Kesis Yared Gebremedhin የያሬድ ቤት

Kesis Yared Gebremedhin  የያሬድ  ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Kesis Yared Gebremedhin የያሬድ ቤት, Religious organisation, Columbus, OH.

05/09/2026
የሩጫ ጊዜ በክብር ተጠናቀቀ ። ድካም  ውጣ ውረድ ቦታውን ለዘላለም ዕረፍት አስረከበ ።እነሆ ክረምት አለፈ ዝናብም አልፎ ሔደ የዜማም ጊዜ ደረሰ ።ወንድሜ ዲያቆን ዘላለም በብዙ ድካም ያገለገ...
03/08/2026

የሩጫ ጊዜ በክብር ተጠናቀቀ ። ድካም ውጣ ውረድ ቦታውን ለዘላለም ዕረፍት አስረከበ ።እነሆ ክረምት አለፈ ዝናብም አልፎ ሔደ የዜማም ጊዜ ደረሰ ።

ወንድሜ ዲያቆን ዘላለም በብዙ ድካም ያገለገልከው አምላክ የወይኑ እርሻ ባለቤት የድካምህን ዋጋ ሊከፍልህ እንደጠራህ እናምናለን ። እርሱ አምላካችን በክብር ተቀብሎ በዘላለም ቤቱ ያሳርፍልን ።

" ከዚህ በኋላ አየሁ፥ እነሆም፥ አንድ እንኳ ሊቆጥራቸው የማይችል ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ነጭ ልብስም ለብሰው የዘንባባንም ዝንጣፊዎች በእጆቻቸው ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆሙ፤ በታላቅም ድምፅ እየጮሁ። በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው ለአምላካችንና ለበጉ ማዳን ነው አሉ። መላእክቱም ሁሉ በዙፋኑና በሽማግሌዎቹ በአራቱም እንስሶቹ ዙሪያ ቆመው ነበር፤ በዙፋኑም ፊት በግምባራቸው ተደፉ፥ ለእግዚአብሔርም እየሰገዱ።አሜን፥ በረከትና ክብር ጥበብም ምስጋናም ውዳሴም ኃይልም ብርታትም ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ለአምላካችን ይሁን፤ አሜን አሉ ። " ( ራእ ዮሐ ፯-፱ )

" ይህ ናፍቆቴ ተስፋዬ ነውና ባንድ ነገር እንኳ አላፍርም ። ነገር ግን በሕይወት ብኖር ወይም ብሞት ክርስቶስ በግልጥነት ሁሉ እንደ ወትሮ በሥጋዬ ይከብራል። ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ሞትም ጥቅም ነውና....ልሔድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ፣ ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና " ( ፊልጵ ፩ ፥ ፳ )

03/08/2026

ከሠላሳ ዓመታት በላይ ከገጠር እስከ ከተማ ከሀገር ውስጥ እስከ ዓለም ሀገራት ወንጌልን ሲዘራ በታማኝነትና በትጋት ያለዕረፍት ያገለገለው መምህር ዘለዓለም ወንድሙ ከድካመ ሥጋ አርፏል።
በመምህራችን ህልፈት የቤተ ያሬድ ሚዲያ የተሰማንን ኀዘን እንገልፃለን። ለቤተሰብ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለመላው ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።

ኑ ወደ  ገዳም ወደ በረሃ እንውረድጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ በአስቸጋሪው በረሃማ ሥፍራ ከቆመበት ሳያርፍ  ከዘረጋበት ሳያጥፍ  አርባ መዐልት እና አር...
03/06/2026

ኑ ወደ ገዳም ወደ በረሃ እንውረድ

ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ በአስቸጋሪው በረሃማ ሥፍራ ከቆመበት ሳያርፍ ከዘረጋበት ሳያጥፍ አርባ መዐልት እና አርባ ሌሊት ጾሟል። በዚህም ለአዳም እና ለሔዋን በሦስቱ አርእስተ ኃጣውእ ( ስስት ፣ ትዕቢት ፣ ፍቅረ ንዋይ ) ዲያቢሎስን ድል ነሥቶላቸዋል ። አንድም ሠራዔ ሕግ ነውና ጾምን መጀመሪያ ሕግ አደርጎ ሥራውን በጾም ጀመሯል ። አንድም አዳም በአርባ ቀን ያገኘውን ልጅነት አስወስዶ ነበርና ለሱ እንደካሰ ለማጠየቅ ጌታችን ጾሟል ። አንድም ጠላትን በጾም በጸሎት ድል ማድረግ እንደሚቻል አስተምሮናል ። እናንተም አርባ መዐልት ወአርባ ሌሊት ብትጾሙ ምስጢር ይገለጥላችኋል ተሐድሶተ ነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ለጾሞ አርአያ አብነት ሆኖናል
( ማቴ ፬ ፥ ፩ ) ።

