TT ethio

TT ethio እዝህ ፔጅ ማውራት የሚንችለው የሃገራችንን ኢትዮጵያ ታርክ ከእያንዳንዱ መንደር በመሰብሰብ እና በመደመር የታላቋን ኢትዮጵያ በጎ ገፅታ የሚናሳይበት ነው

08/03/2024
መልካም የገና ዋዘማ በዓል ይሁንላችሁ
06/01/2023

መልካም የገና ዋዘማ በዓል ይሁንላችሁ

ክፍል 8 ወይ ካፋ ሁሉ ሞልቶ ከሁሉም የሌለሽ!ለምለም በጠፈጥሮ የታደለች ምድር በዩኔስኮ በአለም ቅርስነት የተመዘገበ የደን ባለበት ካፋ,ከተፈጥሮ ደን ውስጥ ያሉ ገፀ-በረከቶች ለምሳሌ ቡና የ...
14/10/2020

ክፍል 8
ወይ ካፋ ሁሉ ሞልቶ ከሁሉም የሌለሽ!
ለምለም በጠፈጥሮ የታደለች ምድር በዩኔስኮ በአለም ቅርስነት የተመዘገበ የደን ባለበት ካፋ,ከተፈጥሮ ደን ውስጥ ያሉ ገፀ-በረከቶች ለምሳሌ ቡና የካፋ ማር ኮሮሪማ ጥምዝ እና የተለያዩ ለቁጥር የሚዳግቱ ለባህላዊ መድሃኒት የሚሆኑ እፅዋቶች ያሉባት ምድር ካፋ ,ማንኛውንም እህል ማብቀል የሚችል ለም መሬት ማዳበሪያ እንኳን የማይፈልግ መረት ያላት ምድር ካፋ,ማንኛውንም የቤት እንስሳት ለማርባት ምቹ እና ተስማሚ የሆነች ምድር ካፋ,ለምሳሌ የቦንጋን በግ ማንሳት ይቻላል አጠቃላይጠለሰው ልጆች ለኑሮ የሚስማማ አየር ያላት ምድር ካፋ ህዝቡ ያለውን አካፍሎ የሚበላ ደግ ህዝብ ሰው አክባሪ እንግዳ ተቀባይ ሩህሩህ ከደግነት ውጪ ምንም ክፋት የማያውቅ ኩሩ መለመን የማያውቅ ህዝብ ያላት ምድር ካፋ,ለመዝናኛ ምቹ የሆኑ ቦታወች ያሏት ለምሳሌ ባረታ ፋፋቴ የእግዜር ድልድይ የካፋ ደን በጥቂቱ ታይተው የማይጠገቡ እፅዋቶች መንፈስን የሚያድሱ ንፁ አየር ያለባት ምድር ካፋ ሁሉ ሞልተዋል ግን ሁሉ የላትም፡፡ታዲያ የእኔ ጥያቄ ይህ ሁሉ ሃብት ያላት ምድር ያ ሁሉ ደግ ህዝብ ያላት ምድር ነዋሪዎቿ ለምን ጎስቋላ ኑሮ እንዲገፉ ተፈረደባቸው?ለምንድነው ነዋሪዎቿ ታመው መታከም ሳይችሉ ጎጆአቸው ቁጭ ብለው ሞትን የሚጠብቁት?ለምንድነው በዝህ ዘመን ነዋሪዎቿ 7 ሰዓት እና 8 ሰዓት በእግር የሚጓዙት መኪና መንገድ ባለመኖር?በካፋ ምድር ላይ መኪና መንገድ ለመስራት የሚያስቸገር ቦታ አለ?ለምሳሌ ካፋ ዞን ከሁሉም ወረዳዎች ክረምት ከበጋ የሚያገናኝ የሰለጠነ መንገድ አለ?ከአድሷ ወረዳ ሽሾ እንዴ ውጪ እሷም ሚዛን መስመር ላይ ስለሆነች አጋጣሚውን ተጠቅማ ነው፡፡በዝህ ጉዳይ የሚሞግተኝ ካለ ዝግጁ ነኝ፡፡ከጎረበት ሸካ ዞን ለመሄድ አንድ ሰዓት በላይ የማይወስድ ድሪማሻ መንገድ ባለመሰራቱ ሸካ ለመሄድ ቀን ሙሉ በመኪና መጓዝ ይጠበቅብሃል ምክንያቱ ወይ በሚዛን ቴፒ ዞረህ ነው ወይም በጅማ መቱ ጎሬ አድርገህ ስትዞር ታመሻለህ ድሪ ማሻ መንገድ ለመስራት ምንም አይነት መሰናክል የለም ላለመስራት ነው የሚያስቸግረው እንጂ ለመስራት ምንም አያስቸግርም ስንት ዓመት እንደፈጄ ሁሉም ሰው ያውቃል እስከመቼ ነው ህዝቡ መንገለታት ያለበት?የዞኑ ሃብት ወዴት እየሄዴ ነው?ለምሳሌ ውሽውሽ ሻይልማት ለህዝቡ ምንድነው የጠቀመው?ተቀጥሮ የሚሰራው የቀን ሰራተኛ ስንት ነው ገቢው?ስንት ብር እየተከፈለው ነው?ወይስ መሄጃ ስሌለው ጉልበቱ ይበዝበዝ?ለመሆኑ ሻይልማቱ ባለቤት ማነው?ለዙኑ ልማት የደገፈው ምንድነው?ነዋሪው የተከለውን ደን ጨፍጭፎ ሻይ እየተከለ ተተኪ ደን ይተክላል ወይ?ነዋሪው ስበሉ እያየ መኖር ነው ያለበት?ይሄ ህዝብ አያሳዝንም?ብዙ ሚሊዮን ብር ገቢ እያስገባ ገበረውን እያፈናቀለ ለገበረው የሰራው ጤና ጣቢያ የታለ?ለገበረ ልጆች የሰራው ትምህርት ቤት የታለ?እሺ ማነው ተጠያቅው?አይበቃም ወይ ይሄ ግፍ?ዙኑን የምትመሩ የመንግስ አካላት እስካሁን ስትመሩ የነበራቹ የመንግስት አካላት ይሄን ሂሳብ ታወራርዳለህ፡፡ብዙ ጠያቂ እየመጣብህ ነው አሁን ያለህ የመንግስት አካላት እንዝህን ጥያቄዎች መልስ ይፈልጋሉ ጥያቄዎቹ ልክ አይደሉም ካልክ የሚሞግቱህ ዝግጁ ናቸው ካልቻልክ ልቀቅ ሃላፊነት ሃብት ማካበቻ ሳይሆን ሃብት እንዲያክብቱ ለተፈቀደላቸው ሰዎች በፍትሃዊ መንገድ ማመቻቸት ነው ሃላፊነት ለህዝብ ማገልገል እንጂ ከህዝብ መገልገል አይደለም፡፡ሃላፊነት ለህዝብ የሚቆምበት እንጂ በተቃራኒ ከቆሙት ተመሳጥረህ ለግልህ የሚትገብርበት አይደለም ይሄ ጊዜ ይቆማል በሰራሄው ልክ ሂሳብ ታወራርዳለህ፡፡

