EOTC Maryland Diocese

EOTC Maryland Diocese በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት የሜሪላንድ ግዛት ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት

"በጎነትን መመስከርና ለጽድቅ መቆም የሕሊና ግዴታ ብቻ ሳይሆን፣ የነፍስ ጥሪም ነው!"
05/14/2026

"በጎነትን መመስከርና ለጽድቅ መቆም የሕሊና ግዴታ ብቻ ሳይሆን፣ የነፍስ ጥሪም ነው!"

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ የተገመተ G+2 ሕንጻ  መኖሪያ ቤት  ለመቄዶንያ በስጦታ አበረከቱ።ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሚያዚያ ፳፫/፳፻፲፰ ዓ/ም ብፁዕ አ...
05/02/2026

ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ የተገመተ G+2 ሕንጻ መኖሪያ ቤት ለመቄዶንያ በስጦታ አበረከቱ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ሚያዚያ ፳፫/፳፻፲፰ ዓ/ም

ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል የሰሜን አሜሪካ የዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ የተገመተ G+2 ሕንጻ መኖሪያ ቤት ለመቄዶንያ በስጦታ አበረከቱ።

በአሁኑ ሰዓት ብፁዕነታቸው መቄዶንያ ባዘጋጀው የቀጥታ ሥርጭት ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ላይ ተገኝተዋል።

ብፁዕነታቸው ቤቱ ከ23 ዓመታት በፊት ለገዳማትና ለወላጆቻቸውን በተለያያዩ ምክንያቶች ላጡ ወገኖች ዕርዳት እንዲሆን በማቀድ የተሠራ መሆኑ ገልጸዋል።

በዚህ ላለፉት በርከታ አመታት በተከራይቶ ከሚገኘው ገንዘብ ለተለያዩ በጎ ዓላማ ሲውል መቆየቱን አስተውሰው በአሁኑ ሰዓት ቀደም ብየ ያሰብኩትንና በውስጥም ስሠራበት የነበረውን በጎ ሥራ በዘለቄታዊነት ሊያስቀጥል የሚችል በጎ አድራጎት ድርጅት ሳስብ የመጣለኝ መቄዶንያ በመሆኑ ለዚሁ እንዲሰጥ ወሰንኩኝ ብለዋል።

ቤቱን የሰጡት የካቲት 1/2018 ዓ/ም ቢሆንም በመቄዶንያ ሥራ አስኪያጅ ክቡር አቶ ቢንያም አማካኝነት ብፁዕነታቸው በሚዲያ ቀርበው እንዲሰጡና ርክክቡም በአካል በቤቱ በመገኘት እንዲሆን እንዲሁም ይህን አርአያነት ያለውን መልካም ሥራ ለሌሎችን ትምህርት እንዲሆን በማሰብ የግድ ወደ ሚዲያ እንደመጡም ተገልጿል።

የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ሕሙማን መረጃ ማዕከል በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚረዱበትና በሀገረ ደረጃም በበረካታ ቦታዎች ቅርጫፎችን የከፈተ መሆኑ የሚታወቅ ነው።

©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው

“ሐዋርያትም የጌታን የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ በታላቅ ኃይል ይመሰክሩ ነበር፤”ሐዋ 4:13መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ በሞቱ ሞትን ድል አድርጎ መነሳቱ የሰው ልጆች የነጻነት አዋጅ እና የ...
04/17/2026

“ሐዋርያትም የጌታን የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ በታላቅ ኃይል ይመሰክሩ ነበር፤”ሐዋ 4:13

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ በሞቱ ሞትን ድል አድርጎ መነሳቱ የሰው ልጆች የነጻነት አዋጅ እና የደስታችን ምንጭ መሆኑን በማስብ በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሥር የሚገኙ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቃነ መናብርት እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤት ሊቃነ መናብርት በጋራ በመሆን ለሃገረ ስብከቱ ሊቀ ዻዻስ ለብፁዕ አቡነ ፋኑኤል የእንኳን አደረስዎ መርሀግብር ዛሬ በአዳም ሐሙስ በዲሲ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በደመቀ ሁኔታ አክብረው ውለዋል።

ጉባኤው በብፁዕ አቡነ ፋኑኤል መሪነት በጸሎት የተከፈተ ሲሆን፤ በመቀጠልም የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ መልአከ አርያም መምህር ብርሀኑ ጎበና የመግቢያ መልዕክት ያስተላለፋ አስተላልፈዋል፤ በመልዕክታቸውም አያይዘው ይህ መሰባሰብ እና አንድነት የብፁዕ አባታችን የትጋት እና የጸሎት ውጤት መሆኑን ጠቅሰው፤ በውጭ ያለችዋ ቤተክርስቲያን ለዘመናት ተከፍላ በእንግልት የቆየች በመሆኗ በዚህ ደረጃ አንድነት ተፈጥሮ መታየቱ የእግዚአብሔር ቸርነት እና ረድኤት ከቤተ ክርስቲያን እንዳልተለየ ያሳያል ብለዋል።

