Gospel Mission worldwide Church / የወንጌል ተልዕኮ ቤ/ን

Gospel Mission worldwide Church / የወንጌል ተልዕኮ ቤ/ን ወንጌል ይሰበካል፣ለበሽተኞች ይፀለያል፣ሰዎች ከአጋንት እስራት ይፈታሉ፣በመንፈስ ቅዱስም ይሞላሉ፤
ለእግዚአብሔር የሚሳነውነገር አለን ? መታቹ እዩ።

08/25/2024

የሐሰተኛ ነብይና የሳተ ህዝብ ሁለቱ
መገለጫዎች
1, የሐሰተኛ ነብያት መገለጫ
ማስፈራራት ሲሆን
2, የሳተ ህዝብ መገለጫ
መፍራት ነው ።

ምሳሌ 29÷25 ሰውን መፍራት ወጥመድ ያመጣል፤ በእግዚአብሔር የሚታመን ግን እርሱ ይጠበቃል።

25 The fear of people becomes a snare, but whoever trusts in the Lord will be set on high.

07/20/2024
Justice for Kurifti oromia Ethiopia Kal hiwot church ዛሬ ይሄንን ጉዳይ ዝም ብንል ቀድሞ እንደተደረገብን አድሎ በየሰፈሩ በሚነሱ ወንጌል ጠል ባለ ስልጣኖች እጅ...
07/20/2024

Justice for Kurifti oromia Ethiopia Kal hiwot church

ዛሬ ይሄንን ጉዳይ ዝም ብንል ቀድሞ እንደተደረገብን
አድሎ በየሰፈሩ በሚነሱ ወንጌል ጠል ባለ ስልጣኖች እጅ ትውልዱን መጣል ነውና

Never finished until we win !!

11/20/2023

የዛሬ 28 ዓመት 1987 በኢትዮጵያ ገና ጨቅላ እድሜ ሳለው ማለቴ እውነትንና ሐሰትን መለየት ባልጀመርኩበ፣ ጊዜ ነበር ትዝ የሚለኝኝኝ
የሰፈሬ ልጆች ሲፈልጉ ጥምቀት ባህር
ሲፈልጉ ኢድ አልፈጥር ሲከትቡኝ
አንዳንድ የመንደሬ ሃብታሞች እንደጋርድ የሚጠቀሙብኝ ፣
ብቻ ምን አለፋችሁ ባጭሩ ሰውም ሰይጣንም ሚዘውሩኝ እውነቱም ሐሰቱም የተደባለቀብኝ የሐይማኖቶች ብዛት ግራ አጋብቶኝ ፣ የድህነት ኑሮ አስጠልቶኝ ዋሽቼም ቀምቼም በባሌም ሆነ በቦሌ
ሃብታም ለመሆን "ወይም ፋሻ ወይም ባሻ" ብዬ የተነሳሁበት ወቅት ነበር
በደቡብ ክልል ውቢቷ አዋሳ በቀድሞ አጠራሩ አብዮት አደባባይ The freedom of Human bing ነፃ የሚያወጣውን የወንጌል ምስራች ይዞ ከተፍ ያለው ፤ ወንጌላዊ ሬንሃርድ ቦንኪ (ጀርመናዊ)
በጀርመን ሃገር የተወለደ ከአንደበቱ እንደሰማነው
በልጅነቱ ለአፍሪካ እግዚአብሔር ወንጌልን እንዲሰብክ እንደጠራው ይናገራል ። ለወላጅ አባቱ ምን እንደሚያስብ ሲነግረው ገንዘብ የለንም ይሄ እንዴት ይሆናል እንዳለውና እግዚአብሔር ያዘጋጃል ብለው አብረው መፀለይ እንደጀመሩም ይናገራል
ወንጌላዊ ሬን ሃርድ ቦንኪ
ተልኮውን ከፈጣሪ ከተቀበለ ቦኃላ በየሰፈሩ እየዞረ ከጓደኞቹ ጋር ጠጠር መጫወቱን ያቆማልና ጓደኞቹ ቦንኪ ና ጠጠር እንጫወት ሲሉት የመለሰው መልስ ለሁላችንም ጠቃሚ ስለመሰለኝ ላቅርበው
" ተራራን እንድገፋ እግዚአብሔር ጠርቶኝ በጠጠር
አልጫወትም"
የሚለው አባባል ጠቅሞኛል።

