Debre Selam St.Michael EOTC

Debre Selam St.Michael EOTC በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ወቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሳክራሚንቶ , አሜሪካ
3909 36th St, Sacramento, CA 95820

https://gofund.me/d0f334052

06/09/2026

st m

� New to streaming or looking to level up? Check out StreamYard and get $10 discount! �

በክርስቶስ ያለውን መልካሙን ኑሮአችሁን የሚሳደቡ ሰዎች ክፉን እንደምታደርጉ በሚያሙበት ነገር እንዲያፍሩ በጎ ሕሊና ይኑራችሁ።” — 1ኛ . ጴጥሮስ 3:16
06/08/2026

በክርስቶስ ያለውን መልካሙን ኑሮአችሁን የሚሳደቡ ሰዎች ክፉን እንደምታደርጉ በሚያሙበት ነገር እንዲያፍሩ በጎ ሕሊና ይኑራችሁ።” — 1ኛ . ጴጥሮስ 3:16

06/07/2026

ግንቦት 30 ቅዳሴ እሁድ ግንቦት ፴ ፳፻፰ / Liturgy June 07, 2026

06/04/2026
06/04/2026
ድርሳነ_መድኃኔዓለም_ወገድለ_መባዓ_ጽዮንጌታችንም ለመባዓ ጽዮን እንዲህ አለው፡ "መታሰቢያዬንም እንደ አንተ በየወሩ የሚያደርግ ሁሉ በዓርብ ቀን ብዙ ነፍሳትን ከሲኦል አወጣለታለሁ፡፡"አቡነ መ...
06/04/2026

ድርሳነ_መድኃኔዓለም_ወገድለ_መባዓ_ጽዮን

ጌታችንም ለመባዓ ጽዮን እንዲህ አለው፡ "መታሰቢያዬንም እንደ አንተ በየወሩ የሚያደርግ ሁሉ በዓርብ ቀን ብዙ ነፍሳትን ከሲኦል አወጣለታለሁ፡፡"

አቡነ መባዓ ጽዮን ሌላኛው ስማቸው ተክለማርያም ይባላል፡፡ ለሥጋ ወደሙ እጅግ ትልቅ ክብር ስለነበራቸው የቆረበ ሰው ከቤተክርስቲያን ወጥቶ ሲሄድ እንቅፋት እንኳን ሲመታው ስለሥጋ ወደሙ ክብር ብለው የደማውን እግር ይጠቡ ነበር፤ ደሙ የፈሰሰበትንም አፈር ይመገቡ ነበር፡፡ ይህም መድኃኔዓለምን ሥጋና ደም ከማክበራቸው የተነሳ ነው፡፡ ሚስት አላገባም ብለው የዚህን ዓለም ጣዕም ንቀው የምንኩስና ልብስ ከለበሱበት ጊዜ ጅምረው በበቅሎና በፈረስ ላይ ተቀምጠው አያውቁም፤ በአልጋም ሆነ በምንጣፍ ላይ አልተኙም ይልቁንም የአንድ ሰው ሸክም የሚያህል ትልቅ ድንጋይ በደረታቸው ተሸክመው ከአመድ ላይ ይተኙ ነበር እንጂ፡፡ ከሰንበት ቀናት ውጭ ሲቀመጡም ድንጋዩን በራሳቸው ላይ ይሸከሙታል፤ ሲሰግዱም በጀርባቸው ያዝሉት ነበር፡፡ ጻዲቁ በይበልጥ የሚታወቁት ወር በገባ በሃያ ሰባት መድኃኔዓለምን አብልጠው በመዘከራቸው ነው፡፡ መድኃኔዓለምም በየጊዜው በሕፃን አምሳል ይገለጥላቸው ነበር፡፡ በዕለተ ዓርብ እንደተሰቀለም ሆኖ ተገልጦላቸዋል፡፡ ጌታችን የወርቅ በትር ሰጥቷቸው በእርሷ ነፍሳትን ከሲኦል አውጥተዋል፡፡ እንደ ቅዱስ ተክለሃይማኖት ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም በመልአክ ተወስደው የሥላሴን መንበር ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር አጥነዋል፡፡ ‘’እንደ አንተም በየወሩ በሃያ ሰባት የሞቴ መታሰቢያ ለሚያደርግ ነፍሳትን ከሲኦል አወጣለታለሁ‘’ የሚል ድንቅ ቃልኪዳን የተቀበሉ ልዮ አባት ናቸው፡፤ በዓለ ዕረፍታቸውም እጅግ አብዝተው በሚዘከሩበትና ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ታስቦ በሚውለው በመድኃኔዓለም ቀን ጥቅምት ሃያ ሰባት ቀን ነው፡፡ ከመጽሐፈ ገድላቸው ውስጥ የሚከተሉትን አስደናቂ ትምህርቶች እናገኛለን፡፡

1.1.ትንባሆ_የሚጠጡ_ሰዎች_ለምን_ለማቆም_እንደሚቸገሩና_መጨረሻቸውም_ምን_እንደሆነ፡-

“ይቅርታውና ምሕረቱ ከሁላችን የጥምቀት ልጆች ጋር ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኔዓለም ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡፡ አባታችን ዘርዓ ቡሩክ መድኃኔዓለምን እንደወደደውና በየወሩ በሃያ ሰባት ቀን በዓሉን እንደሚያከብር በአሥራ ስድስት ቀንም ኪዳነ ምሕረትን አንደሚያከብር እንሆ እንነግራችኋለን፡፡

+ በለሟልነትን ባገኘ ጊዜና መድኃኔዓለም የእሳት ፈረስንና የመስቀል ምልክት ያለበት የወርቅ በትርን በሰጠው ጊዜ ‘ወደ ኢዖል ሂድና መሸከም የምትችለውን ያህል ነፍሳትን አውጣ’ አለው፡፡ ሄዶም ወደ ሲዖል ገባ፤ ነፈስ በነፍስ ላይ እንደ ንብ እየተጨናነቁ በሰውነቱ ላይ ታዘሉ፡፡ ነፍሳትንም ይዞ ሲወጣ አንድ ኃጢአተኛ ‘ዘርዓ ቡሩክ ብቻዬን ቀረሁ፤ አውጣኝ‘ አለው፡፡ ዘርዓ ቡሩክም ወደ እርሱ ተመልሶ ሳበው፡፡ ሰም ከፈትል ጋራ እንሚጣበቅ ከሲዖል ጥልቅ ጋር ተጣብቆ እምቢ አለው፡፡ የእሳቱ ነበልባልም ዘርዓ ቡሩክን አቃጠለው፤ እርሱም ተወው፡፡ ክብር ይግባውና እነዚያን ነፍሳት ይዞ ወደ ጌታው ወደ መድኃኔዓለም ሄደ፡፡

