03/18/2020
https://www.facebook.com/735465573315241/posts/1311506852377774/
በስመ አብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
"ወደፈተና እንዳትገቡ ተግታችሁ ፀልዩ "ማቴ.26÷41
በቦስተን እና አካባቢው የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ እንደሚታወቀው በከተማችን በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት መንግስት በአንድ ቦታ ላይ ከ 10 ሰው በላይ መሰብሰብ እንደማይቻል ማስታወቁ ይታወቃል። ይህንንም መሰረት በማድረግ ምንም እንኳን ቤተክርስቲያን የመዳኛ ቦታ መሆኑ ብናቅም ህግን ተከትለን መንቀሳቀሳችን ደሞ ተገቢ በመሆኑ ቤተክርስቲያናችን መንግስት አዲስ የተሻሻለ ህግ እስኪያወጣ ድረስ ለአገልግሎት ዝግ ሆኖ እንደሚቆይ እያሳወቅን ነገር ግን የእለተ ሰንበት አገልግሎት በቀጥታ በቤተክርስቲያንዋ ፌስፑክ ወይም ዩቲውብ የሚተላለፍ መሆኑን መግለፅ እንወዳለን ።
ስለዚህም ቤተክርስቲያንናችን ለአገልግሎት ክፍት እስክትሆን ድረስ ከቤተክርስቲያንዋ የሚተላለፈውን መልእክት የቤተክርስቲያንዋን ፌስፑክ ላይክ ወይም ፎሎው በማድረግ እንድትከታተሉ እና ባላችሁበት ቦታ በፀሎት እና በሱባዔ በመሆን ትቆዩ ዘንድ ቤተክርስቲያን መልእክቷን ታስተላልፋለች።
ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው። 1ኛ ዮሐ 5÷4
የቦስተን መካነ ሕይወት ቅዱስ ሚካኤል ወኪዳነምህረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን