Christ Embassy DMV Amharic Service

Christ Embassy DMV Amharic Service Believers LoveWorld Incorporated, (a.k.a Christ Embassy) is a global ministry with a vision of taking God’s divine presence to the nations of the world

05/31/2026

የእሁድ 05/31/26 ቀጥታ ስርጭት ክሪይሰት ኤምባሲ ዲ. ኤም. ቪ. የአማሪኛ ፕሮግራም

05/24/2026

የእሁድ 05/17/26 ቀጥታ ስርጭት ክሪይሰት ኤምባሲ ዲ. ኤም. ቪ. የአማሪኛ ፕሮግራም

05/10/2026

የእሁድ 05/15/26 ቀጥታ ስርጭት ክሪይሰት ኤምባሲ ዲ. ኤም. ቪ. የአማሪኛ ፕሮግራም

05/09/2026

የእሁድ 05/03/26 ቀጥታ ስርጭት ክሪይሰት ኤምባሲ ዲ. ኤም. ቪ. የአማሪኛ ፕሮግራም

01/02/2026

የክርስቶስ የማዳን መልዕክት

📖 ════════
ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል። (ማቴዎስ 24:14) ።

ፓስተር ክሪስ
━━━━━━━━━
የክርስቶስ የማዳን መልዕክት በዓለም ላይ ላለው ጨለማና ግራ መጋባት የእግዚአብሔር መልስ ነው። ጌታ ዳግመኛ ከመምጣቱ በፊት ሁሉም ሰው ይሄን ወንጌል እንዲሰማና እንዲቀበል ማድረግ የእኛ ኃላፊነት ነው። ጌታ ወንጌል በዓለም ሁሉ ለምስክርነት እንደሚሰበክ ተናግሯል፤ ከዚያም መጨረሻው ይመጣል።

ይህ ማለት የጊዜው ቀመር የተዘጋጀው ቤተክርስቲያን ሥራውን እንድትጨርስ ታስቦ ነው። እናንተ ዘመኑን ለመጨረስ ከተመረጠው ትውልድ አካል ናችሁ። ዝም ብላችሁ ሌሎች ሲሰሩ አትመልከቱ። በምልጃ ጸሎት፣ ወንጌልን ለመስበክ በሚደረግ እንቅስቃሴ፣ በገንዘብ አብሮ ሰራተኛ በመሆን እና በድፍረት በመመስከር በንቃት ተሳተፉ።

የእግዚአብሔር መንፈስ ወደ ዓለማችሁን እንድትደርሱ መሳሪያውን አስታጥቋችኃል። 2ኛ ቆሮንቶስ 3:5-6 እንዲህ ይላል "ብቃታችን ከእግዚአብሔር ነው እንጂ፥ በገዛ እጃችን እንደሚሆን አንዳችን እንኳ ልናስብ ራሳችን የበቃን አይደለንም፤ እርሱም ደግሞ በመንፈስ እንጂ በፊደል ለማይሆን ለአዲስ ኪዳን አገልጋዮች እንሆን ዘንድ አበቃን . . ." የሐዋርያት ሥራ 1:8 እንዲህ ይላል "ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ።"

አስታውሱ፥ ተልዕኮው ይቀጥላል። የመንፈስ ትዕዛዝ እና አስቸኳይነት ግልጽ ነው፤ እግዚአብሔር ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ፥ አንድ አምላክ ብቻ እንዳለን እና በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ራሱን ለሁሉ ቤዛ አድርጎ የሰጠው ክርስቶስ ኢየሱስ እንደሆነ እንዲያውቁ ይፈልጋል። (1ኛ ጢሞቴዎስ 2:5-6)።

ለችግር ሁሉ መልስ እርሱ ነው፣ በዓለም ውስጥ ላለ ህመም፣ መከራ፣ መበስበስ እና በሽታ መፍትሔ እርሱ ነው። እርሱ ሕይወት ሰጪ ነው። እርሱ እውነተኛው አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው "የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው" (1ኛ ዮሐንስ 5:20) ።

