03/24/2026
ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ለዴንቨር ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን:-ምእመናን እና ወዳጆች በሙሉ፤ቤተ ክርስቲያናችን ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ስብሐተ እግዚአብሔርና ስብከተ ወንጌል ሳይታጎልባት፥ ሳትከፈልም ለምእመናን የልብ ማረፊያ፥ለልጆችም በሥነ ምግባር መታነጫ፤ሃይማኖታቸውን፥ ሥርዓታቸውንና ትውፊታቸውን መማሪያ፤ ለመንፈሳዊውም ባሕላችን መጠበቂያ ሆና በማገልገል ላይ ትገኛለች።ከዚህም የተነሣ በአራቱም ማዕዘን የምትናፈቅ ናት።ሆኖም እስከ ዛሬ እየተገለገልንበት ያለው ሕንፃ ቤተ መቅደስ በጣም ስለ ጠበበን በገዛነው መሬት ላይ:-
፩ኛ:-ሰፋ ያለ ቤተ መቅደስ፤ ፪ኛ:-ሁለ ገብ አዳራሽ፤ሦስተኛ የልጆች ት/ቤት ለመሥራት ቆርጠን ተነሥተናል።ለዚህም የነፍስ ሥራ ዓለም አቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጅተናል።ቅዱስ መጽሐፍ:-“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፤”እንዲል:-እኛን ለማገዝ የምታደርጉት ጥቂት ነገር ብዙ ሥራ ይሠራል ብለን እናምናለን።ይልቁንም ከሁሉ በሚበልጠው ጸሎታችሁ እንድታግዙን በአምላካችን በመድኃኔዓለም ስም መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ፪ኛ:ቆሮ:፱፥፯።ደግሞም ቤተ ክርስቲያን ካህናት የምትቀድሱባት፥ምእመናን የምትቆርቡባት የጋራ ቤታችን ናት።የመድኃኔዓለም ቸርነት፥የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን።
The name of the parish church is Denver Debreselam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. Denver Debreselam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo ...