Bete Tekle

Bete Tekle Bete Tekle is an online school for the Ethiopian Orthodox Tewahedo believers.

https://youtu.be/PXcLgff8A4I?si=aXvfQGJuBI79ZFAY
08/03/2025

https://youtu.be/PXcLgff8A4I?si=aXvfQGJuBI79ZFAY

ዛሬ እጅግ ልዩ የሆነ ቪዲዮ ይዘንላችሁ ቀርበናል! የብዙዎችን ሕይወት በትምህርታቸው የቀየሩት፣ የአእምሮና የነፍስ ብርሃን የሆኑት የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን መምህር የሆኑት ታ.....

ያሁኑ ይባስ!ሰላም ለመልክእኪ እመልክአ ሐና ወኤልሳቤጥ::ዘብዑድ ስኑ ወልምላሜሁ ፍሉጥ::ማርያም ቅድስት ድንግልተ አፍኣ ወውስጥ::ቤዛ ይኩነኒ ኪዳንኪ በገጸ ፈጣሪ ሥሉጥ::አመ ወርኀ ነጊድ የ...
04/24/2025

ያሁኑ ይባስ!
ሰላም ለመልክእኪ እመልክአ ሐና ወኤልሳቤጥ::
ዘብዑድ ስኑ ወልምላሜሁ ፍሉጥ::
ማርያም ቅድስት ድንግልተ አፍኣ ወውስጥ::
ቤዛ ይኩነኒ ኪዳንኪ በገጸ ፈጣሪ ሥሉጥ::
አመ ወርኀ ነጊድ የሐልቅ ወይጸራዕ ሤጥ::
ነገረ አበዊነ!
የአባቶቻችን ጉዳይ ዝም ብለን ልናየው የሚገባ አይደለም::
ዝም ባልን ቁጥር የእነሱንም የቤተ ክርስቲያኒቱንም ውድቀት እያፋጥን እንደሆነ ይሰማኛል::
ጥቂቱ ለማስታወስ ያህል::
1/ ከቀኖና ውጭ ሁለት ሲኖዶስ ሲያቁዋቁም ዝም አልናቸው ከሐዋርያት ቀኖና ጋር ተቃራኒ የሆነ ሢመት ሲፈጽሙም ዝም አልናቸው እኛም በተለያየ መንገድ ተከፋፍለን አብረን ስናጠፋ ከረምን::
2/ እልሃቸው በረድ ሲልላቸው ታረቅን አሉ ስለተጣሰው ቀኖና ምንም ማብራሪያ ሳይሰጡ ተቀላቀሉ ዝም አልን::
3/ በየመንደሩ የከብረውን ሢመተ ክህነት ሲያዋርዱ ዓለም ዐቀፍ የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን የመንደር ሲያደርጉአት ዝም አልን:: ይሄ ጉዳይ እንደ ቀላል የምናልፈው መሆን የለበትም ለምሳሌ: የኦሮሚያ የትግራይ የቅባት ጳጳሳት ነን ባዮች በሀገራችን እንደ ልባቸው እየተንቀሳቀሱ እሱዋ ያልተነሳች ልታቁዋቁም መጣች እንዲሉ አበው በሌላቸው ክህነት ክህነት እንሰጣለን እያሉ በቤተ ክርስቲያን ላይ ሲቀልዱ ዝም አልን::
4/ አጥማቂ ነን የሚሉ መጥቁሎችን ባደባባይ እያሞገሱ ቤተ ክርስቲያንን የሲሞናውያን መቀለጃ ሲያደርጉአት ዝም አልን::
5/ በኛ ዝምታ ራሳቸውን እንደፈጣሪ ከቆጠሩት (አነ ፈጠርኩክሙ) ለማለት በዝግጅት ላይ ያሉት አባቶቻችን ምን ታመጣላችሁ በሚመስል መልኩ ትምህርተ ኑፋቄን በአደባባይ የቤተ ክርስቲኒቱ መሠረት የሆነው ነገረ ትስብእትንና ነገረ ማርያምን መናድ ጀመሩ:: በኛ ቤተ ክርስቲያን ካልገባን ከመምህራን ይጠየቃል ከመምህራን መልስ ካልተገኘም ሱባኤ ይያዝበታል እንጂ ብድግ ብሎ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት የተደረሱትን ከዚያም አልፎ የዘወትር ሥርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ የሆኑትን መጻሕፍት ብድግ ብሎ ትክክል አይደሉም ማለት ከስህተትም በላይ ስህተት ነው:: መረጋጋት ማንን ገደለ የሆነ ትምህርት ተምረዋል ማለት ጠቅላላ የቤተ ክርስቲያኒቱን ዕውቀት ጠንቅቀዋል ማለት አይደለም:: ይህን ሁሉ ያመጣው ግን የኛ ዝምታ ነው አንድ የቀረችን ሃይማኖታችን ናት ዝም ብለን አባቶች ያሉትን ነው የምንቀበል እያልን የመጨረሻ መጠጊያችን አፍርሰው መጠለያ እንዳያሳጡት በጊዜ እባካችሁ ተውን ልንላቸው ይገባል:: ይተው አንጅ! እመቤታችንማ ቤዛችን ናት ቅዱሳንማ ቤዛዎቻችን ናቸው ቤዛ ሲያሳጡን ለምን አንደነግጥም?
እጅግ የሚያሳዝነው የስቅለት ዕለት ሕዝበ ክርስቲያኑ ሁሉ በተመስጦ በሚውልበት ቀን መሆኑ ነው:: ለመሆኑ የስቅለት ቀን በአዳራሽ ጉባኤ የሚደረገው በምን ምክንያት ነው? በሀገራችን ስቅለት ብሔራዊ በዓል ስለሆነ ሥራ ዝግ ነው ያ ሁሉ ሕዝብ ቤተ ክርስቲያን መዋል ሲገባው እንዴት እዚያ ተገኘ? ይሄ ራሱ ሌላ ስህተት አይደለም ወይ?
ምንተ ንግበር ሊቃውንት ካህናት ዲያቆናት ምእመናን ወምእመናት! አሁንም ዝም እንበል?
መልሱን ለእናንተ እተዋለሁ!!

