ሊቀ ዲያቆናት ጎርፉ ስጦታው " ዘኳታር ቅድስት ሥላሴ "

  • Home
  • Qatar
  • Doha
  • ሊቀ ዲያቆናት ጎርፉ ስጦታው " ዘኳታር ቅድስት ሥላሴ "

ሊቀ ዲያቆናት ጎርፉ ስጦታው  " ዘኳታር ቅድስት ሥላሴ " 💚💛❤️ አምላኬ ኳታር ቅድስት ሥላሴን ሳልጨርስ የትም አትውሰደኝ ::

17/06/2026

🔔 የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ የክብረ በዓል ጥሪ 🔔
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” (መዝ 33፡7)

በኳታር የምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን በሙሉ፤ የሞት ደብዳቤን ወደ ሕይወት የለወጠው የታላቁ ሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ የክብረ በዓል ደርሷል።
በመሆኑም በዚህ አርብ ሰኔ 12 ቀን (June 19, 2026) ከጠዋቱ 4:00 (10:00 AM) ጀምሮ በኳታር የኤርትራ ደብረ ሳሕል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በሚደረገው ታላቅ የክብረ በዓል መርሐ-ግብር ላይ ተገኝታችሁ የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ የደብሩ አስተዳዳሪ አባታችን መልአከ ሳሕል ቀሲስ ሐዱሽ ሙሴ ጥሪያቸውን በታላቅ መንፈሳዊ ፍቅር አስተላልፈዋል ።

🕊️ የቅዱስ ሚካኤል አማላጅነትና ረድኤት አይለየን! 🕊️
(ለወዳጅዎ ሼር በማድረግ የመልአኩን የበረከት ጥሪ ያድርሱ)

 #እሽዬ ይህ ቪዲዮ ይበልጥ ማንነትህን ለአለም የገለጠ እኔ በጣም የተማርኩበት ድንቅ ነው ሁላችንም ካፈርኩ አይመልሰኝ ብለን በኢጎ ተወጥረን ብዙ በምናጠፋበት በዚህ ዘመን ይህንን ሳይ በብዙ ...
15/06/2026

#እሽዬ ይህ ቪዲዮ ይበልጥ ማንነትህን ለአለም የገለጠ እኔ በጣም የተማርኩበት ድንቅ ነው ሁላችንም ካፈርኩ አይመልሰኝ ብለን በኢጎ ተወጥረን ብዙ በምናጠፋበት በዚህ ዘመን ይህንን ሳይ በብዙ ተማርኩ በርታልኝ ወንድሜ ::

📌የዶንኪ ትዩብን አገልግሎት ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!!https://donkeytube.not...

እሽዬ ትችላለህ ሁሌም ታስደምመኛለህ !!
12/06/2026

እሽዬ ትችላለህ ሁሌም ታስደምመኛለህ !!

📌የዶንኪ ትዩብን አገልግሎት ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!!https://donkeytube.not...

❖ የምስጋና እና የአድናቆት መግለጫ ❖"በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም ዕውቀት የበለፀጉ፣ ፍቅርን በተግባር ያሳዩን ድንቅ አባት!"የመካከለኛው ምስራቅ ሀገረ ስብከት የሒሳብ እና በጀት መምሪያ እን...
07/06/2026

❖ የምስጋና እና የአድናቆት መግለጫ ❖
"በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም ዕውቀት የበለፀጉ፣ ፍቅርን በተግባር ያሳዩን ድንቅ አባት!"

የመካከለኛው ምስራቅ ሀገረ ስብከት የሒሳብ እና በጀት መምሪያ እንዲሁም የሚዲያ ክፍል ኃላፊ የሆኑት መጋቤ ምስጢር ቀሲስ ያሬድ መኮንን በኳታር ለነበረን ቆይታ ያበረከቱት እጅግ የላቀ አባታዊና ወንድማዊ አገልግሎት ሁላችንንም እጅግ አስደስቶናል ::

አባታችን ወደ ኳታር መጥተው ካከናወኗቸው በርካታ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ተግባራት መካከል ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል፡-

• ቀድሰው ፣ አቁርበው ፣ ቃለ እግዚአብሔር አስተምረው በመንፈሳዊ ሕይወታችን ላይ ታላቅ መነቃቃትን ፈጥረዋል እንዲሁም ባላቸው ጥልቅ ዕውቀት እና ልምድ አስተዳደራዊና የኦዲት ሥራ፦ ቤተ ክርስቲያኑ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ያለውን የሒሳብ ሥርዓት እንዲሁም የሰበካ ጉባኤውን የ4 ዓመታት ሙሉ የሥራ ጉዞ እጅግ በበሰለና በሰለጠነ መንገድ ኦዲት አድርገው በስኬት አጠናቀዋል።

መጋቤ ምስጢር በሁሉም ረገድ ምሉዕ የሆኑ በዓለማዊውም ዕውቀትና ጥበብ የላቁ፣ በመንፈሳዊውም ሕይወትና ዕውቀት የበለፀጉ ድንቅ ሠው ናቸው። የኦዲት ሥራውን ያከናወኑበት ጥንቃቄና ጥራት ላይ የሙያ ብቃታቸውን፤ በሰጡን ምክርና አስተምህሮ ደግሞ የመንፈሳዊ አባትነታቸውን ጥልቀት በተግባር አሳይተውናል።

ሀገረ ስብከታችን እንደ እሳቸው ያለ በሳል፣ ታማኝ፣ ሥራ አዋቂ እና አርቆ አሳቢ በማግኘቱ እጅግ የታደለ ነው፤ እኔም በዚህ አጋጣሚ ታላቅ ደስታ ተሰምቶኛል ።

ውድ አባታችን
በኳታር ቆይታዎ ስላሳለፍነው እጅግ ጣፋጭና ፍሬያማ ጊዜ፣ ስላሳዩን ወንድማዊና አባታዊ ፍቅር፣ እንዲሁም ስለደከሙት ድካም ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ::
እግዚአብሔር አምላክ ዕድሜና ጤና ይስጥልኝ! የአገልግሎት ዘመንዎን ያርዝምልኝ፣ በጸጋ ላይ ጸጋ ይጨምርልዎት። በሰላም ከመጡበት በሰላም ስለተመለሱ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን!!

