Harewa Anole Full Gospel church

Harewa Anole Full Gospel church Jesus Is Lord king of king

ከሞተ አንድ ሳምንት በኋላ ለባሏ ገዳዮች እንዲህ ስትል ጻፈች፡፡ ይቅር ብያችኋለሁ፡፡ ደግሞም እወዳችኋለሁ፡፡  ይህንን መልዕክት ያስተላለፈችው አኒታ ሰሚዝ ትባላለች፡፡ ሊቢያ ቤንጋዚ ውስጥ የ...
12/09/2024

ከሞተ አንድ ሳምንት በኋላ ለባሏ ገዳዮች እንዲህ ስትል ጻፈች፡፡ ይቅር ብያችኋለሁ፡፡ ደግሞም እወዳችኋለሁ፡፡ ይህንን መልዕክት ያስተላለፈችው አኒታ ሰሚዝ ትባላለች፡፡ ሊቢያ ቤንጋዚ ውስጥ የ10 ዓመት የትዳር አጋሯን ለገደሉት የእስልምና አክራሪዎች ነው፡፡
ባሏ ሩኒ ሰሚዝ ይባላል፡፡ ከአሜሪካ ቴክሳስ በኬሜስትሪ መምህርነት እና በወንጌል አጋይነት ወደ ሊቢያ መጣ፡፡ ይህንን ውሳኔ እንዲወስን ያደረገው ጆን ፓይፐር የተባለ ሰባኪ የሰበከው ስብከት ነው፡፡ ስብከቱ ጥቅም ባለው ሞት ውስጥ ተልዕኮን መፈጸም /Doing mission when dying is gain/ የሚል ነው፡፡ ከዚህ ስብከት በኋላ ሚስቱን እና ጨቅላ ልጁን ይዞ ወደ ሊቢያ አቀና፡፡ ከመምህርነቱ ጎን ለጎን ወንጌል ስራው ነው፡፡
ሩኒ ሰሚዝ አጭር ጊዜ ነው በምድር የኖረው ነገር ግን በኖራት አጭር ዘመን እንዲሁም በሞቱም ጭምር ወንጌልን ሰብኮ ተሰውቷል፡፡ በቤንጋዚ የነበሩ ተማሪዎቹ ስለሱ ብዙ ይናገራሉ፡፡
ይቅር ብያችኋለሁ፡፡ ደግሞም እወዳችኋለሁ ፡፡ ከኢየሱስ የተማርኩት ይህንን ነው፡፡ ትላለች አኒታ ስሚዝ ለባሏ ገዳዮች፡፡
ጣቶቻቻሁን ውደዱ ሉቃ 6፡35

በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1930ዎቹ አካባቢ በተራራማው የሮማንያ ሀገር የሚኖር አንድ አናጺ እግዚአብሔር ሆይ ጸሎቴን በምድርም በሰማይም እንድትመልስልኝ እፈልጋለሁ የሚል ጸሎት ነበረው፡፡ ጸሎቱ ...
02/09/2024

በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1930ዎቹ አካባቢ በተራራማው የሮማንያ ሀገር የሚኖር አንድ አናጺ እግዚአብሔር ሆይ ጸሎቴን በምድርም በሰማይም እንድትመልስልኝ እፈልጋለሁ የሚል ጸሎት ነበረው፡፡ ጸሎቱ ደግሞ እግዚአብሄር ሆይ እንደምታውቀው ኢየሱስ ክርስቶስ ከአይሁድ ወገን ነው እኔ ሽማግሌ ፡ደሃ፡ በሽተኛ እና ደካማ ነኝ ሀገራቸው ሔጄ ወንጌል መስበክ አልችልም፡፡ በዚህ በአካባቢዬ ደግሞ አይሁዳዊ የለም፡፡ ስለዚህ እዚሁ ባለሁበት አይሁዳዊ ላክልኝ እና ከመሞቴ በፊት አንድ አይሁዳዊ ጌታ ኢየሱስን እንደ አዳኝ ላስቀብል አለ፡፡
እግዚአብሄርም ጸሎቱን ሰማው በአስደናቂ ሁኔታም ጸሎቱን መለሰለት፡፡ እንድ ወጣት በእግዚአብሄር መኖር የማያምን ነገር ግን መልስ ባላገኘላቸው መንፈሳዊ ጥያቄዎች የተሞላ አይሁዳዊ ይህ ደሃ አናጺ ወደ ሚኖርብት መንደር መጣ፡፡ ምን እንደ ገፋው ሳያውቅ ወደዚህ አናጺ ቤት ጎራ አለ፡፡ በሮማንያ 12 ሺ መንደሮች አሉ ነገር ግን ለምን እዚህ እንደመጣሁ አላውቅም አለው ለአናጺው፡፡
አናጺው ይህ የጸሎቱ መልስ መሆኑን ተረዳ መጽሐፍ ቅዱስ አወጣና እና ለዚህ ወጣት አይሁዳዊ ሰጠው፡፡ ወጣቱ ሲናገር ይህ ሰው የሰጠኝዝም ብሎ በወረቀት ላይ የተጻፈ መጽሐፍ ሳይሆን በጸሎት እሳት የነደደ ከውስጡ የሚፋጀውን የኢየሱስን ትኩስ ፍቅር የሚያሳይ ነበር ይላል፡፡ አነበብኩት ፡ አለቀስኩ፡ በዚህ ፍቅር ልቤ ቀለጠ የኔን የረከሰ ሕይወት ከኢየሱስ ንጹህ እና ጥልቅ ፍቅር ጋር አስተያየሁ፡ በመጨረሻም ነፍሴን ሰጠሁት መድሐኒቴን ተቀበልኩ፡፡
ይህ ወጣት አይሁዳዊ ሪቻርድ ውምብራንድ ይባላል፡፡ እጅግ የተወደደ ለዚህ ለተቀበለው ኢየሱስ በሮማንያ እስር ቤቶች ለ14 አመታት በጣባብ እና ጨለማ ክፍል ውስጥ በድደባና እና በእስራት የተሰቀየ፡ በጻፋቸው መጽሐፎች ለሚሊዮን ክርስቲያኖች መጽናኛ የሆነ ሰው ነው፡፡ በተለይ ለክርስቶስ ተሰቃየሁ /Tortured for Christ/ በሚለው መጽሐፉ በመከራ እና በስደት ለሚያልፉ አማኞች መበርቻ የሆነ ወንድም ነው፡፡ በሐገራችንም በደርግ ዘመን በክርስቲያኖች ላይ በነበረው ስደት ይህ መጽሐፍ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ለብዙዎች መጽናኝ ሆኗል፡፡
አንተስ እኔስ አንቺስ ከመሔዳችን በፊት ጸሎታችን ምን ይሆን?

Waldaa Mulu wongeelii Harawaa Aanoleetii 07/04/2016 Namonii kudhan(10) Cuphaa bishaan fudhatanii jiru.
02/01/2024

Waldaa Mulu wongeelii Harawaa Aanoleetii 07/04/2016 Namonii kudhan(10) Cuphaa bishaan fudhatanii jiru.

17/01/2016 መሪዎችና የአግልግሎት ዘርፎች ከአምስቱም ቸርች በመገኘቱ ተባርከናል።
01/10/2023

17/01/2016 መሪዎችና የአግልግሎት ዘርፎች ከአምስቱም ቸርች በመገኘቱ ተባርከናል።

18/09/2023
27/11/2022
የወንጌል እሳት በሐረዋ ይቀጥላል ።
26/11/2022

የወንጌል እሳት በሐረዋ ይቀጥላል ።

የረዳን ጌታ ስሙ ይክበር።
13/07/2022

የረዳን ጌታ ስሙ ይክበር።

Address

Berbera

Telephone

+251938085524

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harewa Anole Full Gospel church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share