ጸሎት / የእምነት አዋጅ
━━━━━━━━━
ውድ አባት ሆይ፣ የወንጌልን ኃላፊነት ስለሰጠኸኝ አመሰግናለሁ። የክርስቶስን ፍቅር፣ ኃይልና ጽድቅ ለዓለሜ ለማድረስ በመንፈስህ ኃይል አግኝቻለሁ። በእኛ በኩል ጸጋህና እውነትህ በሁሉም ሥፍራ ይገለጣል እንዲሁም በዓለም ሁሉ ያሸንፋል። በኢየሱስ ስም። አሜን።

ለተጨማሪ ጥናት:
የማርቆስ ወንጌል 16:15;
ሮሜ 1:16;
የማቴዎስ ወንጌል 28:19-20
━━━━━//━━━━━
RHAPSODY OF REALITIES(Amharic)
(ዓርብ - ታህሳስ 24 - 2018)

እግዚአብሔርን በቅንነት እና በደስታ አገልግሉ📖 ════════ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁል...
12/07/2025

እግዚአብሔርን በቅንነት እና በደስታ አገልግሉ

📖 ════════
ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ (1ኛ ቆሮንቶስ 15:58) ።

ፓስተር ክሪስ
━━━━━━━━━
የክርስትና ሕይወታችን ጨዋታ አይደለም፤ ዋና ነገር ነው እንዲሁም በመንፈሳዊ መርሆች ላይ የተመሰረተ ነው። እየኖርን ያለነው መንፈሳዊ ሕይወት ነው። የቤተክርስቲያን ንጥቀት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዛሬ ቀርቧል። ስለዚህ፣ በየቀኑ፣ ንጹህ አእምሮአችሁን ማንቃት፣ እራሳችሁን መገምገም እና የክርስትና ሕይወታችሁ ከቃሉ ጋር የሚስማማ መሆኑን ማረጋገጥ አለባችሁ።

ትኩረታችሁን በቃሉ ላይ አድርጉ። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል ". . . በምትሄድበትም ሁሉ እንዲከናወንልህ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አትበል" (ኢያሱ 1:7) ። ቃሉ በአእምሮአችሁ እና በመንፈሳችሁ ላይ፣ በሃሳባችሁ እና በአመለካከታችሁ ላይ እንዲገዛ አድርጉ። መጽሐፍ ቅዱስ ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው ይላል (መዝሙር 119:105) ። በጨለማ ጎዳና ስትጓዙ፣ መንገዱ እንዲታያችሁ መብራት ትጠቀማላችሁ። ያም ቃሉ ነው፤ የሕይወትን መንገድ ያሳያችኋል እናም በጽድቅ መንገድ ይመራችኋል።

2ኛ ተሰሎንቄ 2፡3 " . . . ክህደቱ አስቀድሞ ሳይመጣና የዓመፅ ሰው እርሱም የጥፋት ልጅ ሳይገለጥ፥ አይደርስምና" በማለት ያስጠነቅቀናል። ቀጥሎም በማቴዎስ 24:12 ጌታ እንዲህ አለ "ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች።” ስለዚህ፣ ለጌታ ባላችሁ ፍቅር እንደተቀጣጠላችሁ ቆዩ። ለመንፈሳዊ ነገሮች ያላችሁን እምነት እና ቅንዓት ምንም ነገር እንዲቀንስባችሁ አትፍቀዱ።

ጌታን የእውነት በሚወዱት፥ በትክክል እርሱን በሚያገለግሉት እና በማያገለግሉት መካካል ልዩነት ሊኖር ይገባል። እራሳችሁን መመልከት አለባችሁ። ልባችሁን መርምሩ። መንፈሳችሁ ጠብቁ። በዮሐንስ 13:35 "እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ" ብሎአልና በፍቅር ተመላለሱ።

