳይ ላይ ይቅርታ ጠይቋል።  (ዶ/ር ተስፋዬ...
05/28/2026

"ይቅርታ እጠይቃለሁ ‼️ "
በቅርቡ ከሰዶማውያን ወይም ሰዶማዊነትን ከሚደግፉ ሰዎች እርዳታ መቀበልን በተመለከተ በጻፈውና ከባድ ውዝግብ ባስነሳው ጉዳይ ላይ ይቅርታ ጠይቋል። (ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ)

ይቅርታ እጠይቃለሁ!
ከ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ
ሰዶማውያን ከሆኑ ወይም በፅንሰ ዐሳብ ደረጃ ሰዶማዊነትን ከሚደግፉ ሰዎች:—
(1) ስጦታዎቻቸውን ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ በድፍን ቅል መቀበል እንችላለን፣
የሚል እምነት ድሮም አልነበረኝም ዛሬም የለኝም።
የእኔ አቋም የነበረው:—
(2) ቢያንስ በንድፈ ዐሳብ ደረጃ፣ ስጦታዎች አስገዳጅ ጫና ካልተደረገባቸው (no hidden obligations) መቀበል እንችላለን የሚል ዐሳብ ነበር።
ብዙ አስተያየት ሰጪዎችና ኂስ አቅራቢዎች ይህን በውል የተረዱልኝ አልመሰለኝም።
አንዳንድ ወንድሞች በፅንሰ ዐሳብ ደረጃ ካልሆነ በቀር፣ ይህ ጫና ያልተደረገበት ስጦታ በምንኖርበት ዓለም እውን ሊሆን እንደማይችል አስረድተውኛል። ስለዚህ በምንኖርበት ዓለም ከሰዶማውያን ወይም ሰዶማዊነትን ከሚደግፉ ሰዎች፣ አንዳችም ስጦታ መቀበል እንደማንችል ግልጽ ሆኖልኛል። ስለዚህ ከዚህ በፊት የነበረው አቋሜ በዚህ አግባብ እንደ ተስተካከለ እንድታውቁት በትልቅ አክብሮት እጠይቃለሁ።
ይህ እንዳለ ሆኖ፣ ይህን ርእሰ ጒዳይ ያነሣሁት፣ ለውይይት በሚል እንጂ የትኛውንም ወገን ለማስደሰትም ሆነ ለማስከፋት አይደለም። ከወገንተኝነት ተነሥቶ ነው፣ የሚሉ አስተያየቶች ስሕተት ናቸው። እንደ እውነቱ ከሆነ የመካነ ኢየሱስ መሪዎችንም ሆነ የመሠረተ ክርስቶስ መሪዎችን አላውቃቸውም። እንወያይበት የሚለውን ጒዳይ ያመጣሁት በፍጹም ቅን ከሆነ ኅሊና በመነጨ መንገድ ነው።
ዘጠና ከመቶ (90%) የሚሆነው የአገልግሎቴ ዕገዛ የሚመጣው ከቤተሰቤ ሲሆን፣ ዐሥር ከመቶ (10%) የሚሆነው ደግሞ ከሁለት ኢትዮጵያውያን አብያተ ክርስቲያናትና አገልግሎቴን ከሚደግፉ ጥቂት ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ነው።
ይህ እንዳለ ሆኖ ርእሰ ጒዳዩን በማንሣቴ ያዘናቹ ወንድሞቼንና እኅቶቼን ይቅርታ እጠይቃለሁ።

"ካውንስሉ ቤተክርስቲያን አይደለም" ዶ/ር ስምዖን ሄሊሶ ‼️ ካውንስል በተመለከተ ካውንስሉ ምንድነው? ስልጣኑስ የት ድረስ ነው? ለሚለው ጥያቄ ቃለ ህይወት በመሪዎቿ በኩል አቋሟን ግልፅ አድ...
05/28/2026

"ካውንስሉ ቤተክርስቲያን አይደለም" ዶ/ር ስምዖን ሄሊሶ ‼️

ካውንስል በተመለከተ ካውንስሉ ምንድነው? ስልጣኑስ የት ድረስ ነው? ለሚለው ጥያቄ ቃለ ህይወት በመሪዎቿ በኩል አቋሟን ግልፅ አድርጋለች።

ዶ/ር ስምዖን የሚከተለውን ብለዋል:-
1, ካውንስሉ የኔትወርክ ድርጅት ነው!
2, ካውንስሉ ቤተክርስቲያን አይደለም!
3, ካውንስሉ ቤተክርስቲያናት ከሌሉ ህልውና የለውም!
4, ካውንስሉ ባይኖርም አብያተክርስቲያናት ግን ይኖራሉ!
5, ካውንስሉ የቤተክርስቲያንን ስራ መስራት የለበትም
6, እስከ አሁን የተሰሩ ስህተቶች (ካውንስሉን በተመለከተ) ይታረማሉ!
7, በመግባባት የማይፈታ ከሆነ (ከካውንስሉ ጋር ያለው ግንኙነት) በህግ የቃለ ህይወትን መብት እናስጠብቃለን!

©️ዶ/ር ስምዖን ሄሊሶ

ዛሬ በሀደሮ አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል አዘጋጅነት በከተማዉ ጎዳናዎች ላይ በአገራዊና አለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ምልጃና ፀሎት ተደርጓል።
05/28/2026

ዛሬ በሀደሮ አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል አዘጋጅነት በከተማዉ ጎዳናዎች ላይ በአገራዊና አለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ምልጃና ፀሎት ተደርጓል።

"Artisan" brand stainless steel glass door lock, typically designed for frameless glass doors. These locks are standard ...
05/28/2026

"Artisan" brand stainless steel glass door lock, typically designed for frameless glass doors.

These locks are standard for tempered glass with a thickness of 10mm to 12mm.
Commonly used for office glass partitions, retail shop storefronts, or residential glass doors.

Built for modern installations, they offer the strength, clean design, and professional look that today’s projects demand.

Need door locks for an upcoming project? Contact us.
📞 +251900830904
📧
🌐 https://artisantrading.my.canva.site/untitled-app




በቻይና ምን ተከሰተ ❗ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት፣ በቻይና ክርስትና ቀስ በቀስ ማደጉን ቀጥሏል። ይህም በመላው ዓለም ያሉ ተመራማሪዎችንና የሃይማኖት ተከታዮችን ትኩረት ስቧል።የታሪክ ግምቶች እን...
05/28/2026

በቻይና ምን ተከሰተ ❗
ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት፣ በቻይና ክርስትና ቀስ በቀስ ማደጉን ቀጥሏል። ይህም በመላው ዓለም ያሉ ተመራማሪዎችንና የሃይማኖት ተከታዮችን ትኩረት ስቧል።
የታሪክ ግምቶች እንደሚያሳዩት፣ በ1949 የነበረው የክርስቲያን ሕዝብ ቁጥር አነስተኛ ነበር። ነገር ግን በሂደት በጣም ጨምሯል።
# # ፈጣን እድገት (ከ1980ዎቹ–2000ዎቹ)
ከባህል አብዮት (Cultural Revolution) በኋላ፣ ክርስትና በፍጥነት ተስፋፍቷል፦

* 10% እድገት፦ ፕሮቴስታንት በየዓመቱ በዚህ መቶኛ ያድግ ነበር።
* ከ60–100+ ሚሊዮን፦ በ2010ዎቹ ውስጥ የአማኞች ቁጥር እዚህ ደርሷል።
* የቤት ውስጥ አብያተ ክርስቲያናት (የቤተሰብ ማኅበራት)፦ ይህ እድገት በብዛት የተከሰተው በሕግ ባልተመዘገቡ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ነበር።

# # ወቅታዊ ሁኔታ እና ትንበያ

* ድብቅ አብያተ ክርስቲያናት፦ በትንንሽ ቡድኖች ስልት መስፋፋታቸውን ቀጥለዋል።
* ትንበያ፦ ቻይና በዓለም ላይ ከፍተኛ የክርስቲያን ሕዝብ ቁጥር ያላት አገር ልትሆን ትችላለች።
* የትውልድ ሁኔታ፦ አዲሱ ትውልድ የሕይወትን ትርጉምና የግል እምነትን በመፈለግ ላይ ይገኛል።
* ግንኙነት፦ አማኞች በግል ግንኙነትና በጋራ እምነት ላይ ተመስርተው አብረው ይሰባሰባሉ።

እግዚአብሔር በሥራ ላይ ነው!
ሃሌ ሉያ እና አሜን! 🥳✝️
ይህ እድገት የሚቀጥልበት መንገድ በአዲሱ ትውልድ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይፈጥራል።
ጋላታ ካራዩ (ምስጋና ለካራዩ)
------------------------------
Galata Karayu

የጉለሌ ቤቴል መካነየሱስ “ለ” መዘምራን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዩቤልዩ በዓል በድምቀት ተከበረበአዲስ አበባ የሚገኘው ጉለሌ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን የ“ለ” መዘምራን ህብረት የተ...
05/28/2026