ጀርመናዊው ወንጌላዊ ሲነሳ የደቡብ አብያተክርስቲያናትና የአጥቢያ መሪዎች አይረሱኝም
ፓ/ር ተሰማ ሎዴቦ
ፓ/ር ጌቱ አያሌው
ፓ/ር ተስፋዬ ጋቢሶ
ፓ/ር የሸዋ ሉል
ፓ/ር አባባ ሚልክያስ
ፓ/ር አባባ ሻኛ
ፓ/ር ተስፋዬ ቃሚሶ
ስለነ ፓስተር ኤልያስ ኮላቶና ሌሎችም ወንጌላውያን፣አስተማሪዎች አሁንም ጌታን በቅንነት ስለሚያገለግሉቱ እንዳልዘረዝር ጊዜ የለኝም።
ትዝ የሚለኝ ወንጌላዊ ቦንኪን የያዘች አውሮፕላን
አዋሳ አውሮፕላን ሜድ ስትደርስ ሰዎች ነጭ ልብስ ለብሰው በአንድነት አየር ማረፊያው እስኪሞላ ከበው የምስራቹን ወንጌል ሰባኪ በቅንነት እንደተቀበሉት ትዝ ይለኛል።

ማስገንዘቢያ
አሁን አንዳንዶች ሰባኪ ስለሆኩኝ ካልሰገዳቹልኝ
ገንዘብ ካልሰጣቹኝ ፣ V8 ካልገዛቹልኝ የሚሉ ኢየሱስን ሸፍነው ዓለምን ወደው ጌታን የሚያገለግሉ የሚመስሉትን ማለቴ አይደለም።
ወንጌላዊ ቦንኪ ኢየሱስን ሰብኮ እስከዛሬ ሊደበዝዝ በማይችል ሁኔታ በልቤ ላይ ኢየሱስን እንደሳለው ህያው ምስክር ነኝ።

ፕሮግራሙ ከሰኞ ጀምሮ ሙሉውን ሳምንት ባልሳሳት ከ9-3 ምሽት ድረስ ይቆይ ነበር ሰዎች ግጥም ብለው ይሞሉም ነበር በጊዜው እኔ ልጅ ስለነበርኩኝ ተሹለክልኬ ፊት አከባቢ መሬት ላይ ተቀምጬ እሰማም ነበር

የማልረሳው በአደባባዩ አከባቢ የአዋሳ ገብርኤል ቤ/ን ነበረና ልክ የአደባባዩ ኮንፍረንስ ሲጀመር የገብርኤሉም ድምፅ ማጉያ ይከፈት ነበርና መናፍቃኖች ጋር አትሂዱ ይባል ነበር
እኔ ግን ሁሉም ክርስቲያን ስለሚመስለኝ ልብም አላልኩም በጊዜው ማስታውሰው የማቃቸው ዲያቆናት ወደ አደባባይ እየገቡ የመናፍቃን ጉባኤ ነው ብለው ብዙዎችን ይከራከሩ እንደነበር አስታውሳለው።

እኔ ግን ሁሉም ጋር ዝም ብዬ እሄድ ስለነበር ልዩነት
አይታየኝም ነበር አንድ ጌታ የሁሉ ጌታ ይመስለኝ ነበር ግን የዲያቆናቱና የቄሶቹ ወከባ ፕሮግራም እንዳይደረግ የሚያደርጉት ግብግብ እኔንም እውነትን እንድመረምር ለህይወቴ ዋጋ ሰጥቼ ሐይማኖት ላይ ሳይሆን አዳኙ ኢየሱስ ላይ ልቤን እንድጥል አድርጎኛልና።

የገብሬሉ ድምፅ ማጉያ በጣም ሃይለኛ ለአከባቢው በቂ የሆነ ቢሆንም በሚበልጠው የአደባባዩ ድምፅ ማጉያ መዋጡን ተመልክቻለው ። ስፒከሩ ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ ድምፅ ማሰማት የሚችል ከተማውና ዙርያውን ገጠራማ አከባቢውን ሚያጠቃልል እንደነበር ይነርለት ነበር ።
ብዙዎች ወንጌልን ሰሙ እግዚአብሄርም አብሮ ይሰራ ነበርና ከበሽታ ፣ ከውልቸር ፣ ከአጋንት እስራት ነፃ
ይወጡ ነበር። ብዙ በጥንቆ አሰራር የበለፀጉ እጃቸውን ለጌታ ሰጡ ባለቤቴ የባለቤቴም ቤተሰቦች የዚይን ጊዜ ነበር ወደ ጌታ መንግስት የተቀላቀሉት።

