Menbere Tsebaot Holy Trinity EOTC Virginia መንበረ ፀባዖት ቅ/ሥላሴ ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቨርጅንያ

  • Home
  • United States
  • Chantilly, VA
  • Menbere Tsebaot Holy Trinity EOTC Virginia መንበረ ፀባዖት ቅ/ሥላሴ ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቨርጅንያ

Menbere Tsebaot Holy Trinity EOTC Virginia መንበረ ፀባዖት ቅ/ሥላሴ ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቨርጅንያ ይህ በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት የቨርጅንያ መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ገጽ ነው።
(1)

06/13/2026

ታላቅ የቅድስት ሥላሴ ወርሃዊ በዓልና ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ!!!

በቨርጂንያ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ (ቻንቲሊ፣ ቨርጂንያ)

እሁድ በዕለተ ቅድስት ሥላሴ!

በማህሌት፣ በቅዳሴ፣ በትምህርተ ወንጌል፣ በዝማሬና በሌሎችም ልዩ ልዩ መንፈሳዊ አገልግሎት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ይውላል።

በዕለቱ በቅድስት ሥላሴ ጠበል መጠመቅ ለሚፈልጉ የፈውስ ጥምቀት አገልግሎት ይሰጣል!

እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓም (June 14, 2026)

በዕለተ ቅድስት ሥላሴ፤ ከሥላሴ ደጅ በፍፁም አይቀርም!

መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን (ቻንቲሊ፣ ቨርጂንያ)

📅 Sunday, June 14, 2026

⏰ Time: 3 AM-10 AM

📍 Location: 14595 Avion Pkwy, Chantilly, VA 20151

📞 Contact: +1 (571) 776-6519 ✉️ Email: [email protected]

የቅድስት ሥላሴ ምህረት፣ ይቅርታና ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን!!!

05/30/2026
" "+++++++++++++++++++++++++++++"አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።" ዮሐ 14፥26በ...
05/29/2026

" "
+++++++++++++++++++++++++++++
"አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።" ዮሐ 14፥26

በኢ/ኦ/ተ/ቤተ/ክ በዋሽንግተን ዲሲ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት፣ የቨርጂንያ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ/ክ።

ለበለጠ መረጃ:

+1 (571) 776-6519 ይደውሉ
Email: [email protected]

የቨርጅንያ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሚዲያ ገጾች እና አድራሻዎች:-

FB page 1

https://www.facebook.com/profile.php?id=61574980444871&mibextid=ZbWKwL

FB page 2

https://www.facebook.com/share/16ZAdbj451/

FB page 3

https://www.facebook.com/share/1AafNiRz56/


https://youtube.com/channel/UC3j7G8IKmDu8mkanZw6YGwQ?si=YdDYzv5MOS0LqAqb


https://t.me/+7GMEc-Bl9LkzNTlh


https://menberetsebaotholytrinityeotc.org/


Menbere Tsebaot Holy Trinity EOTC _VA

#አድራሻ:- 14595 Avion Pkwy, Chantilly, Virginia 20151

ዓረገ ውስተ አርያም ፄዊወከ ፄዋወወሀብከ ፀጋከ ለዕጏለ እመሕያው እስመ ይክህዱ ከመ ይሕድሩ                          በዓለ ዕርገትመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ፣ የኢትዮጵያ ኦር...
05/23/2026

ዓረገ ውስተ አርያም ፄዊወከ ፄዋ
ወወሀብከ ፀጋከ ለዕጏለ እመሕያው
እስመ ይክህዱ ከመ ይሕድሩ

በዓለ ዕርገት

መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን (ቻንቲሊ፣ ቨርጂንያ)

በፀሎተ ኪዳን፣ በቅዳሴ፣ በትምህርተ ወንጌልና በዝማሬ

📅 Sunday, Date: May 24, 2026

(እሁድ፣ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ/ም)

⏰ Time: 5 AM-10 AM

📍 Location: 14595 Avion Pkwy, Chantilly, VA 20151

📞 Contact: +1 (571) 776-6519

✉️ Email: [email protected]

05/16/2026
05/15/2026

የቅድስት ሥላሴ ወርሃዊ በዓል!

May 17, 2026

14595 Avion Pkwy, Chantilly, VA 20151

ምሥጢረ ሥላሴ በቀደምት አባቶቻችን:-“አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በአካል ሦስት በባህርይ አንድ ነው ብሎ ማመን ይህ ነው፤ የማይመረመር በቅድምና የነበረ አብ በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤…የማይመረ...
05/15/2026

ምሥጢረ ሥላሴ በቀደምት አባቶቻችን:-

“አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በአካል ሦስት በባህርይ አንድ ነው ብሎ ማመን ይህ ነው፤ የማይመረመር በቅድምና የነበረ አብ በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤…የማይመረመር በቅድምና ነበረ ወልድም በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤….የማይመረመር በቅድምና የነበረ መንፈስ ቅዱስም በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤ ሐዋርያት ያስተማሩዋት ቅድስት ቤተክርስቲያን የተቀበለቻቸው ቅዱሳት መጻሕፍት እንደተናገሩ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቄርሎስ ምዕራፍ 70፡14-17)

“እግዚአብሔር አንድ ነው፤ የማትከፈል የማትፋለስ መንግስትም አንዲት ናት፤ ከሥላሴ ምንም ምን ፍጡር ደኃራዊ የለም፤ በእነርሱ ዘንድ አንዱ ለአንዱ መገዛት የለም፡፡ አብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፣ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፤ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፤ ሥሉስ ቅዱስ በዘመኑ በቀኑ ሁሉ በግብርም በስምም ሳይለወጥ ሳይፋለስ ጸንቶ ያለ ነው እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘሠለስቱ ምዕት ምዕራፍ 19፡5-6)