የጉለሌ ቤቴል መካነየሱስ “ለ” መዘምራን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዩቤልዩ በዓል በድምቀት ተከበረ

በአዲስ አበባ የሚገኘው ጉለሌ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን የ“ለ” መዘምራን ህብረት የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዩቤልዩ በዓል ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።

በበዓሉ ላይ የአዲስ አበባ መካነ ኢየሱስ ሲኖዶስ ፕሬዝደንት ቄስ ፅጌ በረዳ፣ የቤተክርስቲያኗ አገልጋዮች ፣ ከሀገር ውጪና ከሀገር ውስጥ የመጡ የቀድሞ የመዘምራኑ አባላት፣ የማህበረ ምዕመኗ አባላት እና እንግዶች ተገኝተዋል።

የመዘምራኑ መስራች ቄስ በላይነህ አለማየሁ የኳየሩን የ50 ዓመት ጉዞ፣ የስደት ዘመን ታሪክና የአገልግሎት ትውስታዎችን አካፍለዋል። እንዲሁም ቄስ አስቻለው ሲማ መንፈሳዊ መልዕክት ሲያቀርቡ፣ ዶክተር ፈይሳ ረጋሳ እና ቄስ ፅጌ በረዳ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የ“ለ” መዘምራን በ1967 ዓ.ም በጉለሌ መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተመሰረተ ሲሆን፣ ለ50 ዓመታት በዝማሬ፣ በጸሎት፣ በምክርና በቅስና አገልግሎት በታማኝነት ሲያገለግል ቆይቷል። በዓሉ ላይ ከመስራቱ ጀምሮ እስከዛሬ በአገልግሎት የቆዩ አባላት በልዩ ዝማሬ አገልግለዋል።

በመርሐ ግብሩ ውስጥ ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ አባላት የዕውቅናና የካባ ሽልማት የተሰጠ ሲሆን፣ በሕይወት ላልኖሩ የቀድሞ አባላት ቤተሰቦችም የማስታወሻ ዕውቅና ተበርክቶላቸዋል።

በመጨረሻም በቄስ እስክንድር ፍሪሳ አማካኝነት የስጦታ ፕሮግራም ተካሂዶ፣ የኬክ ቆረሳ ሥነ-ሥርዓት ተከናውኗል። የበዓሉ ፕሮግራምም በቄስ ተስፋሁን መከተ ቡራኬ ተጠናቋል።

 !!ፍትህ ለጉራጌ ተወላጅ ወንጌል አማኞችወንጀለኛው ዳኛ ሆኗልእኛ የጉራጌ ተወላጆች የሆንን የወንጌል አማኞች በእ/ኤ/ሙገር ወረዳ ሚቄ ከተማ በወንጌል አማኞች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ እን...
05/27/2026

!!
ፍትህ ለጉራጌ ተወላጅ ወንጌል አማኞች

ወንጀለኛው ዳኛ ሆኗል

እኛ የጉራጌ ተወላጆች የሆንን የወንጌል አማኞች በእ/ኤ/ሙገር ወረዳ ሚቄ ከተማ በወንጌል አማኞች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ እንቃወማለን፣በስልጣን ላይ ያሉ የሌላ ዕምነት ተከታዮች በግል ሃይማኖቱን በመጥላት ፍትሀዊ ያልሆነ ድርጊት እየፈፀሙ ነው።

ይሄ ከስር የምትመለከቱትን የሶሳል ሚዲያ ፅሁፍ ሼር አድርገሀል ጥቅስ ፅፈሃል በሚል የሚቄ ቃለህይወት ቤተክርስቲያን አባል የሆነውን ይርጋለም የተባለ ወጣት ቤቱ ድረስ በመሄድ ጊቢውን በመስበር ሚስቱ እና ልጁ ሳይቀር የደበደቡ ወጣቶች ለፍትህ መቅረብ ሲኖርባለው ለእነርሱ ነፃነትን ሰጥቶ ፖሊስ የተደበደበውን የወንጌል አማኝ ጥፋተኛ በማድረግ እስር ቤት አቆይተውት እለተ ማክሰኞ 18/9/2018 ጥፋተኛ ነህ ሲሉ ወስነዉበት ዳኛው በዐል ላይ ነው በሚል ለቅጣት ውሳኔ ለ26/9/2018 ቀጥረውታል ከታች የቅጣት አስተያየታቸዉን አያይዘነዋል።