+ ሄዶም ‘ጌታዬ ሆይ! አንዲት ነፍስ ስሜን እየጠራች ቀርታለች ማርልኝ‘ አለው፡፡ መድኃኔዓለምም ‘ዘርዓ ቡሩክ ሆይ! በእኔ ዘንድ ባለሟልነትን ብታገኝ ትንባሆ የሚጠጣንውን ማርልኝ ትለኛለህን?' አለው፡፡ እርሱም ‘ጌታዬ ሆይ! ይህቺ እንጨት በምን ትከፋለች?፤ ከሁሉ ኃጢአትስ በምን ትበልጣለች? አለው፡፡ ወይቤሎ መደኅን ኢስማዕከኑ ግብራ ለዛቲ ዕፅ ዘከመ ዘርዓ ሰይጣን ውስተ ገራህተ ዓለም፡፡ መድኃኔዓለምም 'የዚህችን እንጨት ሥራ በዓለም እርሻ ሰይጣን እንደዘራት አልሰማህንም?' አለው፡፡

+ እንሆም እንነግራችኋለን፤ ስሙ ሐዊ የሚባል የፈጣሪውንም ሕግ የሚጠብቅ አንድ መምህር ነበር፡፡ በዓርብ ቀንም ወደ ሰማይ ይሔዳል፤ በቀዳሚት ሰንበትና በእሑድ ከፈጣሪው ጋራ ይነጋገራል፡፡ በሰኞ ቀንም ወደ ቦታው ይመለሳል፡፡ ለሀገር ሰዎቸም በጉባኤ ይነግራቸዋል፤ በአዋጅ ነጋሪ ቃልም ይሰበሰባሉ፡፡ ይህቺ ሀገር ትልቅ ናትና እስከ ዓርብም ያስተምራቸዋል፡፡
+
በዚያን ጊዜ ሰይጣን ቀና፡፡ አባ ሐዊም አንደልማዱ በዕለተ ዓርብ ወደ ሰማይ በሄደ ጊዜ ያ ሰይጣን በመቀመጫው ተቀምጦ በእርሱ በሐዊ ተመስሎ በቀዳሚት ሰንበት ቀንም ተገልጦ 'ፈጣሪያችን የሚወዳትን ነገር እነግራችሁ ዘንድ ሁላችሁም ተሰብሰቡ' አለ፡፡ ሁላችውም ተሰበሰቡ፡፡ 'አባት ሆይ! ያለ ልማድህ ዛሬ ለምን መጣህና ጠራኸን?' አሉት፡፡ ያ ጠላት ዲያብሎስም 'ጌታዬ ለሕዝቦቼ የዚያቸን በቤትህ አንፃር ያለችውን እንጭት ቅጠል በጥርሳቸው ይጨምሩ ዘንድ፤ በአፋቸውም ያጤሱ ዘንድ ዛሬ ካልነገርሃቸው ወዳጄ አይደለህም አለኝ' አላቸው፡፡

+ ይህቸንም እንጨት ባያት ጊዜ እንዲህ አደረገ፤ ሔዋንን በእንጨት እንዳሳታት አሳታቸው፡፡ ዛሬ አንደሚያደርጉትም የጥንባሆ ዕቃን አደረጉ፡፡ ቅጠሏንም አምጥተው ቀጥቅጠው በእሳት አጢሰው ትንሹም ትልቁም፤ የከበረውም የጎሰቆለውም ሁላቸውም ጠጡ፡፡

+ ሐዊም በሰማይ ሳለ በጸጋ አውቆ አዘነ፤ ነገር ግን ስለ ሰንበታት ክብር ብሎ አደረ፡፡ ሰኞ በነግህም ሐዊ መጣ፤ ሰይጣንም አንደ ጢስ በኖ ጠፋ፡፡ እርሱም ሰዎቹን ሰብስቦ 'ይህን ማን አስተማራችሁ' አላቸው፡፡ 'አንተ ነህ' አሉት፡፡ 'ሰይጣን ነው እንጂ እኔ አይደለሁም፤ ከዛሬ ጀምሮ ተው' አላቸው፡፡ 'ትናንት ጠጡ፤ ዛሬ ተው ይለናል' ብለው እምቢ አሉት፡፡ እርሱም አወገዛቸው፡፡ 'በእርሻው የዘራት፤ በአፉም የጠጣት፤ በእጁም የያዛት የተረገመ ይሁን' አላቸው፡፡ ጋኔኑም በቅሉ ውስጥ ሆኖ ይነጋገራል፤ በውጭ ያሉትንም አጋንንት ይጠራቸዋል፡፡ በዚህን ሰዓት የተውም አሉ፤ እምቢም ያሉ አሉ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያቺ እንጨት ተረገመች፡፡ ሰውም በጠጣት ጊዜ የአምስት ቀፎ ሙሉ ንቦችን የሚያህሉ አጋንንት ይመጣሉ፡፡ በሁለቱ ዓይኖቹ ውስጥ፤ በሁለቱ አፍንጫዎቹም፤ በሁለቱ ጆሮዎቹም፤ በአፉም፤ በታች በሰገራ መውጫም በእነዚህ ሁሉ እንደ ቀፎ ንብ ይገባሉ፤ ይወጣሉ፡፡ ትምክህትን፤ ትዕቢትን፤ መግደልን፤ ሥርቆትንም፤ ክፉውንም ሁሉ ይመሉታል፡፡ ወሶበ ይሰትያ ብእሲ ይመጽኡ አጋንንት ዘየአክሉ መጠነ ፭ቱ ቀፈዋት ዘመልኡ አንህብት ወይበውኡ ውስቴቱ፡፡ በ፪ አዕይንቲሁ፤ ወበ፪ አዕናፊሁ፤ ወበ፪ አዕዛኒሁ ወበመንፈሱ ዘታህት በአፋሁ በዝንቱ ኩሉ ከመ ንህብ ዘቀፎ ይበውኡ ወይውጽኡ፡፡ ወይመልእዎ ትምክህተ፤ ወትቢተ፤ ቀትለ፤ ወሠሪቀ ወኩሎ ዕከያተ አንዲል መጽሐፍ፡፡ አባታችን ዘርዓ ቡሩክም ይህን ሰምቶ እጆቹን በትከሻው አመሳቅሎ አለቀሰ፤ በሥዕሉም አለ፤ በዚያን ጊዜ ወደ ዓለም ወጣ፡፡ ይህችን የተረገመች እንጨት አንዲህ ብሎ አወገዛት፡- 'በአፉ የጠጣት፤ በእጁም የያዛት፤ የዘራት፤ የሸጣት፤ የገዛትም የጥምቀት ልጅ አይደለም፤ በሥጋው አይጠቀምም፤ ነፍሱም ወደ ሲዖል ትወርዳለች፡፡ ልጄ የሆነ ግን መድኃኔዓለምንና ኪዳነ ምሕረትን ያክብር። ጥንባሆንም አይጠጣ' አለ። የዚህ ጻዲቅ በረከቱ ያልታዘዝንውን ከመብላት ይጠብቀን አሜን" በማለት ተአምረ መድኀኔዓለም ወገድለ መባዓጽየን ነገረ ጥንባሆን በሰፊው ዘግቦታል፡፡ በሌላም በኩል ትንባሆን በተመለከተ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የሰጣቸው ቃልኪዳን በራሳቸው በዘርዐ ቡሩክ ገድል ላይ የተጻውን ከገጽ ፩፻፰ ላይ መመልከት ይቻላል፡፡ እንዲሁም ይህችን የተረገመች ዕፅ የሚጠቀሙባት ሁሉ የሰይጣን ማደሪያዎች እንደሚሆኑና ክፉውንም ሁሉ እንደሚያሠሩት በሌላም ቦታ በአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ገጽ ፩፴፬ ላይ የተጻፈውን ይመልከቱ፡፡