እንዲህ ባለው የጾም የጸሎት ወቅት እኛም ጌታችንን አብነት አድርገን ወደ ገዳም ወደ በረሃው መውረድ ይገባናል ። ብቻችንን ወደ ምንሆንበት በረሃ ። ራሳችንን ወደ ምናደምጥበት በረሃ ጭልጥ ብለን መሄድ አለብን ። ለተፈቀደላቸው ይህ በረሃ ዋልድባ ፣ ማኅበረ ሥላሴ ፣ ደብረ ሊባኖስ ፣ ዝቋላ ፣ አሰቦት ፣ራማ ኪዳነ ምሕረት ...... ነው ። የታደሉ ነፍሳት በእነዚህ በረሃማ ሥፍራዎች በገዳም ተሰብስበዋል ። ፈጣሪን ብቻ እያሰቡ ለእርሱ ብቻ እየኖሩ ነው።

በዓለም የምንኖር ደግሞ ኪዳን እያደረስን ፣ ቅዳሴ እያስቀደስን ፣ በዓውደ ምሕረት የሚነገረውን ቃሉን እየሰማን ወደ ልባችን በረሃ እንሰደድ ። ከራሳችን ጋር ብቻ ለማሳለፍ ይህን ዓለም ወደ ጎን ትተን በልባችን በረሃ እንቀመጥ ። ኋላም ብቻችንን እንሆናለን ። ሁሉን ጥለን እናልፋለን ። ስለዚህ ዛሬ ብቸኝነትን አንፍራው ። ከራሳችን ጋር መሆናችንን አንፍራው ። በእርግጥም ግርግር ለለመደ ይህ ከባድ ነው ። ነገር ግን ኃይልን በሚሰጠን በክርስቶስ ሁሉ ይቻላልና ( ፊል ፬ ፥ ፲፫ ) በልባችን በረሃ እንከተት ።

በዓለም ፍቅር የነደደ በረሃማው ልባችን ለመጠጊያነት ምቹ ላይሆን ይችላል ። ዲያቢሎስ በልባችን ያኖረው የዚህ ዓለም አምሮት እና ፈቃድ ፈተና ሊሆንብን ይችላል ። ነገር ግን ጨክነን ከተሸሽግን ፣ ፈተናውን ታግሰን በጾም በጸሎት ከጸናን ፣ ልባችን እንደ ገዳመ ቆሮንቶስ እንደዋልድባ የቅድስና የበረከት መመላለሻ መዳረሻ ወደብ ይሆናል ። እንደ ግብጽ ገዳማት በእናት እና ልጅ ይባረካል ። አስኬጥስ ገዳምን መምሰል ይጀምራል ።

" የልቡን ተዘክሮ ሁል ጊዜ ወደ እግዚአብሔር የሚያደርግ ። በመረዳት በተስፋ ጸንቶ ከበአት ያለመውጣት ከሰው ጋር ያለመጫወት በጽማዌ ሁኖ እግዚአብሔርን የሚዘከር ። መሻቱን የሚያውቅ ጌታ ከሱ በሚገኝ ጥበብ ዐዋቂ ያደርገዋል ። ከእግዚአብሔር በሚገኝ በማያልፍ ክብር በልቡናው ደስ ይለዋል " ( አረጋዊ መንፈሳዊ ድርሳን ፴፪ ) ።

ኑ እንውረድ ወደ በረሃው ልባችን እንሰደድ ከራሳችን ጋር እንነጋገር ። የንስሐ ዕንባ አንብተን ፣ ፈጣሪን ይቅርታ ጠይቀን ከጨለማ ወደ ብርሃን እንሸጋገር ።

ቀሲስ ያሬድ ገብረ መድኅን
( ኮለምበስ ኦሀዮ )

Address

Columbus, OH

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kesis Yared Gebremedhin የያሬድ ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Kesis Yared Gebremedhin የያሬድ ቤት:

Share