“ወንድሞቻችን እኛስ እንዲህ እናምናለን፤ ያልተወለደ እግዚአብሔር አብ በተለየ አካሉ አንድ ነው፤ የተወለደ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስም በተለየ አካሉ አንድ ነው፤ በወደደው የሚያድር የአብ የወልድ እስትንፋስ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም በተለየ አካሉ አንድ ነው እንላለን፡፡…አብ አምላክ ነው፤ ወልድም አምላክ ነው፤ መንፈስ ቅዱስም አምላክ ነው፡፡ ግን ሦስት አማልክት አይባሉም አንድ አምላክ እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ምዕራፍ 25፡2-4)

“ከሦስቱ ፍጡር የለም ፍጡራን አይደሉምና፡፡ ከዕውቀት ከሃይማኖት የተለዩ መናፍቃን ከቅድስት ሥላሴ መለኮት መከፈልን በአካላት መጠቅለልን ሊያመጡ አይድፈሩ ሦስት አማልክት ብለን አንሰግድም አንድ አምላክ ብለን እንሰግዳለን እንጂ፡፡ በስም ሦስት ናቸው እንላለን፤ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ባህርይ አንድ ሥልጣን ናቸው፤ በአንድ መለኮት በባህርይ አንድነት የጸኑ ሦስት አካላት ሲሆኑ ከሦስቱ አንዱ የሚበልጥ አንዱ የሚያንስ አይደለም፤ በማይመረመር በአንድ ክብር የተካከሉ ናቸው እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ምዕራፍ 60፡6-7)

“ወልድ ሳይኖር አብ ከአዝማን በዘመን ፈጽሞ አልነበረም፤ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ በዘመን አልነበረም፤ ሳይለወጡ ሳይለዋወጡ በገጽ በመልክ ፍጹማን በሚሆኑ በሦስት አካላት ጥንት ሳይኖራቸው በዘመን ሁሉ የነበሩ፤ ፍጻሜ ሳይኖራቸው የሚኖሩ ናቸው እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎፍሎስ ምዕራፍ 68፡5)

“እኛ ግን በሥላሴ ዘንድ በማዕረግ ማነሥና መብለጥ የለም በመለኮት አንድ ወገን ናቸው እንላለን” (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ተግሳጽ ዘሰባልዮስ)

ማጠቃለያ
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምስጢረ ሥላሴን በተረዳ ነገር ‹‹ሥላሴ አንድ ሲሆኑ ሦስት፣ ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸው፡፡ አንድነቱ ሦስትነቱን ሳይጠቀልለው፣ ሦስትነቱ አንድነቱን ሳይከፋፍለው በሕልውና ተገናዝበው የሚኖሩ ናቸው፡፡›› ብላ ታምናለች፤ ታስተምራለችም፡፡ ይህም እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ራሱን የገለጠበት፣ ነቢያት የመሰከሩት፣ ወልደ እግዚአብሔር በተለየ አካሉ ሰው ሆኖ ያስተማረው፣ ሐዋርያትም በዓለም ዞረው የሰበኩት ምስጢር ነው፡፡

ስለዚህ እኛም እንደ አባቶቻችን “ምንም እንኳን ሥላሴን በስም፣ በአካል በግብር ሦስት ናቸው ብንልም ሦስቱ በባህርይ፣ በመለኮት፣ በህልውና፣ በፈቃድ አንድ ናቸው፡፡ አንድ አምላክ እንጂ ሦስት አማልክት አንልም፡፡ አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ አላቸው፡፡ ነገር ግን በህልውና አንድ ናቸው፡፡” ብለን እናምናለን፤ እንታመናለን፡፡

ስብሃት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፡፡ አሜን!!!

የቅድስት ሥላሴ ምህረትና ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን!!!

“ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም፤ በማርያም ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ!” (ቅዱስ ያሬድ) ነቢዩ ኢሳይያስ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ከነገደ ዕሴይ እንደሚሆንና ...
05/08/2026

“ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም፤ በማርያም ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ!” (ቅዱስ ያሬድ)

ነቢዩ ኢሳይያስ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ከነገደ ዕሴይ እንደሚሆንና እርሷም ጽጌ (አበባ) የተባለ አካላዊ ቃል ክርስቶስን በሕቱም ድንግልና እንደምትወልድ ተገልጾለት ‹‹ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ፤ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል›› (ኢሳ11፥1) በማለት ታላቅ ትንቢትን ተናግሮ ነበር፡፡ ይህች በትርም ከእሴይ ዘር የተገኘችው በዚህች ዕለት ነውና ልደቷ በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡

ይህንንም መሰረት በማድረግ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ‹‹መልካሟ ርግብ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፤ ከእሴይ ሥር የተገኘሽ መዓዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ›› በማለት በውዳሴ አመስግኗታል፡፡

የእመቤታችን የድንግል ማርያም ልደት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን (ቻንቲሊ፣ ቨርጂንያ) በታላቅ ድምቀት በልዩ ልዩ መንፈሳዊ አገልግሎት ተከብሮ ይውላል።

ዕርስዎም የዚህ መንፈሳዊ በዓል ተካፉይ ይሆኑ ዘንድ በክብር ተጋብዘዋል።

ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ አሜን!!!

📅 Date: Sunday, May 10, 2026
⏰ Time: 5:00 AM

📍 Location: 14595 Avion Pkwy, Chantilly, VA 20151

📞 Contact: +1 (571) 776-6519

✉️ Email: [email protected]

Address

14595 Avion Pkwy
Chantilly, VA
20151

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Menbere Tsebaot Holy Trinity EOTC Virginia መንበረ ፀባዖት ቅ/ሥላሴ ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቨርጅንያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share