የወንጌላዊው ቦንኬ የአፍሪካ አገልግሎቱ ቢቀጥልም
ከአዋሳ ኢትዮጵያ ሲስናበተን ግን በምድር ካልተገናኘን በሰማይ እንገናኛለን የሚል መሰናበቻ ንግግሩ ብዙዎቻችንን ያስለቀሰ እንደነበር ትዝ ይለኛል።
ሁሉም አልፎ ከብዙ አመታት ቦኋላ ወደ አሜሪካን አገር ሚኒሶታ ግዛት ለአገልግሎት እንደመጣ ሰማሁኝና ማግኘት አለብኝ ብዬ በተጣበበ ጊዜ አገልግሎቱን ተካፍዬ ነበር።
በወቅቱ የነበርንበት ጉባኤ ብዙ ነጮች ያሉበት ነበረና በአገልግሎቱ መሃል "ይሄን ስብከት አፍሪካ ሰብኬ ቢሆን ስንት እልልታ፡ ስንት ፉጨት ፡ጭብጨባ ብዙ ነፍሳትም ወደጌታ በተጨመሩ ነበር" ብሎ በተናገረበት ጊዜ ህዝቡ በዕባ ከወንበራቸው ተነስተውና መሬት ወድቀው ጌታን እንዳከበሩ የቅርብ ዓመታት ትዝ ታዬ ነውና ። አሁን የወንጌል ሰባኪው ወንጌላዊ ሬንሃርድ ቦንኬ ወዳገለገለው ጌታ የመሰብሰቡን ዜና ስሰማ እንዲህ አልኩኝ ጀግንነት በምድር ላይ ይሄ ነው።
አንባቢዎቼ
ወንጌል ዱላ ቅብብሎሽ ስለሆነ የምታደርጉትን በማስተዋል አድርጉት ምክሬ ነው።
ለማሳጠር ያህል
ይሄ የእግዚአብሔር ሰው የመዳንን ወንጌል በሰበከበት ወቅት የአዋሳ ከተማ ጣኦቶቿን አራግፋ በእድገት ጎዳና የገባችውና በኢትዮጵያ የክልል ከተሞች አደረጃጀት የደቡብ ክልል በሚል መጠሪያ የ56 ብሄረሰብ ከተማ ሆና የመጀመሪያውን ሽልማት ማግኘት የጀመረችው። አዋሳ የተወለድኩባት አባቴ ጫካዋን መንጥሮ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር ለሚቀጥለው ትውልድ ያሸጋገሯት የሁላችን ከተማ ወንጌል በሰሙና ባመኑ ህዝቦች ተመስርታ ወንጌልን ረስተው ሰውን አባረው ብቻቸውን ያለጌታ ለመንገስ ባሰቡ ካድሬዎች ከእድገቷ እያሻቀበች ያለች ዕምብርቴ የተቀበረባት ከተማ ገና የሚነሱ ለኢትዮጵያ እድገት እንኳ ምክንያት የሚሆኑ ካንቺ ይወጣሉና አዋሳ የግዚአብሄር ከተማ ተብለሽ እንደገና ትጠሪያለሽ !!!

ይቅርታ እምባቢዎቼ emotional ሆንኩኝ።
ለኔም ያ የሰማሁት ቃል በውስጤ እያደገ አለማዊነትን ፣ ትዕቢትን፣ ክፋትን በየጊዜው እያስወገደ በጠባቧ በር
ለመግባት በየቀኑ ከዚህ ዓለም ገዢ ከአመፃው መንግስት ጋር መጋደልን ከጀመርኩኝ እነሆ 28 አመት ሞላኝ። እድሜክ ስንት ነው ታዲያ ካላችሁኝ መልሴ የሚሆነው 28 አመቴ ነው ነው ምክንያቱም ሰው በጌታ እንጂ በሐማኖት ወይም ያለሃይሞኖት የኖረበት ዘመን አይቆጠርለትምና።
አመሰግናለው
በጌታ ያላችሁ በርቱ ጌታን ያላመናቹ እመኑ
ካለን በምድር ወደጌታም ከሄድን በሰማይ እንገናኝ ።
ተሜ (ዘመቻ ወንጌል)

 #አስገራሚ  #ቀናት!እንጦጦ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ (ሽሮሜዳ ላይ)፣  በኮሚኒስታዊው የደርግ ዘመን ኢየሱስ ሲሰበክና በስሙ አጋንንቶች ሲወጡ፣ ፈውስ ሲሆን ለኢትዮጵያ እና ለአዲ...
12/07/2022

#አስገራሚ #ቀናት!
እንጦጦ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ (ሽሮሜዳ ላይ)፣ በኮሚኒስታዊው የደርግ ዘመን ኢየሱስ ሲሰበክና በስሙ አጋንንቶች ሲወጡ፣ ፈውስ ሲሆን ለኢትዮጵያ እና ለአዲስ አበባ ምልክትና ምስክር አድርጎ እግዚአብሔር ካስነሳቸው ሰዎች አንዱ ነበሩ።
እነዚያ ቀናት ደማቅ ናቸው! ቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶች በጌታ ተፅናኑ!

ሞተዋል አይባልም ! ወዳገለገሉት ጌታ ሄደዋል።

የወንጌል ተልዕኮ ቤ/ን ሚኒሶታ USA
PA Temesgen

10/01/2022

Welcome to the Ethiopian Evangelical Church of Atlanta's web-stream. We are proud to offer our viewers LIVE broadcasts of our Sunday morning service, as well...

Address

Saint Paul, MN
55116

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gospel Mission worldwide Church / የወንጌል ተልዕኮ ቤ/ን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Gospel Mission worldwide Church / የወንጌል ተልዕኮ ቤ/ን:

Share