05/28/2026
በህንድ በክርስቲያኖች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ
በህንድ በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ጥቃት፣ ማስፈራራትና መድሎ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን የህንድ ወንጌላዊ ፌሎውሺፕ የሃይማኖት ነፃነት ኮሚሽን (EFIRLC) ባወጣው አመታዊ ሪፖርት ገልጿል።
ሪፖርቱ በ2025 ብቻ 747 የጥቃትና የጥላቻ ክስተቶች መመዝገባቸውን ያሳያል። ይህም በ2024 ከተመዘገቡት 640 ጉዳዮች በላይ ሲሆን፣ በ2014 ከነበሩት 147 ጉዳዮች ጋር ሲነጻጸር ከአምስት እጥፍ በላይ ጭማሪ መኖሩን ያመለክታል።
ኮሚሽኑ በዓመቱ 915 በላይ ሪፖርቶችን ቢቀበልም፣ 747ቱ ብቻ ከበርካታ ገለልተኛ ምንጮች በተደረገ ጥብቅ ማረጋገጫ የተረጋገጡ መሆናቸው ተገልጿል።
የህንድ ወንጌላዊ ፌሎውሺፕ ዋና ጸሃፊ ቄስ ቪጃዬሽ ላል፣ “የሕሊና ነፃነትና የሕግ እኩልነት ለሁሉም ዜጎች መከበሩን ማረጋገጥ አስፈላጊ ነው” ሲሉ ገልጸዋል።
ሪፖርቱ በህንድ ያሉ አናሳ ክርስቲያኖች በቀጣይነት ከግፍ፣ ከጥቃትና ከማስፈራራት ጋር እየተጋፈጡ መሆናቸውን በግልጽ አመላክቷል።
በዳንኤል አንተነህ
ዘገባው፤ የክርስቲያን ክርስቲያን ኮንሰርን ነው።