+++ ማስታወሻ፡- ገድለ መባዓ ጽዮን ስለ ጻዲቁ ዘርዐ ቡሩክ ቃልኪዳን ሲናገር ከላይ እንደተጠቀሰው ሰይጣን የዕፅዋን ዘር በዓለም ወስዶ በመዝራት እርሷን በተለያየ መንገድ የሚጠቀሙባት ሁሉ ርጉማን እንዲሆኑ አድረጓል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንድ መታወቅ ያለበት ነገር አለ፡፡ የሥነ ፍጥረት አስገኚው ልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ ከተፈጠሩት 22 ፍጥረታት ውስጥ ለከፋ ተግባር የተፈጠረ ፍጥረት ፈጽሞ የለም፡፡ ፍጥረታትም ከተፈጠሩበት ዓላማ አንጻር ሊኖርም አይችልም፡፡ የሰው ልጅ ለአምላኩ ሕግ የመገዛቱና የመታዘዙ ውጤት የሚያስገኝለት በረከትና የሚያመጣበት መርገም እንዳለ እርግጥ ነው፡፡ እናም የሰው ልጅ የፈጣሪውን ሕግ ስለሻረ በደረሰበት መርገም ምክንያት ባሕርይው ጎስቁሉ በነፍስም በሥጋም ሞት የተፈረደበት ሆኖ ወደ ምድር መጣ! ትውልዱም ምድርን በኃጢአቱ አረከሳት፡፡ ነገር ግን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ሞትን አጥፍቶ የጎሰቆለውን የሰውን ልጅ ባሕርይ አድሶ፤ የቀደመ ክብሩን መልሶለት፤ የረከሰችውን ምድር በወርቅ ደሙ ቀድሶ! ጽድቅንና ተድላን በሰማይና በምድር ፈጽሟል፡፡

+ ስለዚህ ሲጀመር ሃያ ሁለቱም ፍጥረታት ከተፈጠሩበት ዓላማ አንጻር ምንም ለክፋት ተብሎ የተፈጠረ ፍጥረት የለም፡፡ ሲቀጥል በሰው ለጆች ኃጢአት ያደፈችው ዓለምም በክርስቶስ ደም ነፅታለች፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ ፍጥረታትን የሚጠቀምበት መንገድና ሁኔታ መጥፎም ጥሩም ሊሆን ይችላል፡፡ ለምሳሌ ቃልቻዎችና ክፉ ደብተራዎች ስር ምስው ቅጠል በጥሰው የተለያዩ የሟርት፤ የጥንቆላና የክፋት ሥራዎችን ሁሉ ይሠራሉ፡፡ ስለዚህ አሁን የሰው ልጅ ፍጥረታትን (ዕፅዋትን) ለመጥፎ አንደተጠቀመበት ሁሉ ቀድሞውንም ሰይጣን ኃጢአት የሆነውን ክፉውን ሥራ ሁሉ ለማሠራት ሲል በገድላቱ ላይ እንደተጠቀሰው ያችን የዕፅ ዘር በዓለም ሁሉ ወስዶ መዝራቱን በቀላሉ መገንዘብ አንችላላን፡፡ በእርግጥ በጠንቋዮችም ላይ አድሮ የሚሠራ እርሱ ነው፡፡

+ ያቺን ሰይጣን በዓለም ሁሉ ወስዶ የዘራትን ዕፅ በተለያየ መንገድ የሚጠቀሙ ሰዎች ኃጢአታቸው የክርስቶስን ክቡር ሥጋና ደም፤ ቅድስት ድንግል ማርያምን እንዲሁም ቅዱስ መስቀሉን ከካዱ ሰዎች ጋር የሚስተካከል እንደሆነ በገድለ ዘርዐ ቡሩክ የተጠቀሰውን ማየት ተገቢ ነው፡፡ “ዳግመኛም እግዚአብሔር ዘርዐ ቡሩክ እንዲህ አለው፡-‘ብዙ ኃጢአት ከሠሩ ከክርስቲያንም ወገን ቢሆኑ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ሰም ያለተጠመቁ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም የተወለደ የክርስቶስ ሥጋና ደም ካልተቀበሉ ከአረማውያንም ወገን ቢሆኑ ንሳሓ ገብተው በጸሎት በሚፀኑ በቃልኪዳንህም ቢያምኑ ከገሃነመ እሳትና ከሁለተኛ ሞት ይድናሉ‘ ብሎ ቃልኪዳንና ጽኑ መሐላ ሰጠው፡፡ ‘እኔን ከካዱ የባሕርይ አባቴ አብን የባሕርይ ሕይወቴ መንፈስ ቅዱስን ከካዱ ሰዎች በቀር፤ እናቴንና መስቀሌን፤ ሥጋዬንና ደሜን ከካዱ ሰዎች በቀር፤ ስሙ ትንባሆ የሚባል የተረገመ ቅጠልን ከጠጡ ሰዎች በቀር ንስሓ ገብተው በጸሎትህ ቢማፀኑ ከዘለዓለም እሳትና ከሁተኛ ሞት አድናቸዋለሁ' አለው“ ተብሎ ነው የተጻፈው፡፡