በጉባኤው ላይም ሊቀ ጠበብት ጥበብ ይኄይስ ዕለቱን የተመለከተ ያሬዳዊ ዝማሬ ያቀረቡ ሲሆን፤ በመልአከ ሰላም ጥዑመ ልሳን ለብጹነታቸው ቅኔ ቀርቧል። እንዲሁም መርሀግብሩን በማኅበራዊ ሚዲያ በቀጥታ ሲከታተሉ የነበሩ መጋቤ ምስጢር ሰሎሞን ተስፋዬ ከኦስተን ቴክሳስ (Austin,TX) ተጨማሪ ዘአምላክየ እና ጉባኤ ቃና ቅኔ በጽሑፍ ልከው በመጋቤ ወንጌል መምህር ኤልያስ ቀርቧል።

በጉባኤው የፍቅር ማዕድ የተደረገ ሲሆን፤በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በሀገረ ስብከቱ ያሉ ሁሉንም አድባራትና ገዳማትን አመስግነው፤ ይህንን መርሀግብር በማስተባበር በትጋት የሰሩትን የሦስቱም ስቴት ሊቃነ ካህነትንና ኮሚቴውን አመስግነው፤ ይህ የሚደረገው መርሃግብር የቤተ ክርስቲያን ትውፊትን መሠረታ ያደረገ ሲሆን ይህንኑ ሳይለቅ በባዕድ ምድር መደረጉ የቤተ ክርሰቲያን ክብር ከፍ አድርጎ የሚያሳይ ብሎም ተተኪው ትውልድ ይህንኑ የአባቶችን ሃይማኖት፤ ሥርዓት እና ትውፊትን ይዞ ለመሄድ ፈርቀዳጅ ዝግጅት መሆኑን በመጥቀስ፤ ይህ የአብያተ ክርሰቲያናቱ ህብረት እና ፍቅር እንዲቀጥል ሁላችንም አብረን ከሀገረ ስብከቱ ጋር ልንሰራና የቤተ ክርሰቲያናችንንም አገልግሎት ለሁሉ እንዲዳረስ የበኩላችንን መንፈሳዊ ግዴታን እንድንወጣ አባታዊ ምክር እና ቡራኬ ሰጥተው ጉባኤው በጸሎት ተጠናቋል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

01/27/2026
01/15/2026
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችኹ!!
01/13/2026

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችኹ!!

የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ዻዻስ ለብፁዕ አቡነ ፋኑኤል የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዐል አስመልክቶ የአንኳን አደረሰዎ መርሀ...
01/18/2025

የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ዻዻስ ለብፁዕ አቡነ ፋኑኤል የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዐል አስመልክቶ የአንኳን አደረሰዎ መርሀ ግብር በትላንትናው ዕለት ጥር ፰:፳፻፲፯ ዓም በደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል አዳራሽ አከናውኗል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የአድባራት አስተዳዳሪዎች የሀገረስብከቱ የአስተዳደር ጉባኤ አባላት የግዛት ቤተ ክህነት አመራር አባላት ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ተገኝተዋል።

በጉባኤው ላይ ሊቃውንተ ቤተክርሰቲያን ቅኔና ያሬዳዊ ዝማሬን ያቀረቡ ሲሆን የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ እና ዋና ፀሐፊ መልእክት አስተላልፈዋል።

ዋና ስራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን ዶር ዘበነ ባስተላለፉት መልእክት የካህናት ለእግዚአብሔር መለየት በዓላማ የሆነ እና ካህናትም ይህንን የኖላዊነትን ተግባር በቅንነት ስርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመጠበቅ እና በማስጠበቅ መንፈሳዊ ዓላማን ማስፈፀም እና አርአያነትን ለቤተ ክርስቲያን ምእመናን ማሳየት ይገባል ብለዋል በተመሳሳይ ሁኔታ የሀገረ ስብከቱ ዋና ፀሐፊ መልአከ አርያም በበኩላቸው ይህ የእንኳን አደረስዎ መርሀ ግብር ሁላችንም ቡራኬን የምንቀበልበት እና በቅርበት ስለ ቤተ ክርስቲያን ሰላም እና አንድነት የምንወያይበት መልካም አጋጣሚ መሆኑን አወስተው በሀገረ ሰብከቱ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ከኪራይ በመውጣት የራሳቸውን ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በመግዛት የተሻለ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን አውስተው አንዳንድ ስርዐተ ቤተ ክርስቲያንን ያልጠበቁ ክንውኖች መከሰታቸውን ጥቆማ ለሀገረ ስብከቱ መድረሱን ገልፀው ተጨማሪ መረጃን ለማግኘት ብሎም ወደፊት ተመሰሳሳይ ችግሮች እንዳይከሰቱ ሀገረ ስበከቱ በመፍትሄ ዙርያ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በአንዳንድ የደብር አለቆች ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የጣሰ ድርጊት መፈጸሙን አውስተው ሀገረ ስብከቱ ይህን በዝምታ እንደማያልፈው ገልጸው ለድርጊቱ ፈጻሚዎችም ሆነ ከዚህ በኋላ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ለሚጥሱ ሌሎች ካህናትም አስተማሪ የሚሆን ቀኖናዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቀዋል።

በተጨማሪም በዋሽንግተን ሜትሮ ፖሊታን አካባቢ ከዚህ በፊት በዋናነት ባሉ ታቦታት አዲስ ቤተ ክርስቲያን መትከልም ሆነ መደረብ ከዚህ በኋላ እንደማይፈቀድ ዳሩ ግን በተደራቢነት ካሉት በዋናነት ከሌሉ በእነርሱ ስም አዲስ ቤተ ክርስቲያን ለመትከል ለሚቀርብ ጥያቄ መመሪያውን መሠረት አድርጎ ፈቃድ እንደሚሰጥ ገለጻ አድርገዋል ጉባኤውም ውሳኔው ተገቢ መሆኑን በጭብጨባ አጽድቋል።ወደ ሀገረ ስብከቱ በተለያየ ጉዳይ የሚመጡ ብፁዓን አበውን የለ ሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ እውቅናና ፈቃድ መጋበዝና ክህነትን እንዲሾሙ የመዓርግ ስም እንዲሰይሙ በሚያደርጉት ላይ ቀኖናዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አበክረው አስገንዝበዋል። ለዚሁም ደግሞ በየአድባራቱ ያሉ አገልጋይ ካህናት እና በዋናነት የሀገረ ስብከቱ ጽቤት እንደሚሰራ እና ተጨማሪ መመሪያ እንዲያወጣ በጉባኤው ሀላፊነት ተጥሎበታል።

ጉባኤው ከመቸውም በላይ ለሀገረስብከቱ አንድነት ሁነኛ መፍትሄዎችን ያሳለፈበት እና በርካታ አበው የተገኙበት ነበር። የዚህን ዝግጅት ወጪ አድባራቱ ለሀገረ ስብከቱ መንበረ ዽዽስና መግዣ ዳጎስ ያለ ወጪ ማውጣታቸውን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ከካህናት እና ከአድባራቱ ለዚህ በአል ወጪ ሳይጠየቅ እነዲታለፍ በማሰብ ወጪውን የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት የሸፈነ ሲሆን፥ ከዚህ በኋላ በሚኖሩት በዓላት ላይ ግን አብያተ ክርስቲያናቱ አስተዋጽኦ በማድረግ እንደሚሸፍኑት የተገለፀ ሲሆን ይህንን አስመልክቶ በጽ/ቤቱ መመሪያ እንደሚሰጥበት በመርሀ ግብር መሪው ተገልጾ በብፁዕ አባታችን ቡራኬና ፀሎት መርሀ ግብሩ ተጠናቋል።

በሜሪላንድ ግዛት በሐይትስቪል ከተማ የምትገኘው የኆኅተ ምሥራቅ ኪዳነ ምሕረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሕንጻ ቤተ ክርስቲያንዋ አጠገብ ያለውን ጠቅላላ ይዞታው 13 ኤከር...
12/17/2024

በሜሪላንድ ግዛት በሐይትስቪል ከተማ የምትገኘው የኆኅተ ምሥራቅ ኪዳነ ምሕረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሕንጻ ቤተ ክርስቲያንዋ አጠገብ ያለውን ጠቅላላ ይዞታው 13 ኤከር የሆነና በላዩ 2.27 ኤከር ሕንጻ ያረፈበትና ከ750 በላይ መኪና ማቆሚያ ያለውን የቀድሞ ኬማርት ሕንጻን በዛሬው ዕለት የዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፣ የግዛት ቤተ ክህነቱ የሥራ ኃላፊዎች፣ የአድባርት አስተዳዳሪዎችና የደብሩ ካህናትና ምእመናን እንዲሁም የአበዳሪው ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት በተገኙበት የመጨረሻው የግዢ ፊርማ ስነ ሥርዓትና የንብረት ርክክብ ተፈጽሟል።

Address

6509 Riggs Rd
Hyattsville, MD
20782

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EOTC Maryland Diocese posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to EOTC Maryland Diocese:

Share