ይህ ታላቅ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ላይ ቀጥታ ውይይት ስለሚጀምር እንዳያመልጠዎ ለወዳጅ ቤተሰብዎ ሊንኩን ያጋሩ።
04/11/2025

ይህ ታላቅ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ላይ ቀጥታ ውይይት ስለሚጀምር እንዳያመልጠዎ ለወዳጅ ቤተሰብዎ ሊንኩን ያጋሩ።

ይምላዕ ስብሐቲሁ ኩሎ ምድረ ምስጋናው ምድርን ሁሉ ይምላ። ነቢየ ጽድቅ ዳዊት ከመንግሥታዊ ተልዕኮው በበለጠ ለመንፈሳዊ ቅንዓት የነበረው ቦታ በእጅጉ የተለዬ ነበር ለዚህም ነው መቶ ሃምሳ መዝ...
03/28/2025

ይምላዕ ስብሐቲሁ ኩሎ ምድረ
ምስጋናው ምድርን ሁሉ ይምላ። ነቢየ ጽድቅ ዳዊት ከመንግሥታዊ ተልዕኮው በበለጠ ለመንፈሳዊ ቅንዓት የነበረው ቦታ በእጅጉ የተለዬ ነበር ለዚህም ነው መቶ ሃምሳ መዝሙሮች ያሉትን በስሙ የሚጠራውን የምስጋና ድርሰት ከትውልድ ወደ ትውልድ ላይቋረት የማይቋረጥ ዥረት አድርጎ ያፈለቀልን።
ይኸውም ሊታወቅ ማኅሌት ብንቆም በዳዊት ድርሰት(ስንጀምር ስምአኒ)፣ ሰአታት ብንቆም በዳዊት ድርሰት(ግነዩ ለእግዚአብሔር)፣ ቅዳሴ ብንቀድስ በዳዊት ድርሰት(ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር)፣ ሁሉም ጸሎታችን በዳዊት ድርሰት የሆነው።
እርሱ ለልጆቹ ለእኛ ከሰጠን መመሪያ አንዱ ይምላዕ ስብሐቲሁ ኩሎ ምድረ ለይኩን ለይኩን፣ ምስጋናው ዓለምን(ምድርን) ሁሉ ይምላ ይሁን ይሁን ይላል መዝ 71፧19
ይህ ትእዛዝ እስከ ዓለም ፍጻሜ የሚጸና የሁላችን ትእዛዝ መሆኑን የተረዳንም በዓለም ሁሉ ማኅሌት እንዲቆም፣ ሰዓታት፣ እንዲቆም፣ ቅዳሴ እንዲቀደስ የአባታችንም ትእዛዝ እንዲከበርና እንዲያከብረን በዚህ ውይይታችን ላይ በዖንላይን ተገኝተው ጉባኤ ቤታችን እየገነባው ባለ ኢንተርናሽናል እስኮለርሽፕ ግንባታ ላይ የበኩልዎን አስተዋጽኦ እንዲያበረከቱ በጉባኤው ባለቤት በመድኃኔ ዓለም ተጠርተዋል። መድኅኑ ይፍቀድልዎ።
መምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ

02/28/2025
ክፍል ፪ልዩ ውይይት        መምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ         ሊቀ ጠበብት  Tekle Worete        ዲ/ን  ሄኖክ ኃይሌስለ ደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔ ዓለም የዐራ...
10/01/2024

ክፍል ፪
ልዩ ውይይት
መምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ
ሊቀ ጠበብት Tekle Worete
ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
ስለ ደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔ ዓለም የዐራቱ መጻሕፍተ ጉባኤ ቤት በቤተ ተክሌ ሁላችሁም በክብር ተጋብዛችሁአል::

09/11/2024

እንኳን ከዘመነ ቅዱስ ዮሐንስ ፳፻፲፮ ወደ ዘመነ ቅዱስ ማቴዎስ ፳፻፲፯ ዓ.ም. በሕይወት፣ በጤና፣ በሰላም አሸጋገረዎ!

ዐዲሱ ዘመን በጎ ሥራ የምንሠራበት የምሕረት፣ የሰላም ዘመን ያድርግልን።

05/28/2024

Address

Dallas, TX
75243

Opening Hours

Thursday 12pm - 2pm
Saturday 2pm - 4pm

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bete Tekle posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Bete Tekle:

Share