በስፍራው በተደጋጋሚ የወንጌል አማኙን በሚጠሉ እና በሚያሳድዱ የመንግስት ሹመኞች ወንጌል ይሰደዳል!! ቤተክርስቲያን ትበደላለች እንዲህ አይነት ፍትህ እንኳን አይን ባፈጠጠ መልኩ ይካዳል፣ስንደበደብ ፖሊስ እንኳን እንከለከላለን የጉራጌ ወንጌል አማኞች ሼር በማድረግ አድርሱልን የሚመለከታቹ የመንግስት ሹመኞች ፍትህ ስጡን ስንል እንጣራለን

እንኳን ለ 19ኛ ዓመት የጋብቻ በዓላችሁ አደረሳችሁ 🔥
05/27/2026

እንኳን ለ 19ኛ ዓመት የጋብቻ በዓላችሁ አደረሳችሁ 🔥

 #የዘማሪ ሊሊ እናት የወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ አጭር የህይወት ታሪክ* የሕይወት ታሪክ ዝግጅት ፦ ዕዝራ እጅጉ*ቀብራቸው በአሜሪካ ከደቂቃዎች በኃላ ይፈፀማል    ክብርት ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎ...
05/27/2026

#የዘማሪ ሊሊ እናት የወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ አጭር የህይወት ታሪክ

* የሕይወት ታሪክ ዝግጅት ፦ ዕዝራ እጅጉ

*ቀብራቸው በአሜሪካ ከደቂቃዎች በኃላ ይፈፀማል



ክብርት ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ ተድላ ሚያዝያ 9 ቀን 1944 ዓም በደሴ ከተማ ከአባታቸው ከፊታውራሪ ጳውሎስ ተድላ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ታእከማሪያም ስንቄ
ተወለዱ::ወሮ ቅድስት አብዛኛውን የልጅነት ጊዜያቸውን በአዲስ አበባ ከተማ በወላጅ አባታቸው በልዩ እንክብካቤ ያደጉና በአብሮ አደጎቻቸውም ዘንድ እጅግ የተከበሩና የተወደዱ ልጅ ነበሩ::

ወይዘሮ ቅድስት የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አሜሪካን ሚሽን ተብሎ በሚጠራው ት/ቤት ቀጥሎም በካቴድራል ልደታ ማርያም ትምህርት ቤት ተከታትለዋል:: እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቅድስት ማርያም ወይም St Mary's secondary school አጠናቀዋል። ከዚያም በመቀጠል
በአዲስ አበባ ንግድ ስራ ኮሌጅ በመግባት ከፍተኛ ትምህርት ጊዜያቸውን በብቃት አጠናቀው በ1965 ዓም ተመርቀዋል:: ከዚያም የስራ ዘመናቸውን በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የበጀትና የፋይናንስ አናሊስት ባለሙያ ሆነው በመቀጠር ሙያዊ አበርክቶታቸውን ሰጥተዋል:: በዚሁምመስሪያ ቤት ለ25 አመታት በትጋትና በታማኝነት አገልግለዋል::

ወ/ሮ ቅድስት ጵውሎስ በዚህ ሁሉ የህይወት መንገዳቸው በወጥነት በመልካም ባህርያቸው በተግባቢነትና እና በማህበራዊ ክህሎታቸውው እጅግ የተመሰከረላቸው ሴት ነበሩ::

ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ ከትምህርት ቤት አንስቶ ከተዋወቁት የፍቅር አጋራቸው ከአቶ ጥላሁን በሻህ ጋር በ1963 ዓም በጋብቻ ተጣምረው ባሳለፉት የፍቅርና የትዳር ህይወታቸው የ5 ልጆች እናትና የ15 የልጅ ልጆች አያት ለመሆን በቅተዋል::

ወ/ሮ ቅድስት ጳውሎስ በቤተሰባዊ ፍቅራቸው እጅግ የሚታወቁና የተመሰከረላቸው እንዲሁም ለአቋማቸው ሁልጊዜም ፅኑ የሆኑ ሴት ነበሩ:: በእግዚአብሔር ብዙ ቸርነትና በተሰጣቸው ልዮ የእናትነት ፀጋ ልጆቻቸውን በላቀ ስነ ምግባር አሳድገው ለታላቅ ቁምነገርና ለብዙ ፍሬ አብቅተዋል:: በዚህም በመልካም ስነ ምግባር ልጆችን የማሳደግ ተምሳሌትነታቸው በብዙ እናቶች መካከል እንደ አርአያ እንዲታዮ አድርጉዋአቸዋል::

ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ በእርግጥም Selfless በሆነ የመስዋዕትነት ህይወት ቤተሰባችውን እየተንከባከቡ የፍቅር ሰውነታቸውን በተግባር ያስመሰከሩ ታላቅ ሴት ነበሩ:: ከወጣትነት ዕድሜ ጅምሮ የራሳቸውን ምቾትና ድሎት ወደ ጎን አድርገው ለልጆቻቸውና እና ለትዳራቸው ተሰጥተው የኖሩ ድንቅ እናት ነበሩ::

ዛሬ በህይወት የሌሉት ባለቤታቸው አቶ ጥላሁን በሻህንም ሕይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ ለትዳር አጋር የሚገባውን ግሩም እንክብካቤ በመስጠት የባለቤትነት ተግባራቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል::

እንዲሁም በመኖሪያ አካባቢያቸውም ሆነ በሥራ ቦታቸው የተቸገረን ለመርዳት ወይዘሮ ቅድስትን የሚቀማቸው አልነበረም።
ወ/ሮ ቅድስት ባላቸው መልካም ማህበራዊ ግንኙነት ብዙ መልካም ወዳጆች ያፈሩና እንዲሁም ትንሽ ትልቅ ሳይሉ ሁሉንም በማቅረብ አለኝታነታቸውን ያሳዮ ነበር::
ይህም ፈሪሀ እግዚአብሔር ያደረባቸው ደግ ርህሩህና መንፈሳዊ ሴት መሆኗቸውን በተግባር የገለፀ የስብዕናቸው ማሳያ ነበር።

ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ አብረዋቸው በኖሩ የቅርብ ዘመዶቻቸውና ጉዋደኞቻቸው በብዙ መልክ ይገለፁ ነበር:: ከነዚህም የፍቅር ስሞች መካከል አባይ ቅድስት፣ ቅድስትዬ ሆዴ፣ ኪዲ፣ ኪዲዬ ተብለው እጅግ ባማረ የመወደድና እና የክብር ስም ይጠሩ ነበር ። ከሁሉ ሚገርመው የልጆቻቸው ጉዋደኞች ሳይቀር የሚጠሩአቸው ኪዲዬ በሚል የቁልምጫ ስም እንደነበር በፅኑ የሚታወስ ነው::

ወ/ሮ ቅድስትን ወዳጅ ዘመድና ጉዋደኞቻቸው በታማኝነታቸውና በሰው አክባሪነታቸው ሁልጊዜ ያስታውሱአቸዋል::
የራሳችውንም ሆነ የሌላውን ሰው ክብር ጠባቂ ከመሆን ብሻገር ሰውን በማንነቱ ብቻ የሚወዱ ግሩም ሴት ነበሩ:: ወሮ ቅድስት ለንፁህ ወዳጅነት ራሳቸውን የሰጡ የብዙዎች እህትና ወዳጅ በቤተሰባችውም ዘንድ ተናፋቂ እመቤት ሆነው ይታወሳሱ:::

ወ/ሮ ቅድስት ዛሬ በስጋ ቢለዮንም በብዙ መልካም ስራቸውና ትዝታቸው በልጅቻቸውና በዘመዶቻቸው እንዲሁም በወዳጆቻቸው ልቦና ውስጥ ሁልጊዜ ሲታሰቡ ይኖራሉ::

ወ/ሮ ቅድስት ባደረባቸው ህመም ምክንያት በቤተሰባቸው ከፍተኛ እንክብካቤ ሲደረግላቸውና እንዲሁም አስፈላጊው የህክምና እርዳታ ሲታገዙ ኖረው በመጨረሻም ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል::

"ሰው በልቡ አምኖ ይፀድቃል በአፉም መስክሮ ይድናል" ተብሎ እንደተፃፈው የእግዚአብሔር ቃል በማያጠራጥር መልኩ በታመኑ ምስክሮች ፊት ጌታቸውን መስክረው ልባዊ የሆነ እምነታቸውን አፅንተው በመጨረሻው ሰዓት ወደ ጌታቸው ተሰብስበዋል::

ወይዘሮ ቅድስት ዛሬ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓም ልጆቻቸው የቅርብ ወዳጆቻቸውና ዘመዶቻቸው በተገኙበት ስርዓተ ቀብራቸው ይፈፀማል::

ስለሁሉም የዘመን ባለቤት የሆነውን ታማኙን ጌታ ታላቁን ልዑል እግዚአብሔርን እጅግ አድርገን እናመሰግናለን:: ስለ ሁሉ ለእግዚአብሔር ለአምላካችን ክብርና ምስጋና ይሁንለት!!

Address

1701 Liberty Lane, Blacksburg
Virginia Beach, VA
24060

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AmlekoTube - አምልኮቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to AmlekoTube - አምልኮቲዩብ:

Share