+ ሱስን በተመለከተ በአሁኑ ሰዓት ዓለም ላይ ያለውን ችግር ሁሉም ሰው በደንብ ያውቀዋል፡፡ በቅዱሳን ገድላቱም ላይ (ማለትም በገድለ መባዓ ጽዮን፤ በገድለ ዘርዐ ቡሩክና በአባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ገድል) ላይ የተጻፈው ነገር አሁን ዓለም ላይ ያለውን ችግር ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በመልእክቱ “ከእግዚአብሔር እንደሆንን ዓለምም በመላው በክፉው እንደተያዘ እናውቃለን“ በማለት እንደተናገረው ሱስ የሰይጣን ስውር የክፋት ሥራ መሆኑን በቀላሉ መረዳት እንችላለን፡፡ 1ኛ ዮሐ 5፡19፡፡ በቀላሉ ሱስ ውስጥ የገቡ ሰዎች ለምን ሱሱን ማቆም እንደሚቸገሩ፤ መጀመሪያውንም በቀላሉም ወደ ሱሱ እንዴትና ለምን አንደሚገቡ፤ ሱስ የሚጠቀሙ ሰዎቸም የተለያዩ ወንጀሎቸን ለምን አንደሚፈጽሙ...... እነዚህ ሁሉ የሰይጣን ሥራዎች በእኛ ዘንድ የተገለጡ ናቸው፡፡ “…ከዚያን ጊዜ ጅምሮ ያቺ አንጨት ተረገመች፡፡ ሰውም በጠጣት ጊዜ የአምስት ቀፎ ሙሉ ንቦችን የሚህሉ አጋንንት ይመጣሉ፡፡ ሰውም በጠጣት ጊዜ የአምስት ቀፎ ሙሉ ንቦችን የሚያህሉ አጋንንት ይመጣሉ፡፡ በሁለቱ ዓይኖቹ ውስጥ፡ በሁለቱ አፍንጫዎቹም፤ በሁለቱ ጆሮዎቹም፤ በአፉም፤ በታች በሰገራ መውጫም በእነዚህ ሁሉ አንደ ቀፎ ንብ ይገባሉ፤ ይወጣሉ፡፡ ትምክህት፤ ትዕቢትን፤ መግደልን፤ ስርቆትንም፤ ክፉውንም ሁሉ ይመሉታል…“ ተብሎ ነው በገድለ መባዓ ጽዮን ላይ የተጻፈው፡፡ ይህ እጅግ አስፈሪ ነው በእውነት!

+ መፍትሄ፡-

“ሰው ለተሸነፈበት ለእርሱ ባሪያ ነው" (2ኛ ጴጥ 2፡19)፤ “ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፤ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና፡፡ ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ" (1ኛ ዮሐ 3፡8)፤ “ሰውነታቸሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተመቅደስ አንደሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ" (1ኛ ቆሮ 6፡19)፤ “የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? ማንም "የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፤ ያውም እናንተ ናችሁ" (1ኛ ቆሮ 3፡17)

ወደ ገድለ መባዓ ጽዮን እንመለስና ሌሎች ጉዳዮችን እንመልከት፡-

1.2.እነዚህን ያላደረጉ ሰዎች መድኃኔዓለም እንደካዱ ይቆጠራሉ፡-

“…ክብር ምስጋና ይግባውና መድኃኔዓለምን የሚክዱትና የሚጠሉት የማይወዱትም እኒህ ናቸው፡- ሰባቱን አጽዋማት የማይጾሙ፤ ይህም ሁሉ ባይቻላቸው የመጾም ክብራቸው እንደ ሰንበታት ክብር የሆኑ ረቡዕንና ዓርብን የተቀደሰች ዓርባ ጾምንም የማይጾሙ፤ በዓላቶቹንና የእናቱንም በዓላት ሰንበታትንም የማያከብሩ፤ የሞቱን መታሰቢያ የማያደርጉ፤ በእነዚህ በዓላትም በስሙ ለመጸለይ የእርሱንና የእናቱን የድንግል ማርያምን ተአምር ለመስማት ወደ ቤተ ክርስቲያን የማይመጡ፤ ኃጢአታቸውንም ለካህን የማይናገሩ፤ ጌታችውን ደስ ሳያሰኙት ንስሓ ሳይገቡ በሞቱ ጊዜ መድኃኔዓለምን እንደ ካዱ ይቈጠራሉ"

1.3. ዘርዓ ያዕቆብን የሚያሙ ሰዎች ዕጣ ፈንታቸው ምን እንደሆነ፡-

"መባዓ ጽዮን በመድኃኔዓለም ፍቅር ስለጨከነ ስለ ሕማሙ ይታመም ዘንድ፤ እጆቹንና እግሮቹንም መቸንከሩን አስቦ ይቸንከር ዘንድ አሰበ፡፡ 'በመሀል እጄ በእግሬም ባደርገው የተቸነከረው ችንካር ይታያል፤ ሰውም ያውቅብኛል፤ ውዳሴ ከንቱም ይሆንብኛል፡፡ ስለዚህ በጉልበቴ ባደርገው ይሻለኛል' ብሎ አሰበ፡፡ የሾሉ ችንካሮችንም አምጥቶ ጉልበቶቹ ላይ በድንጋይ ቸነከራቸው፡፡ ከሕማሙም ጽናት የተነሣ እያለቀሰ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ፡፡ ጌታችን መድኃኔዓለምም ወደ እርሱ መጣና ችንካሮችን ከጉልበቶቹ አወጣለት፤ ቁስሉንም በእጁ ዳሶ ፈወሰው፡፡ 'ይህን ጉልበት የሳመ ለሕይወትና ለመድኃኒት ለኃጢአት ሥርየትም ይሁነው' አለው፡፡ 'የተመላለሰባቸው ሀገሮችም ይባረኩ፤ እነሆ ችንካሮችህን ከሕመሜ ጋራ አንድ ይሆኑ ዘንድ በእጄ ያዝኳቸው' አለው፡፡ ከዚያም ጌታችን መባዓ ጽዮንን ወደ ሰማይ አወጣውና ከመንበሩ ፊት አደረሰው፡፡ በመንበሩም ዙሪያ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይን አየ፡፡ በመንበሩም ዙሪያ ስለተገፉ ሰዎች ፍርድ ይወጣል፡፡ የሚያስደንቁ ነገሮችንና ሰፊ ሀገርንም አየ፡፡ ዳግመኛም ከሚያስፈራና ከሚያስደነግጥ ገደል ውስጥ ጨለማን አየ፤ ብዙ ሰዎችም በውስጡ ይወድቃሉ፡፡ መድኃኔዓለምንም ጠየቀው፤ 'እኒህ ሰዎች እነማን ናቸው?' አለው፡፡ ጌታም 'ንጉሥ ዘርዓ ያዕቆብን ያሙት ሰዎች ናቸው ስለዚህ ነገር ተፈረደባቸው' አለው፡፡ ዳግመኛም በነጫጭ ፈረሶች አምሳል ሁለት ደመናዎችን አየ፡፡ ‘እኒህ ፈረሶች የማን ናቸው?’ አለው፡፡ መድኃኔዓለምም ‘እንዱ የአንተ አንዱ የዘርዓ ያዕቆብ ናቸው፤ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ስትሄዱ የምትቀመጡባቸው ናቸው' አለው፡፡ ‘እኔን በደለኛውን ሃይማኖቱ የቀና እውነተኛ ፈራጅ ከሆነው ከፀሐይ ዘርዓ ያዕቆብ ጋራ በምን አስተካክልከኝ?''በእኔ ፍቅር ልቡናችሁ ስለሚቃጠል ነው‘ አለው፡፡ ይኸን ሰምቶ ከመድኃኔዓለም ስጦታ የተነሣ አደነቀ፡፡"