24/09/2020

ክፍል 6
ሰላም ለሁሉም ሰላም ለኢትዮጵያ ሃገሬ
ስለ ካፋ ታርክ እና ስለ ካፋ ንጉሶች በጥቅቱ ወደ ሃላ መለስ ብዬ ላስቃኛችሁ፡፡
ሁሉም የሃገራችን ነገስታት የየራሳቸው ለሃገራቸው ያበረከቱት አስተዋፅኦ ልመሰገኑ እንደሚገባ አምናለሁ ሁሉም የየራሳቸው አመለካከት እና አስተሳሰብ ብኖራቸውም በኢትዮጵያ ሃገራቸው ልዩነት ፈጥሮ አያውቁም ይሄን ካልኩ በሃላ ስለ አንድ የካፋ ንጉስ ታርክ የተወሰኔ እንሆ
መጠሪያ ስማቸው ጭኔቶ ጋሊቶ ሲሆን የዙፋን ስማቸው ካፊ አቲዮ ጋኬ ሻረቾ (አፄ ጋኬ ሻረቾ) የካፋ ንጉሰነገስት ናቸው፡፡ህዝቡ ዘወትር በፍቅርና በአክብሮት የሚጠራቸው ግን ታተኖ ጭኒ እያለ ነበረ፡፡ታቶ ማለት ንጉስ ማለት ነው በማህበረሰቡ ቋንቋ፡፡ካፋ ነገስታቶች ውስጥ የመጨረሻ ሶስቱ ነገስታቶቹ አንዱ ናቸው እነዝህ 3ቱ ነገስታቶች
1ኛ አፄ ካዮ ሻረቾ (ኪም ዩሮ)እ.ኤ.አ 1854-1870
2ኛ አፄ ጋሊ ሻረቾ (ታተኖ ጋሊ) እ.ኤ.አ 1870-1890
3ኛ አፄ ጋኪ ሻረቾ (ታተኖ ጭኒ)እ.ኤ.አ 1890-1897 የሚኒልክን የግዛት መስፋፋት ዘመቻ መከላከል ዋናው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ተግባራቸው አድርገው የቆዩት ንጉስ ናቸው አፄ ጋኪ ሻረቾ፡፡የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖትና የራስ ደርሶን ሙከራ ሳይጨምር ከሚኒልክ የመጨረሻ የካፋ ዘመቻ ጋር ከአራት መራራ ጦሪነት በሃላ ነበረ ጥንታዊው የካፋ መንግስት የተደፈረውና ዝነኛው የቡሻሼ ሚንጆ ስረወ መንግስት (ዳናይስቲ)የፈረሰው፡፡ከሽንፈት በሃላም ቢሆን ግን የመጨረሻው የካፋ አቲዮ (የካፋ ንጉስ ነገስት) ኩሩና ልቤ ሙሉ እንደነበሩ ታርክ ይመሰክራል፡፡ለምሳሌ በጠላት እጅ በወደቀ ጊዜ እንኳ በወርቅ ሰንሰለት እንዲታሰሩ እንጂ ብር ሰውነታቸውን እንዳይነካ ነበረ የጠየቁት፡፡ሆኖም ራስ ወ/ጊዮርግስ አበዬ (ቆቅማሪ) የወርቅ ሰንሰለት አላዘጋጁም ኖሮ በጥያቄው ተደነቁ፡፡ይሁንና ተሸንፈው ንጉሱ እራሳቸው ባቀረቡት ሰንሰለት ታሰሩ፡፡ጎጀብን ወንዝ ወንዝ በመሻገር ላይ ሳሉም የካፋ መንግስት አለቀልሽ ከውሃ የተገኘሽ የንጉስ ወርቅ ከውሃ ውስጥ ሁኚ (አቼ ዳኔቲ ታቲ አቼኔ አጮች ቤበ) ብሎ የንስና የወርቅ ቀለበታቸውን ወንዝ ውስጥ እንደከተቱት እስከ ዛሬ ይተረካል፡፡ከምኒልክ ፍት እንደቀረቡም ራስህን እንደታላቅ ንጉስ ትቆጥራለህ ነገር ግን ይሄ ግምትህ ከእኔ ጋር ፈፅሞ ሊወዳደር አይችልም ፡፡ላንቴ ዘውድ የተጫነው በሰው እጅ ሲሆን የኔው ግን ከላይ ከአንድ አምላክ የወረደልኝ ነው ማለታቸው ኩሩ እና አይበገረ ለመሆናቸው ማስረጃ ነው፡፡ህዝቡም እንዴ ንጉሱ በቀላሉ አለመበገሩም ፀሃፊ ገ/ስላሴ ሲገልፁ ነገር ግን ስለ ስፍራው ክፋት እየተዋጋ አልገብርም ብሎ ንጉሱ ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ እየተዘዋወረ የካፋ ሃገሩም ጠፋ ሰውም አለቀ ከዘማቹም ከክርስትያኑም ብዙ ሰው አለቀ ፡፡ከዝህ በሃላ 9 ወራት ሙሉ ተዋግቶ በነሃሴ 29 ቀን የካፋው ንጉስ ተማሰከ የተረፈውም ሃገር ሲማረክ ዘውዱ የወርቅ ወንበሩ የወርቅ አለንጋው ነጋሪት ያውም ነጋሪቱ አንዱ የብር አንዱ የነሃስ ነው በነጋሪቱም ላይ ስሙ ተፅፎበታል ይህ ሁሉ ከንጉሱ ጋር ተያዘ በማለት ነበረ የገለፁት፡፡የካፋ መንግስት ለአፄ ምኒልክ አላድርም ብሎ 17 አመት ሙሉ እጁን ሳይሰጥ ቆዬ፡፡ከአድዋ ጦሪነት በሃላ ግን ማለትምጣሊያን በተሸነፈ በአመቱ ተረታ፡፡ይህም ሊሆን የቻለው ከጣሊያን ሽንፈት በሃላ መሳሪያ በመገኘቱ በሃያ ሽህ ዘመናዊ ጠመንጃ በ3 አቅጣጫ ተከበው 9 ወራት ገትሮ ከተዋጋ በሃላ ነበረ የተሸነፈው፡፡አፄ ጋኪ ሻረቾ እና አፄ ምኒልክ እጅግ ተፎካካሪ ነገስታት ነበሩ፡፡ፉክክሩ በግብር አልገብርም ብቻ የተወሰነ ሳይሆን የስረው መንግስት(ዳናይስቲ) ጥያቄ ውዝግብ ስለነበረበት ነው፡፡ስለዝህም የካፋ ህዝብ በታርኩና በማንነቱ እንደሚመካ ባወቄ ጊዜ አደገኛነቱ ስለታያቸው ፔርሃም እ.ኤ.አ በ1948 ሶንታንደን የተባለው አገር አሳሽ ጠቅሶ እንደፃፈው አፄ ምኒልክ የስዊስ አማካሪያቸው የካፋ ነገስታትን የወርቅ ዘውድ ወደሃገሩ እንዲወስድ አደረጉ ፡፡አጋራሻ አቱሞ የተባሉ የታርክ አዋቂ አዛውንት እንደተናገሩት ሁለት ካፋወች ዘውዱን በትረ መንግስቱንና ሌላም ወርቃ ወርቅ የንግስና ዕቃዎችን ከአንኮበር ይዞ ካፋ ከገቡ በሃላ ከምንልክ የተላከ ጦር ሰወችን አሳድዶ ከገደለ በሃላቸው በሃላ ዕቃው ወደ አንኮቀር ተመለሰ፡፡ማርስ ግሩል ስለ ጦሪነቱ ያገኘውን ሠረጃ ስተነትን ወረራውን የአብሲኒያ ጦር ለመመከት የካፋ ጦር ያሳየውን የጀግንነት ስራና አሳዛኝ ፍፃሜው በሰው ልጅ የታርክ ማህደር ውስጥ ቦታ ሊኖረው የሚገባ ነው ይላል፡፡በምኒልክ የሬጅም ጊዜ የመስፋፋት ጦሪነት የካፋ ዘመቻ የመጨረሻው ምዕራፍ ነበረ፡፡በመጨረሻ የተሸነፈው ካፋ ነው የመጨረሻ ከበድ ብትር ያረፈበትም በካፋ ላይ ነበረ፡፡ በመጠኑም ቢሆን ታርኩን እንደተረዳችሁ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

20/09/2020

ሰላም ለእናንቴ ሰላም ለሀገራችን ይሁን፡
ክፍል 5
የካፋ ደንና ውበት በውስጡ ልዩ ትርጉም ያላቸው እፅዋቶች
በካፋ ደን ውስጥ ያሉት እፅዋቶች ጥቅቶቹን ባነሳ ኮሮሪማ ጥምዝ እና ቡና እነዝህ አለም የሚያውቃቸው ስለሆኑ እንጂ ለባህላዊ መድሃኒትነት የሚውሉ በጣም ብዙ ለቁጥር የሚያስቸግሩ እንዳሉ ስንቶቻችን እናውቃለን?ከጠቀስኳቸው ዋናዋናዎቹ ካፋ ለአለም ያበረከተችው ገፀበረከት ቡና ነው ፡፡ስለ ካፋ ሲነገር ስለቡና በተገቢው መጠን ባይነገር ትክክል አይሆን ፡፡ካፋ የቡና መገኛ ብቻ ሳትሆን ከሬጅም ጊዜ በፊት በአፍርካ አህጉር ከፍተኛ የቡና አምራች ሃገርም ነበረች ብሩስ የሚባል የታርክ ፀሃፊ በ1804 በፃፈው መፅሃፍ ላይ ገፅ 246 ተጠቅሶ ተቀምጠዋል፡፡ቡና ከካፋ ለመገኘቱ ከብዙ የታርክ ፀሃፊዎች መካከል ማክስ ግሩል የተባለ ፀሃፊ እንዲ ይላል ከአለም ህዝብ አብዛኛው ለመጀመሪያ ጊዜ በዝህች ሃገር(በካፋ) የበቀለውን ፍሬ (ቡና) ጭማቂ ስለሚጎነጭ የዝህች አፍርካዊ ሃገር ኢትዮጵያ ካፋ ስም ቢያንስ አመቱን ሙሉ በየቀኑ ለብዙ አለም ህዝብ አፍ ይጠራል ፡፡ቡና በካፋ የተገኘውና መታወቅ የጀመረው ታርክ መመዝገብ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ሲሆን አጠቃቀሙም ወደ መላው ደጋማው የኢትዮጵያ ግዛት የተሰራጨው ከዝሁ ሃገር ነው፡፡ ከዝያም በ9ኛው ክ/ዘመን አጠቃቀሙ በፔርሽያ /ኢራን /ይታወቅ ነበረ ማክስ ግሩል በ1932 በፃፈው ታርክ ላይ እንዳስቀመጠው፡፡ከሁለት ምዕተ አመታት በፊት ብሩስ እንዳስተዋለው ካፋ የቡና ተክል መገኛ እንደሆነ በጣም ይታመናል፡፡ ካፋ ጥንት በአፍርካ ዋና የቡና አምራች ምድር እንደነበረ ይነገራል፡፡በየአመቱ ካፋ 350000 ኪ/ግራም የሚሆን ቡና ወደ ውጭ ትልክ ነበረ ላንጌ የሚባል የታርክ ፀሃፊ እንደፃው፡፡ቡና የኢትዮጵያ ዋና የኢኮኖሚ ምንጭ ሲሆን ሜንጩም ካፋ መሆኑ ለዘላለም የሚታወስ ነው ቡና የሚል መጠሪያ ቡኖ የካፋቾ መጠሪያ ቃል ሲሆን በኢትዮጵያ በአብዛኛዎቹ ቋንቋዎችም የዝሁ ቃል መነሻ ሆሄ ተቀጥላ ሆሄያት እንዳለና ሁለተኛ ሆሄ እየተለወጠ ለተመሳሳ ይነገር ለምሳሌ ሲጠብቅና ስላላ ቡና;ቡን;ቡኔ;ቡኒ;ወዘተ በሚል ቢጠሪያነት ያገለግላል፡፡የቡናን ከካፋ አወጣጥና አሰረጫጨት በተመለከተ አንድ የአረብ ሰው በነፍሱ ቆርጦ የቡና ዘር ከካፋ በማውጣት አረቢያ እንደወሰደና በየመን ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲተከል እንዳደረገም ማክስ ግሩል ፅፈዋል፡፡ቡና በአረብ ሃገሮች እስካሁንም በመነሻው ቦታ የተሰጠውን ስያሜ በመያዝ ቡና ተብሎ ይጠራል፡፡ከየመንም በህላንዶች አማካይነት ቀደ ሩቅ ምስራቅ ለመሰራጨት በቅቷል፡፡ዛሬ በአለማችን ከፍተኛ የቡና አምራች ሃገር ብራዝል ስትሆን ወደ እዝች ሃገር የተወሰደውም በፖርቹጋሎች አማካይነት መሆኑ ይታመናል፡፡ቡና በ10ኛው ክ/ዘመን በመካ መዲና ይጠጣ ነበረ ቡና በአውሮፓዊያን ዘንድ በ1600 ዓም ይታወቅ የነበረ ሲሆን በአውሮፓ የቡና ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የተከፈተው በጣሊያንዋ የቨኑስ ከተማ በ1645 ገደማ ነበረ ከዝህ ቀደም ብሎ በ1632 ዓም አካባቢ ደግሞ በሺ የሚቆጠሩ የቡና መጠጫ ቤቶች ካይሮ ከተማ ይገኙ ነበረ፡፡ከዝህ ወቄት ጀምሮ ቡና በመላው አውሮፓና በዓለም ለመሰራጨት በቅተዋል ማክስ ግሩል እንደፃፈው፡፡ከዝህ ሌላ ቡና ከካፋ ስለመገኘቱና ከዋናዋና የገቢ ምንጮችም አንዱ እንደነበረ ብሩስ ,ኒውማን,ስትሮበ,እና ሌሎችም በስፋት እንደፃፉበት የሃለኞቹ እነ ላንጌ እና ግሩል ያረጋግጣሉ፡፡ካፋ ውስጥ ቡና የሚገኘው ተተክለው በእንክብካበው ከሚያድገው ተክል ብቻ ሳይሆን ምንጩ ከሆነው ከጫካ ከሚገኘው አውቆ በቀል በመልቀም ጭምር ነው፡፡ይንንም አባባል ማክስ ግሩል እንዲ በማለት ያረጋግጣል፡፡በብዙ ፓወንዶች የሚመዝን የአለም ምርጥ የቡና ፍሬ በየአመቱ እየወደቀ በጫካው ጥላ ስር የሚበሰብስበት አገር ብሎ ገልፆታል፡፡እንግዲህ ከዝህ የሚንረዳው ስለሃገራችን የተፈጥሮ ሃብት ምንም እውቀት የለንም ለማወቅም ፍላጎት የለንም ሌላ ዜጋ ግን እንዴት ለዓለም እንዳሳወቄ ተመልከቱት እኛ የታርክ ፀሃፊ የለንም?እሺ ድሮ አልተማርንም እንበል የታርክ ምሁር ነን የሚትሉት ባትፅፉ እንኳን የተፃፈውን እያመጣችሁ ትውልድ እንዲያነብ አድርጉት እራሳችንን ሳናው ሌላን ሰው ለማወቅ ከሚንጨነቅ እራሳችንን በደንብ ሳናይ ሌላን ሰው ለማየት ከምንጠራራ መጀመሪያ እራሳችንን እንወቅ ከዛ ሌላውን ብናወቅ አይጎዳም እላለሁ፡፡መልካም ጊዜ ተመኘሁ፡፡

