07/08/2026
🙏🙏🙏🙏🙏🙏
✝️"ተፈሥሑ ለእግዚአብሔር ዘረድአነ፤
ወየብቡ ለአምላከ ያዕቆብ"
✝️"በረድኤታችን በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፥ለያዕቆብም አምላክ እልል በሉ"
መዝሙር 81:1
✝️የተወደዳችሁና የተከበራችሁ በWashington DC, Maryland እና Virginia የምትኖሩ ካህናት, ዲያቆናት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አጋልጋዮችና ምእመናን በሙሉ፤
በቅርቡ በአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ቸርነት፣ በቅድስት ጽዮን ማርያም አማላጅነት፣ በጻድቁ አቦ ረድኤት፣ በሁላችሁም ጸሎትና ድጋፍ የገዛነው ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ለመመረቅና ታቦታቱን ለማስገባት የሚቀጥሉት መርሃ ግብሮች ወጥተዋል፡
✝️ቅዳሜ ሐምሌ 4 (Saturday July 11) ከ6am እስከ 10am
ታቦታቱ አሁን ካለንበት ወደ አዲሱ ቤተ ክርስቲያን መውሰድና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ተገቢውን ጸሎትና ሥርዓት ፈጽሞ ቤተ ክርስቲያንዋ ለቅዳሴ ቤቱ ለእሁድ ማዘጋጀት።
✝️እሁድ ሐምሌ 5 (Sunday July 12) ከ6am እስከ 11am
ቅዳሴ ቤቱን በታላቅ ድምቀት ማክበር።
✝️ማክሰኞ ሐምሌ 7 (Tuesday July 14) ከ6am እስከ 11am
የሐምሌ ሥላሴ በዐለ ንግሥ በእለቱ ማክበር።
ከላይ በተጠቀሱት እለታትና ሰዓታት በመምጣት የእነዚህ ታላላቅና ታሪካዊ በዐላት ተሳታፊ ትሆኑ ዘንድ መንፈሳዊ ጥሪያችንን በአክብሮት እናስተላልፍላችኋለን።
ሊ/ኅ ቀሲስ ይስሐቅ ወልደ ማርያም፣ የደብሩ አስተዳዳሪ
✝️አድራሻ፡
3245 Glen Carlyn Rd Falls Church, VA 22041
✝️ለበለጠ መረጃ (703) 606-1976