+ "ሐሜትንም የሚገልጥ ሰነፍ ነው፤ በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም፤ ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው" (ምሳ 10፡19)፤ “በዚያም ቀን የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቅሶና ወደ ዋይታ ራስን ወደ መንጨትና ማቅንም ወደ መልበስ ጠራ፡፡ እነሆም፤ ሐሜትና ደስታ… ሆነዋል፤ እናንተ ነገ እንሞታለንና እንብላ እንጠጣ ብላችኋልና፡፡ ይህም ነገር በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ጆሮ ተሰማ፡፡ እስክትሞቱ ድረስ ይህ በደል በእውነቱ አይሰረይላችሁም ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር“ (ኢሳ 22፡12-14)፤ “ሰመጣ፤ እንደምወደው ሳትሆኑ አገኛችሁ ይሆናል ብዬ እፈራለሁና፤ ምናልባት ክርክር ቅንዓትም ቁጣም አድመኝነትም ሐሜትም ማሾክሾክም ኩራትም ሁከትም ይሆናሉ" (2ኛ ቆሮ 12፡20)፤ “እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዱ" 1ኛ ጴጥ 2፡

1.4 መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለአቡነ መባዓ ጽዮን የተገለጠበት ልዩ ሁኔታ

1.4.1.ጌታችን ለአቡነ መባዓ ጽዮን በመሠዊያው ላይ በበግ አምሳል እንደታየው፡-

“አባታችን መባዓ ጽዮን ‘በመሠዊያው ፊት እያጠነ ሳለ ቄሱም ወንጌል ለማንበብ በወጣ ጊዜ በፃህሉ ላይ ቁርባኑ ሲንቀሳቀስ አየሁ’ አለ፡፡ ‘የሆነውንም አውቅ ዘንድ መሸፈኛውን በእጄ ባነሳሁት ጊዜ ነጭ በግ ሆኖ አገኘሁት፤ ደንግጬ እንደመጀመሪያው ሸፈንሁት’ አለ፡፡ ካህኑም ወንጌሉን አንብቦ ጨረሶ ሲቀድስ ኅብስት ወደመሆን ተመለሰ፡፡ ‘ሁላችንም ወንዶቹም ሴቶቹም ተቀበልን እንደዚህ ያለም ነገር ሦስት ቀን አየሁ’ አለ፡፡”

1.4 ጌታችን ለአቡነ መባዓ ጽዮን በመሠዊያው ላይ በበግ አምሳል እንደተገለጠለት፡-

“አባታችን መባዓ ጽዮን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደበት ታኅሣሥ ሃያ ዘጠኝ ቀን በዓሉን ለማክበር ከቤቱ በወጣ ጊዜ የዚያን ጊዜ የጨረቃ ብርሃን ነበረ፡፡ ወደ ሰማይም አንጋጦ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ በዚያን ጊዜ የሰማይ በር ተከፍቶ አየ፡፡ ‘እንደመብረቅ ያለ በእኔ ትክክል ወደረ’ አለ፡፡ ‘ወደ እኔም ቀርቦ ሕፃን ሆነ፤ በአጠገቤም ተቀመጠ፤ አንገቴንም አቀፈኝ’ አለ፡፡ ‘በዚያን ጊዜ ፍርሃትና መንቀጥቀጥ ያዘኝ፤ እንደሰምም ቀለጥሁ፤ እንዲህም ሲል መለሰኝ፡-‘በዛሬዋ ቀን የተወለድሁ የማርያም ልጅ እኔ መድኃኔዓለም ነኝ አትፍራ’ አለኝ፡፡ ምንም አላውቅም ልቤን አሳጣቶኛልና፡፡ ለአንድ ሰዓትም በልብሴ ቋጠርሁት፡፡ ከእኔ ላይም ሊነሣ በወደደ ጊዜ ‘ጌታዬ ሳልጠግብህ ልትሄድ ነውን?’ አልሁት፡፡ በዚያን ጊዜ ምራቁን ከራሴ ላይ እንትፍ አለ፡፡ ‘ንሳ ተስፋ ይሁንህ፤ ተረጋጋበትም፤ እኔም አልተውህም፤ ዘወትር ከአንተ ጋር እሆናለሁ’ አለኝ፡፡ ይህንንም ብሎ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡””

+“አባታችን እንደ ልማዱ በዕለተ ዓርብ የመድኃኔዓለምን መታሰቢያ ያደርግ ነበር፡፡ ጌታችንም በሕፃን አምሳል መጣና አንገቱን አቀፈው፡፡ ሁለመናውንም በብርሃን ሸለመው፡፡ ራሱንም ይዞ ፊቱንና ጉንጮቹን ዳሰሰው፤ ከእርሱም ጋራ ተጫወተ፡፡”

1.4.3 መድኃኔዓለም ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ እንደተሰቀለ ሆኖ ለአቡነ መባዓ ጽዮን ታየው፡-

“የመድኃኔዓለምን መከራ እያሰብኩ ደረቴን እየደቃሁ መሪር ዕንባ እያለቀስሁ ‘ፈጣሪዬ ሆይ! ሕማምህን አይቼ ስለ አንተ እንዴት እንዳለቅስ አሳየኝ’ ብዬ እግዚአብሔርን ለመንሁት፡፡ ‘ጌታዬ ሆይ! አንተ ለምን የወደድኸውን ሁሉ እኔ እሰጥሃለሁ አልኸኝ፤ አሁንም ይህን የለመንሁህን ግለጥልኝ፤ እናቴም አባቴም አንተ ነህ፤ ከአንተ በቀር ሌላ የለኝም’ እንዲህ እያልኩ ስለምን ድንገት ተገለጠልኝ፡፡ ‘መከራዬን ማየት ወደድህን?’ አለኝ፡፡ ‘ያንተ ኃይል ያጽናኝ ነገር ግን ታሳየኝ ዘንድ ፈቃድህ ይሁን’ አለሁት፡፡ ከዚህም በኋላ ‘ታይ ዘንድ ና’ አለኝ፡፡ በብርሃን ሰረገላ ወደ ላይ አወጣኝ፤ ኢየሩሳሌም አደረሰኝ፡፡ ‘የተሰቀልሁበት ቀራኒዮ ይህ ነው’ አለኝ፡፡ በዚያን ጊዜ ዕፅ መስቀል መጣ፤ መድኃኔዓለምም እንደቀድሞው በላይ ወጥቶ በዚያ ቆመ፡፡ቅዱሳት የሆኑ እጆቹን በመስቀሉ ላይ ዘረጋ፤ እጆቹንም እግሮቹንም ተቸነከረ፡፡ የእሾህ አክሊል በራሱ ተሸክመሞ ደስ የሚሉ ዓይኖቹንም ዕንባን ተሞልተው ታየኝ፡፡ ባየሁትም ጊዜ ሁለመናዬ ቀለጠ፤ ከመሬትም ወደቅሁ፤ እንደሞትሁም ሆንሁ፡፡

በመድኃኔዓለም በኃይሉ ጽናት ባይሆን ኖሮ ነፍሴ ከእኔ በተለየች ነበር፡፡ ከመስቀሉም ወረደና ‘ሕማሜን ማየት አትችልም አላልኩህም ነበርን?’ ብሎ በቃሉ ኃይል አነሳኝ፡፡ ‘ጌታዬ ሆይ! የሞትህ ገናንነት እንደዚህ የሚያስፈራና የሚያስደነግጥ መሆኑን አላወቅሁም ነበር፤ ምኞቴን የሰጠኸኝ ስምህ ይባረከ፤ ፈቃድህም በእኔ ላይ ተፈጸመ፡፡ ሰውን የምትወድ ጌታ ሆይ! አሁንም ባሪያህ እኔ እንደምችለው መጠን መታሰቢያህን እደርግ ዘንድ ባርክልኝ፡፡ ስለ ፊትህ መጸፋት፤ ስለ ራስህ መመታት፤ ስለ ጀርባህ መገረፍ፤ ስለ እጆችህና እግሮችህ መቸንከር፤ ስለ ጎንህም መወጋት፤ ስለ ሥጋህ መታረድና ስለ ደምህ መፍሰስ የማቀርብልህን ቁርባንና ዕጣን ውደድ’ አልሁት፡፡ እርሱም ‘የተባረከና የተቀደሰ ይሁንልህ’ አለኝ፡፡ ‘መታሰቢያዬን በምታቀርብበት ቀንም እኔ ከአንተ አልለይም፤ በመታሰቢያዬ ቀን ቀርቶ ሁልጊዜም አልተውህም፤ ዘርህንም አልተውም፡፡ ስሜም ከስምህ አይርቅም፤ እንደወደድኸኝ እኔ እወድሃለሁ፡፡ ነገር ግን በምን አምሳል ሁኜ እንደምታይህ ምረጥ፤ ሕፃን ሁኜ ነውን? ወይም ጎልማሳ ሁኜ ነውን? ወይም እንደዛሬው በሞቴ ሕማም ሁኜ ነው?’ አለኝ፡፡

+ እኔም ‘ጌታዬ ሆይ! እንደፍቃድህ ይሁን’ አልሁት፡፡ እርሱም ‘ልብህን ደስ እንደሚያሰኘው አንተ ምረጥ’ አለኝ፡፡ ‘እኔን ባርያህን መባዓ ጸዩንን ከወደድኸኝና ካሰለጠንኸኝ ሕፃን በመሆን እየተጫወትህ ትታየኝ ዘንድ እወዳለሁ’ አልሁት፡፡ ጌታዬም ‘እሺ እንደወደድህ’ አለኝ የዚያን ጊዜም ከእግሩ በታች ሰግደጄ አመሰገንሁት፡፡ ከዚህ በኋላ የብርሃ ሰረገላ ተሸክሞ ከሀገሬ አደረሰኝ፡፡ ሥራውን ቸል የማይል መድኃኔዓለም ተሠወረኝ፡፡”

1.4.4. ጌታችን እፍ ብሎ እስትንፋሱን ከመባ ጽዮን እስትንፋስ ጋር በማዋሃድ ቃልኪዳን አንደሰጠው፡-

“ተክለማርያም የተባለ መባዓ ጽዮን የመድኃኔዓለምን በዓል ከሌላ ጋር አይጨምርም ነበር፡፡ ለመድኃኔዓለም መታሰቢያ የሚሆነውን ሁሉ ለብቻው ያስቀምጠዋል፡፡ በረሃብ እስኪሞት ድረስ ከመድኃኔዓለም መታሰቢያ እህል ምንም አይቀምስም፡፡ ያዘጋጀውንም ኅብስትና ጽዋ ለሕዝቡ ይሰጣቸዋል፡፡ የታመሙ ሰዎቸም ለመድኃኔዓለም መታሰቢያ ከተዘጋጅው በበሉ ጊዜ ከሕመማቸው ሁሉ ይድናሉ፡፡ አባታችን የሚያዘጋጀውን የመድኃኔዓለምን መታሰቢያ ይበሉ ዘንድ እየተጨናነቁ ከቅርብም ከሩቅም ሰዎች በእምነት ይመጡ ነበር፡፡

+ በየወሩ በዓሉም በቀረበ ጊዜ በጾምና በጸሎት ሰባት ቀን ይማለላል፡፡ ሆዱን ሳይጠግብ ራሱን ሳያስተኛ በፍጹም ልቅሶ መከራውን ያስባል፡፡ ምድርን እስኪያርስ ድረስ ከዓይኖቹ ዕንባን ያፈሳል፡፡ ከልቅሶውም ብዛት የተነሣ እስኪጠፋ ድረስ ዓይኖቹ ታመሙ፡፡ እመቤታችን ማርያምም ብርሌ የሚመስል ጽዋን በእጇ ይዛ መጣች፡፡ ‘ወዳጄ ተክለማርያም ሆይ! ስለ ልጄ ፍቅር ለታመሙ ዓይኖችህ መድኃኒትን እሰጥህ ዘንድ እነሆ መጣሁ’ አለችውና ጣቶቿን ከዚያ ጽዋ ነክራ ዓይኖቹን ቀባችው፤ ከሕመሙም ዳነ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሕመም አላገኘውም፡፡

+ በተቀደሰች በዓርባ ጾምም የመድኃኔዓለምን ግርፋት እያሰበ ሰውነቱን በእጅጉ ገረፈ፡፡ ደሙ ከመሬት እስኪወርድ ድረስ ልቡንም አጥቶ ከምድር ላይ ወደቀ፡፡ የመድኃኔዓለምን መከራውን አስቦ እንደሞተ ሆነ፡፡ መድኃኔዓለምም ወደ እርሱ መጣና ‘ተነሥ እኔ ቁስልህን እፈውስሃለሁ’ ብሎ የጀርባውን ቁስል ዳሰሰው፡፡ ምንም ሕማም እንዳላገኘውም ሆነ፡፡ መድኃኔዓለምም አባታችንን ‘በአንተው እጅ ትገደልን? እኔ እንኳ የተገደልኩት በአመፀኞች በአይሁድ እጅ ነው’ አለው፡፡ በዚያችም ሰዓት ጌታ የመባዓ ጽዮንን ከንፈሮቹን ይዞ አፉን ከፍቶ ሦስት ጊዜ እፍ አለበት፡፡ ‘የከበረ ትንፋሼም ከትንፋስህ ጋር ይጨመር፤ ሥጋህም ከነፍስህ ጋራ የከበረ ይሁን’ አለው፡፡ ‘አንተ በላዩ እፍ ያልህበትም የተቀደሰና የከበረ ይሁን’ አለው፡፡ ይህንንም ብሎ ሕፃን መድኅን ወደ ድንግል እናቱ ታቀፈ፡፡ ጡቷንም ጠባ፤ ለእርሱም የግራ ጡቷን አጠባው፡፡ ብፁዕ ተክለማርያምንም አይቶ ለሰው ፈጽሞ የሚያስደንቅ ነገርን ነገረው፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምም ፈገግ አለች፡፡ ስለ ለጇ ስለ ፍቅሩ ገናነትም ተደሰተች፡፡ መድኃኔዓለምም አባታችንን ‘ስለ ሕማሜ ታመሃልና ስለ ክቡር ደሜም ደምህን አፍሰሃልና ስለ ሞቴም ሞተሃልና እንደወደድኸኝ እኔም እወድሃለሁ፤ ሁሉጊዜም ከአንተ አልለይም፡፡ አንተን የወደደ እኔን ወደደ፤ አንተንም የጠላ እኔን ጠላ፤ የላከኝንም ጠላ፤ እኔን እንደጠሉኝ አንደ አይሁድ ይሁን፡፡ ነፍስህ ከሥጋህ ተለይታ በምትወጣበት ቀንም ለሌላ አልሰጣትም እኔ እቀበላታለሁ እንጂ’ አለው፡፡ ‘ወደ አንተ የደረሰ ሁሉ ወደ ቤተክርስቲያንህም የመጣ፤ በአንተም የተማፀነ፤ በእጅህም የተባረከውን ሁሉ እምርልሃለሁ፡፡ በእኔና በእናቴ ማርያም ስም በማይታበል ቃሌ ቃልኪዳን ሰጠሁህ፤ መሐላዬንም አላጎድልብህም’ አለው፡፡ አባታችንም ይህን ሰምቶ ፈጽሞ ተደሰተ፡፡ ‘ያለቸርነቱ በቀር በጎ ሥራ ለሌለኝ ለእኔ ለኃጢአተኛው ይኸን ሁሉ ስላደረገልኝ ለእግዚአብሔር ምን እከፍለዋለሁ?’ አለ፡፡ ነገር ግን ስሙ ለዘለዓለም የተባረከ ይሁን አሜን፡፡”

1.4.5.ሥጋ ወደሙን ሰዎች_ተገቢ ባልሆነ ሁኔታ ሲቀበሉ እመቤታቸን ተገልጣ እንዳናገረችው፡-

“መባዓ ጽዮን አንድ ቀን በቁርባን ጊዜ ከአንድ ቄስ ጋራ ሲያገለግል ታላቅ ማስፈራት ሆነ፡፡ እርሱም ‘ግርማዋ የምታስፈራ ሴትን አየሁ’ አለ፡፡ ‘ዕንባዋንም ከዓይኖቿ ታፈሳለች፤ ከግርማዋ የተነሣ ፈጽሜ ፈራሁ፡፡ ‘የተወደደ የልጄን ሥጋ በጥርሳቸው ሲያላምጡት ታያለህ?’ ስትል መለሰችልኝ’ አለ፡፡ ‘ባየሁትም ጊዜ አንጀቴ ይላወሳል፤ ልጄ የሞተ ይመስላቸዋል፤ ሕይውም እንደሆነ አያውቁም’ ብላ እያለቀሰች ነገረችው፡፡ እርሱም ከእርሷ ጋር አብሯት አለቀስ፡፡ ‘ካህናቱንና ዲያቆናቱንም በጥርሳችሁ በመንጋጋችሁ አታላምጡ፤ በመፍራት በትናጋችሁ ብሉ እንጂ’ ብሎ አዘዛቸው፡፡”

1.4.6. መባዓ ጽዮን የጌታን መከራ እያሰበ ሲያለቅስ እመቤታችን ተገልጣ አብራው እንዳለቀሰች፡-

“አባታችን መብዓ ጽዮን ለአንድ ትሁት ዲያቆን ‘ትጠብቅ ዘንድ ትችል እንደሆን ምሥጢር ልንገርህ’ አለው፡፡ እርሱም ‘እሺ’ አለው፡፡ አባታችንም ‘በሕይወት ዘመኔ ሳለሁ እንዳትናገር በጴጥሮስና በጳውሎስ ሥልጣን ትታሰራለህን? ከሞትኩ በኋላ ግን የወደድከውን አደርግ’ አለው፡፡ ያም ዲያቆን ‘አባቴ እሺ በል ንገረኝ አለው፡፡ ‘አንድ ቀን ከቀኑ በሦስት ሰዓት እየጸልያለሁ ሳለሁ የጌታዬ የመድኃኔዓለም የሞቱን መከራና የቅድስት እናቱ የድንግል ማርያምን ልቅሶ አስቤ አለቀስሁ፡፡ እመቤቴ ሆይ! በዚህች ሰዓት የምትወጂው የአንድ ልጅሽ ስቅለቱንና መራቆቱን መገረፉን መቸንከሩንም አይተሸ እንደምን ተንገላታሽ? እመቤቴ ሆይ! በዚህች ሰዓት የምትወጂው የአንድ ልጅሽ ስቅለቱንና መራቆቱን መገረፉን መቸንከሩንም አይተሸ እንደምን ተንገላታሽ? እመቤቱ ሆይ በዚያች ሰዓት ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ ሳትወጣ የምትወጅው መድኅን የተሰቀለበትን ግንድ ይዤ እኖር ዘንድ ተመኘሁ’ እያልሁ ሳለቅስ በቀኜ በኩል ብርሃን በራ፡፡ በዚያን ሰዓት እመቤታችን ማርያምን አየኋት፤ እንዲህ ስትልም መለሰችልኝ፡- ‘መባዓ ጽዮን ሆይ! ለምን ታለቅሳለህ? እኔስ የልጄን መራቆቱን፤ መገረፉን፤ መቸንከሩን፤ ተሰቅሎ መሞቱን አይቼ አለቀስሁ፤ አንተ ግን ሳታይ ታለቅሳለህ’ አለችኝ፡፡ ይህንንም ባለችኝ ጊዜ ከእርሷ ጋር አለቀስሁ፡፡ ልቅሶንም ከጨረስን በኋላ ነፍሴን ለእርሷ አደራ ሰጠሁ፡፡ እንባዬንም በልብስዋ ጠርጋ ከእኔ ተሰወረች፡፡”

1.5.መድኃኔዓለም ከክርስቶስ ለአቡነ መባዓ ጽዮን የሰጣቸው ልዩ ቃልኪዳን፡-

ቀደም ብለን መድኃኔዓለም ክርስቶስ እፍ ብሎ እስትንፋሱን ከመባዓ ጽዮን እስትንፋስ ጋር እንደባለቀለትና ልዩ ቃልኪዳን እንደሰጠው አይተናል፡፡ ከዚያ በተጨማሪ ጌታ የሚከተለውን እጅግ አስደናቂ ቃልኪዳን እንደሰጠው ቃልኪዳኑንም እስከ ዕለተ ምጽዓት ድረስ እንደሚያጸናለት በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ምሎለታል፡፡

1.5.1 የመድኃኔዓለምን የሞቱን መታሰቢያ ያደረገ ሰው ነፍሳትን ከሲኦል ያወጣል፡-

“ጌታችን ደም ግባቱ ያማረ፤ ልብሱም የመስቀል ምልክት የሆነ ንጹሕ አክሊል በራሱ የተቀዳጁ ጎልማሳ ሆኖ በፊቱ ቶመ፡፡ ‘ልመናህን እፈጽምልህ ዘንድ እነሆ ወደ አንተ መጣሁ’ አለው፡፡

‘...እንደ አንተ በዓሌን ያደረገውን እምረዋለሁ፤ የብርሃን ልብስንም አለብሰዋለሁ...’ ብሎ ቃልኪዳን ከሰጠው በኋላ ሁለመናው በመለኮት ጨውነት ይጣፍጥ ዘንድ አውራ ጣቱን አጠበው፡፡ ከዚህም በኋላ ከእርሱ ተሰወረ፡፡ እንዲሁም በሌላ ጊዜ እንዲህ እያለ ለመነ፡ ‘ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ! በዓልህን እንዳደርግ አንድ አንተ የምትወደውን ግለጥልኝ’ አለ፡፡ ጌታም ‘የሞቴን መታሰቢያ ያደረገ እንደ እኔ ነፍሳትን ከደይን ያወጣል፤ ‘በእኔ የሚያምን እኔ የምሠራውን ይሠራል፤ ከዚያም የበለጠ ይሠራል’ ብዬ በወንጌል እንደተናገርሁ’ አለው፡፡”

+ “ክርስቲያኖች ሁሉ የፈጣሪያችንን የመድኃኔዓለም ክርስቶስን የመታሰቢያ በዓሉን እናድርግ፡፡ የአባቶቻችን የሐዋርያት፤ የጻድቃን፤ የሰማዕታት፤ የመላእክት መታሰቢያቸው ባረፉበት በተሾሙበት ቀን ይከበራል፡፡ እነርሱን የፈጠራቸው እርሱ መድኃኔዓለም ነው፤ ያከበራቸው፤ ከፍ ከፍ ያደረጋቸው፤ ስማቸውን ለጠራ መታሰቢያቸውን ያደረገ እንደሚድን ቃልኪዳን የሰጣቸው እርሱ ነው፡፡ የመድኃኔዓለምን የሞቱን መታሰቢያ ያደረገ ግን የተኮነኑ ነፍሳትን ከደይን ያወጣል፤ በሞቱም ጊዜ ሥቃይን አያያትም፡፡”

+“ጌታችንም ለመባዓ ጽዮን እንዲህ አለው፡-‘መታሰቢያዬንም እንደ አንተ በየወሩ የሚያደርግ ሁሉ በዓርብ ቀን ብዙ ነፍሳትን ከሲኦል አወጣለታለሁ፡፡ አንተ ከምታደርገው ከሞቴ መታሰቢያም ቁራሽ የበላውን፤ ከሩቅም ወሬህን ሰምቶ በልቡ ደስ ያለውና የወደደውን ከሞቴ መታሰቢያ መድረስ ባይቻለውም እንኳ እምረዋለሁ፡፡’ መድኃኔዓለምም ይህን በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ማለለት፡፡”

+አዘጋጅ፡ ዘሪሁን እሸቱ / ከገድላት አንደበት ከሚል መጽሐፍ ከገጽ 65-75 /ዋልድቢት ቅድስት ማርያም ወአባ ሳሙኤል አንድነት ገዳም መነኮሳት ያሳተሙት 1996 ዓ.ም በገብረ ሥላሴ ከተዘጋጀው መጽሐፍ ላይ ተወስዶ በእጅ ተጽፎ በዘሪሁን እሸቱ በቀን 27/03/2010 ዓ.ም ተጻፈ/

በ ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ። መዝ 132፡14

06/04/2026

st m

Address

Sacramento, CA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Selam St.Michael EOTC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share