Medhanealem church - በስቶክሆልም ስዊድን የደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን

  • Hem
  • Sverige
  • Stockholm
  • Medhanealem church - በስቶክሆልም ስዊድን የደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን

Medhanealem church - በስቶክሆልም ስዊድን የደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን Kyrkans ordinarie verksamhet rymmer bland annat dop, bröllop, begravning, och gudstjänst varje söndag
(1)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደብረ ሰላም
መድኃኔዓለም መንበረ ጵጵስና በስቶክሆልም፣ ስዊድን የሚገኝ አንጋፋ እና ታላቅ ቤተክርስቲያን ሲሆን ፤ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳሳችን የብጹዕ አቡነ ኤልያስ መንበራቸው ነው፤ ይህ ገጽም በቤተክርስቲያኑ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን እንዲሁም ለምእመናን የሚተላለፉ መልእክቶችን የምናስተላልፍበት ነው።

22/04/2026
የሰሙነ ሕማማት መርሐ ግብር በደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን
07/04/2026

የሰሙነ ሕማማት መርሐ ግብር በደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን

06/04/2026

የ2018 ዓ.ም ዓመታዊው የመጋቢት መድኃኔ ዓለም እና የሆሣዕና በዓል አከባበር በመንበረ ጵጵስና ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን።

ስቶክሆልም ፣ ስዊድን

27/03/2026
✝️መንፈሳዊ በዓለ ንግሥ እና የስብከተ ወንጌል ጥሪ✝️"እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።"ዮሐ 3፥16ዓመታዊው የጥቅምት መድኃኔ ዓለም ክብረ በዓል በስቶክሆ...
01/11/2025

✝️መንፈሳዊ በዓለ ንግሥ እና የስብከተ ወንጌል ጥሪ✝️
"እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።"ዮሐ 3፥16
ዓመታዊው የጥቅምት መድኃኔ ዓለም ክብረ በዓል በስቶክሆልም መንበረ ጵጵስና ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም /November 8, 2025 GC/ በድምቀት ይከበራል።
በበዓሉ ላይ የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ እና የሀገረ ስብከታችን ዋና ስራ አስኪያጅ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ ይገኛሉ።
መርሐ ግብር፦
✝️ ዓርብ ጥቅምት 28, 2018 ዓ.ም [07-11-2025] ከ16:00 ሠዓት ጀምሮ ሥርዓተ ዋዜማ እና ስብከተ ወንጌል
ማታ ከ21:00 - 06:00 ሥርዓተ ማኅሌት
✝️ ቅዳሜ ጥቅምት 29, 2018 ዓ.ም [08-11-2025] ከ06:00 ሠዐት ጀምሮ ሥርዓተ ቅዳሴ እና በዓለ ንግሥ
📍ቦታ: Huddinge በሚገኘው S.t Matti & S.t Behnams የSyrian ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን!
Grantorpsvägen 1, 141 59 Huddinge

የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ተጋብዘዋል!

የስቶክሆልም ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን
ስቶክሆልም ፣ ስዊድን

እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!የቀጥታ ስርጭት ከመንበረ ጵጵስና ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ስቶክሆልም ፣ ስዊድን
26/09/2025

እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

የቀጥታ ስርጭት ከመንበረ ጵጵስና ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ስቶክሆልም ፣ ስዊድን

የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር ቀጥታ ስርጭት ከስቶክሆልም ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም መንበረ ጵጵስና መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!ቀን:-    - የደመራ በዓል ዓርብ መስከረም  16, 2018 ዓ.ም/September 26, 2025 GC/ ይከበራል።ሰዓት:-    - ከ16:00 ጀም...
21/09/2025

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!

ቀን:-
- የደመራ በዓል ዓርብ መስከረም 16, 2018 ዓ.ም/September 26, 2025 GC/ ይከበራል።

ሰዓት:-
- ከ16:00 ጀምሮ

አድራሻ:-
- T-bana(Hagsätra), Pålsbodagränd 3, Stockholm

የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኃል፡፡

መንበረ ጵጵስና ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ስቶክሆልም ፣ ስዊድን

የሳምንቱ መርሐ ግብር በደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን
14/04/2025

የሳምንቱ መርሐ ግብር በደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን

መንፈሳዊ በዓለ ንግሥ እና የስብከተ ወንጌል ጥሪ"እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።"ዮሐ 3፥16ዓመታዊው የመጋቢት መድኃኔ ዓለም ክብረ በዓል በዕለቱ ቅዳሜ ...
03/04/2025

መንፈሳዊ በዓለ ንግሥ እና የስብከተ ወንጌል ጥሪ

"እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።"ዮሐ 3፥16

ዓመታዊው የመጋቢት መድኃኔ ዓለም ክብረ በዓል በዕለቱ ቅዳሜ መጋቢት ፳፯ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም /April 5, 2025 G.C/ በድምቀት ይከበራል።

በበዓሉ ላይ የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ እና የጣልያንና አካባቢው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ተገኝተው ይባርኩናል::

ተጋባዥ መምህር:- መምህር ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ

መርሐ ግብር፦
- መጋቢት 26 , 2017 ዓ.ም/April 4, 2025/፦
ስብከተ ወንጌል ከ16፡00 ሰዓት ጀምሮ ፣ ሥርዓተ ማኅሌት ከ22፡00 - 06፡00
- መጋቢት 27, 2017 ዓ.ም/April 5, 2025/፦
ሥርዓተ ቅዳሴ እና በዓለ ንግሥ ከ06፡00 ሰዓት ጀምሮ

አድራሻ:-
T-bana(Hagsätra), Pålsbodagränd 3, Stockholm

የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኃል፡፡

የስቶክሆልም ደብረ ሰላም መንበረ ጵጵስና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት
ስዊድን ፣ ስቶክሆልም

Adress

Pålsbodagränd 3 Hagsätra Stockholm
Stockholm

Öppettider

Onsdag 17:00 - 19:00
Fredag 17:00 - 19:00
Söndag 05:00 - 14:00

Telefon

+4687246076

Aviseringar

Var den första att veta och låt oss skicka ett mail när Medhanealem church - በስቶክሆልም ስዊድን የደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን postar nyheter och kampanjer. Din e-postadress kommer inte att användas för något annat ändamål, och du kan när som helst avbryta prenumerationen.

Kontakta Heliga Platser

Skicka ett meddelande till Medhanealem church - በስቶክሆልም ስዊድን የደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን:

Dela