17/09/2020

ክፍል አራት
ባለፈው ከክፍል 1-4 ስለሚዕራብ ኢትዮጵያ ማህበረሰብ ከሆኑት የካፋቾ ማህበረሰብ ባህል እና ወግ ማቅረቤ ይታወቃል አሁን ቀጣዩን ክፍል እንሆ፡- ሞት ለሰው ልጆች የማይቀር የተፈጥሮ ግዴታ ነው ሁላችንም ወደ የማይቀረው ሞት ስማችን እስከሚጠራ በተስፋ እንኖራለን ተስፋ እንዴት ደስ ይላል መሰላችሁ የሰው ልጅ እንደሚሞት እያወቀ ለማይኖራት አለም አብዝቶ ያስባል ወደፍት እያሰበ ተስፋ ያደርጋል ተስፋ ባይኖር ኖሮስ ትውልድ አይቀጥልም ሃገር አይገነባም ይህች ዓለም አትኖርም ተስፋ ከሁሉም በላይ ነው ለማለት ነው ዋናው ለማለት የፈለኩት ሃሳብ የሰው ልጅ የማይቀረውን ሞት በምድር የመኖር ወይም የመቆያ ጊዜውን ጨርሶ ሲሰናበት በሃገራችን የተለያዩ የአሸኛኘት ባህል አለው ከዝህ ውስጥ የካፋቾ ማህበረሰብ የለቅሶ እና የቀብር ስነ-ስርዓት በተወሰነ መልኩ ላስቃኛችሁ ወደድኩ ሟች ልጅም ይሁን አዋቂ ብዙ ጎልቶ የሚታይ ልዩነት የለውም ልክ አንድ ቤተሰብ ውስጥ የሞት አደጋ ካጋጠመ መገመሪያ ቤት ውስጥ ካለው ሰው ውጭ ማንም ሰው እንዲሰማ አይፈለግም በተቻለ መጠን ወረው እንዳይወጣ በሚስጥር ይያዛል ይህ የሚሆንበት ምክንያት በተለይ አሟሟቱ ድንገት ከሆኔ ቤት ውስጥ መስተካከል ያለበት ነገር ለማስተካከል ሲባል በተጨማሪ ሰዓቱም ለቀብር የማይመች ከእሩቅ ዘመድ እስከሚመጣ መጠበቅም ስላለበት ነው በአካባቢው ባህል በማንኛውም ሰዓት ዝግጅት ሳይደረግ የምት ወረው ከተሰራጬ ቀጥታ የቀብር ስነ- ስርዓት መፈፀም እንዳለበት እድሩ ያስገድዳል ዝግጅት ይኑር አይኑር ከእሩቅ የሚመጣ ቤተሰብ ይምጣ አይምጣ የሞቴ ሰው መቀበር እንዳለበት የአከባቢው ዕድር ያስገድዳል ይሄ እንዳይሆን ነው በተቻለ መጠን የሟች ቤተሰብ ሃዘኑን ዋጥ አድርጎ መዘጋጀት ያለበትን ነገር እና በተዘመድ ከሩቅ እንዲደርስ ካደረገ በሃላ ነው በለቅሶ ሃዘኑን የሚገልፀው ለምሳሌ ሟቹ ከጧቱ አራት ሰዓት ህይወቱ አልፋ ከሆኔ እስከ ማታ ሌላው የአካባቢው ሰው ሳይሰማ ቤት ውስጥ መስተካከል ያለበት ነገር እና እራቅ ያለ በተዘመድ መልዕክት ይላክለታል እንዲመጡ ይደረጋል ማታ ከአንድ ሰዓት በሃላ ግልፅ ይሆናል ሁሉም ይሰማል በለቅሶ ሃዘኑን ይገልፃል አራት ሰዓት ላይ ህይወት ያለፈው በዛን ሰዓት በሚስጥር ካልተያዘ ግዴታ የቀብር ስነ-ስርዓት ይፈፀማል ነገር ግን ከአንድ ሰዓት በሃላ ከሆነ ማታ ስለሆነ እስከሚነጋ መሟላት ያለበት ነገር ሟሟላት ስሚቻል ይፋ ይሆናል ማለት ነው ለቅሶ በይፋ ከታወቀ ጊዜ ጀምሮ ሁሉም የሚሰሩ ስራወችን የአካባቢው ዕድር ይረከብና ይፈፅማል ያስፈፅማል በተዘመዱ ሃዘኑን ከመግለፅ በዘለለ ምንም ተደራቢ ስራ አይሰራም ሃላፊነቱን የአካባቢው ዕድር ይረከባል ቀብሩ እንደሁኔታው አድሮ ውሎ እስከ ቀኑ 11 ሰዓት ድረስ ሊቆይ ይችላል በተዘመዱ እስከሚደርስ እና በኦርቶዶክስ ህግ የማስቀደስ ፀሎት የማድረግ ስርዓትም ስለሚከናወን በዝህን የሟቹ ቤተሰብ ህይወቱ ካለፈች ጊዜ ጀምሮ የቀብር ስነ-ስርዓት እስከሚፈፀም እህል ወሃ አይቀመሱም ቀማህበረሰቡ እምነት ሟች አፈር ሳይቀምስ በተዘመዱ እህል ወሃ አይቀምስም የሟቹን ስጋ እንደበላ ይታሰባል ነውር ነው ተብሎ ይታመናል በተጨማሪ 80 ቀን እስክሞላው በተዘመዱ ስጋ አይበላም ይሄም የሟቹ ስጋ ሳይበሰብስ አፈር ሳይሆን ከበላ የሟቹን ስጋ እንደበላ ይቆጠራል ለሟቹም ክብር ወይም ፍቅር የለውም ተብሎ ይታመናል ጊዜው ደርሶ ቀብር ከተፈፀመ በሃላ እዛው ላይ በተዘመድ ተሰብስቦ ሃዘኑን የሚገልፅበትና ሌላው ማህበረሰብ በተዘመዱን በአንድ ቦታ አግኝቷቸው የሃዘኑ ተካፋይ እንዲሆን ቀነ ቀጠሮ ይያዛል የሚያዘው ቀንም የስራ ቀን ያልሆኔ ለምሳሌ እሁድ ቀን ሊሆን ይችላል ቀኑ ላይ የሟች በተሰብ ወስኖ ያሳውቃል ከዛ በሃላ ሁሉም በተዘመድ አስከረኑ ወደ ወጣበት ቤት ይሄዳል ከላይ እንደገተፅኩት የአካባቢው ዕድር ቡና ምግብ አዘጋጅቶ ይጠብቃል ከተበላ ከተጠጣ በሃላ እራቅ ያለ የአካባቢው ማህበረስብ ማለት የእድሩ አባል ያልሆነ ወደቤቱ ይሄዳል የእድሩ አባል ግን እንዴ እድሩ የሰው ሃይል ብዛት የማስተዛዘን ስራን ምግብ ውሃ ቡና የመሳሰሉትን ለቀን ይከፋፈላሉ ለምሳሌ ዛሬ አራት ሰው ሁሉንም ወጪ ከሸፈነ ነጌ ተመሳሳይ አራት ሰው ይመደባል እንደ ሰው ብዛት እስከ 15 ቀን ከዛም በላይ የሟች በተሰብ ስለሚበላው ስለሚጠጣው ነገር አያስብም ውጪውን ዕድሩ ይሸፍናል ከላይ እንደገለፅኩት የተያዘለት ቀን ስደርስ ሰፍ የሆኔ መዳ ተመርጦ ዳስ ነገር ብዙ ሰው ማስተናገድ የሚችል ተደርጎ ይሰራል በቀኑ ጧት ጀምሮ ከሁሉም አካባቢ መጥቶ ሃዘናቸውን ገልፀው በተዘመዱን አፅናንተው ይመለሳል በቀጠሮ ቀን የታመመ እና በአካባቢው ያልነበረ ካልሆነ በስተቀር ከቀጠሮ ቀን በሃላ የሚመጣ ሰው የለም የቀጠሮ ቀን ጥቅሙ በተዘመዱን ለማፅናናት የሚመጣ ሰው በአንድ ቦታ ላይ ሳይጉላላ ያገኛቸውና አፅናንቶ ይሄዳል ለሟች በተሰቦች ደሞ ሁሉንም ጠያቂ በአንድ ቀን አስተናግዶ ወደ መደበኛ ስራቸው ለመግባት ያመቻል ተብሎ ስለሚታሰብ ነው በዝህ ውስጥ በጣም ብዙ ባህልና ወጎች አሉ ግን በዝህ ሁሉንም መግለፅ ስለሚያስቸግር ነው፡፡መልካም አድስ አመት

Address

Ethiopia
Yambio

Telephone

+211916729165

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when TT ethio posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category