08/15/2025
በጉዲና ቱምሳ ሌጋሲ/ፋውንዴሽን በአድዋ ሙዝየም በተዘጋጀው የሙሉ ቀን ስልጠና ስለ ጊዜ ወይም Reading the Signs of the time"በሚል ርዕስ የተሰጠን ስልጠና እጅግ አስገራሚ ጊዜ ነበረን።ይህንን ስልጠና የሰጡት ዶክተር ለማ ደገፋ,ዶክተር ምህረት ደበበ,ዶክተር ቄስ ሳሙኤል ዮናስ,ዶክተር ገለታ እና ሌሎችም።ቄስ ጉዲና ቱምሳ የምድር ቆይታቸው በጣም አጭር ጊዜ ቢሆንም የሰሩት ሥራ እስከ አሁን እያወራ ነው።የእኝህ ጀግና የእግዚአብሔር አገልጋይ ለብዙዎቻችን ጠቃሚ ትምህርት ሆኖልናል።
"የዘመኑን ምልክቶች ማንበብ የሚለው ቃል ለሁሉም ሰው ወሳኝ መልዕክት ነው።“የእግዚአብሔር ወቅት,ጊዜ ወይም ዘመን”የሚለውን ጽንሰ-ሐሳብ በደንብ አብራርተው አስተምሮናል።ከተማሪነው ውስጥ ጥቅቱን እነሆ።የእግዚአብሔር ጊዜ ወይም ዘመን የሚለው ቃል በግሪክ ቃል እንዲህ ይጠራል,“ካይሮስ” (καιρός)፣ ስሆን እሱም "በእግዚአብሔር የተወሰነ፣ በመለኮት የተወሰነ ጊዜን ወይም ዘመንን ያመለክታል።ይህም ሁነኛና እና ዕድለኛ ጊዜን(Opportune) ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ"ክሮኖስ" (χρόνος) የሚለው ደግሞ ተቆጣሪ እና ተቀማሪ ጊዜ,(Calendar),ሰው የምኖርበትን,በምድር ላይ ያለውን ጊዜ ያሳያል።
የካይሮስ ጽንሰ-ሀሳብ በህይወታችን ውስጥ የእግዚአብሔርን ጊዜ የመረዳት እና የመለየት አስፈላጊነትን የሚያሳይ እና እግዚአብሔር የሰጠንን በአገባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። በክሮኖስ ዙሪያ የተዋቀሩ ዕቅዶች ሊኖረን ቢችልም፣ የእግዚአብሔርን ግብአት መፈለግ እና ካይሮስን ማወቃችን በእሱ ዋና ዓላማ እና ጊዜ ውስጥ እንድንመላለስ ያስችለናል።
ይህ አጠቃላይ እይታ “የእግዚአብሔር ወቅት” በቅዱሳት መጻህፍት ውስጥ የካይሮስን በአማኝ ሕይወት ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔር ዘላለማዊ ዕቅድንና ፕሮግራሙን እንድንረዳ ያስችለናል።እግዚአብሔር ሆይ የአንተ ካይሮስ እንዳያመልጠን አንተ እርዳን።በሰጠን ዘመንና ጊዜ የአንተን ዕቅድ እንድንፈጽም አንተ እርዳን።