የክርስትና ሕይወት ጉዞ ነው። እያንዳንዱ ቀን በፍቅር ለመመላለስ አዲስ ቀን ነው። እያንዳንዱ ቀን ጌታን በደስታ ለማገልገል አዲስ ቀን ነው። እርሱ ብርሃን እንደሆነ በብርሃን ለመመላለስ እያንዳንዱ ቀን አዲስ ቀን ነው (1ኛ ዮሐንስ 1፡7)። እያንዳንዱ ቀን የጽድቅ ፍሬ ለማፍራት እና የጽድቅን ሥራ ለመግለጥ አዲስ ቀን ነው። ስለዚህ ጌታን በጽናት እና በደስታ በማገልገል እያንዳንዱን ቀን ውጤታማ አድርጉ።

ጸሎት / የእምነት አዋጅ
━━━━━━━━━
ውድ አባት ሆይ፣ አንተን የማወቅ እና የማገልገ እንዲሁም በአንተ ስም ስለመጠራት እድል እና በረከት አመሰግንሃለሁ። በጌታ ሥራ ሁልጊዜ የበረታሁ፣ የተቀጣጠልኩ እና የማልነቃነቅ ሆኔ እቆማለሁ። በደስታ ልብ፣ በመሰጠት እና በዓላማ ሳገለግልህ ለአንተ ያለኝ ፍቅር ከመቼውም ጊዜ በላይ እየጨመረ ነው። ክብርህን በመግለጥ እና ጽድቅህን በማሳየት በእነዚህ የመጨረሻ ቀናት የበለጠ አበራለሁ። በኢየሱስ ስም። አሜን።

ለተጨማሪ ጥናት:
ዕብራውያን 12:1-2;
ዕብራውያን 6:10-12;
ገላትያ 6:9
━━━━━//━━━━━
RHAPSODY OF REALITIES(Amharic)
(እሁድ - ህዳር 28 - 2018)

Dear Christ Embassy DMV Family, Wishing you a blessed and joyful Thanksgiving. Today, we express gratitude to God for yo...
11/27/2025

Dear Christ Embassy DMV Family,

Wishing you a blessed and joyful Thanksgiving. Today, we express gratitude to God for you, for the gift of family, and for the privilege of fellowship in Christ. May your homes be filled with His peace, your hearts with gratitude, and your lives with testimonies of increase and favor.

Happy Thanksgiving from Christ Embassy DMV.

ወደ ደጆቹ በውዳሴ፥ ወደ አደባባዮቹም በምስጋና ግቡ፥ አመስግኑት፥ ስሙንም ባርኩ፥” ‭‭መዝሙረ ዳዊት‬ ‭100‬:‭4‬ መቅካእኤ‬

Dívíɳҽ 卄ealtɧ CσnfҽssiσɳsI refuse to fret about my health or anything else because the Lord has perfected all that conce...
11/07/2025

Dívíɳҽ 卄ealtɧ Cσnfҽssiσɳs

I refuse to fret about my health or anything else because the Lord has perfected all that concerns me. My body cannot be overtaken by sickness, disease, or infirmity, for it is God’s sanctuary. I glorify God in my body, and it functions perfectly at all times by the Spirit.

I'm Alive!

Follow us Christ Embassy

!!

ታላቅ የፈዉስ የቀጥታ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል በምንም አይነት ህመም ውስጥ ላሉ ሁሉ ይፀለያልሁላችሁም ተጋብዛችሗል ለመመዝገብ ከታች ያለዉን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇👇👇👇👇👇**HSLHS Zonal Regis...
07/15/2023

ታላቅ የፈዉስ የቀጥታ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል በምንም አይነት ህመም ውስጥ ላሉ ሁሉ ይፀለያል
ሁላችሁም ተጋብዛችሗል
ለመመዝገብ ከታች ያለዉን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇👇👇👇👇👇

**HSLHS Zonal Registration Link July 2023 *
http://healingstreams.tv/reg/US1Z1
Glory to God! Healing Streams Live Healing Services with Pastor Chris will return this July; From Friday 28 to Sunday 30 July 2023. Registration is now open!

Address

8777 Georgia Avenue
Silver Spring, MD
20910

Opening Hours

Wednesday 10am - 1:30pm
8pm - 9:30pm
Sunday 10am - 1:30pm
8pm - 9:30pm

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Christ Embassy DMV Amharic Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Christ Embassy DMV Amharic Service:

Share