አንቺ የደም ምድር መቼ ነው ምትረኪው መቼ ነው በቃኝ ምትይው ??  እኛም ሻማዋን ብልጭ እያረግን ሟች እንቆጥራለን አይይይ መጨረሻችን ምን ይሆን እነሱም ከልካይ ስለሌላቸው መጨፍጨፋቸውን እኛ...
02/06/2026

አንቺ የደም ምድር መቼ ነው ምትረኪው መቼ ነው በቃኝ ምትይው ?? እኛም ሻማዋን ብልጭ እያረግን ሟች እንቆጥራለን አይይይ መጨረሻችን ምን ይሆን እነሱም ከልካይ ስለሌላቸው መጨፍጨፋቸውን እኛም መቁጠራችን አናቆምም ያሳዝናል 😭

✈️ የክብር እንግዳ አቀባበል የክብር እንግዳችን መጋቤ ምሥጢር ቀሲስ ያሬድ መኮንን ዶሃ (ኳታር) ገብተዋል።በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመካከለኛው ምስራቅ ሀገረ ስብከት የ...
27/05/2026

✈️ የክብር እንግዳ አቀባበል
የክብር እንግዳችን መጋቤ ምሥጢር ቀሲስ ያሬድ መኮንን ዶሃ (ኳታር) ገብተዋል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመካከለኛው ምስራቅ ሀገረ ስብከት የሂሳብ እና በጀት መምሪያ እንዲሁም የሚዲያ ክፍል ኃላፊ የሆኑት ክቡር መጋቤ ምሥጢር ቀሲስ ያሬድ መኮንን የኳታር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንን ያለፉትን የ4 ዓመታት የሰበካ ጉባኤ እና የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ የሒሳብ መዝገብ ኦዲት ለማድረግ ዛሬ ግንቦት 19 ቀን ዶሃ ሐመድ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሰዋል።

🤝 የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት
ክቡርነታቸው ኤርፖርት በደረሱበት ወቅት የደብሩ መሪዎችና የሥራ ኃላፊዎች በታላቅ መንፈሳዊ ክብርና ደስታ ተቀብለዋቸዋል። በአቀባበሉ ላይ የተገኙት፦
• መልአከ አርያም ቆሞስ አባ ሠርጸ ድንግል — የደብሩ አስተዳዳሪ
• መጋቤ ሐዲስ መምህር ዳንኤል አለባቸው — የደብሩ የአብነት መምህር፣ የስብከተ ወንጌል ኃላፊ እና የደብሩ ዋና ጸሐፊ

🕊️ የምኞት መግለጫ
የደብራችን የፋይናንስ አያያዛችን ግልጽና ሥርዓታማ በሆነ መንገድ እንዲቀጥል የሚያስችለውን ይህንን ታላቅ የኦዲትና የክትትል ሥራ ለመሥራት በዘርፉ ሰፊ የሥራ ልምድ ያላቸው በይፋዊ የሥራ ጉብኝት ወደ ደብራችን የመጡትን ክቡር መጋቤ ምሥጢር ቀሲስ ያሬድ መኮንን ደግመን “እንኳን በደህና መጡልን” እንላለን።
እግዚአብሔር አምላክ ለአገልግሎታቸው ኃይልን ይስጥልን!

ስሳሳላችሁ !!
21/05/2026

ስሳሳላችሁ !!

14/05/2026

ነገ አርብ ግንቦት 7 ቀን የሊባኖሷ አበባ እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ትነግሳለች ሁላችሁም ከጠዋቱ 5 ሰዓት ጀምሮ መጥታችሁ እንድታነግሱ ስል የከበረ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ ::

🌟 ደስ ብሎናል 🌟ወንድሜ  ማዕተቡ "እንኳን ለቅዱስ ጋብቻ አበቃህ! በበረሀዋ ገነት በኳታር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ለነበረህ የረጅም ዓመታት የአገልግሎት እግዚአብሔር ዋጋ...
06/05/2026

🌟 ደስ ብሎናል 🌟
ወንድሜ ማዕተቡ "እንኳን ለቅዱስ ጋብቻ አበቃህ! በበረሀዋ ገነት በኳታር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ለነበረህ የረጅም ዓመታት የአገልግሎት እግዚአብሔር ዋጋህን ከፈለህ ። ዛሬ ደግሞ በሀገርህ በኢትዮጵያ ሆነህ የትዳርን አክሊል በመድፋትህ ደስታችን እጥፍ ድርብ ሆኗል። የቅዱሳን አምላክ ትዳራችሁን ይባርክ፤ የሰላምና የፍቅር ዘመን ያድርግላችሁ።

🌟 ፀዲዬ እንኳን ደስ አለሽ በኳታር የሚገኘው የሀበሻ የውበት ሳሎን ከቁጥር 1 እስከ 3 ቅርንጫፎችን በተለያየ ቦታ በመክፈት ደማቅ ስኬት አስመዝግቧል።  ይህ ብርቱዋ እህታችን ፀዲ ያስመዘገበ...
05/05/2026

🌟 ፀዲዬ እንኳን ደስ አለሽ
በኳታር የሚገኘው የሀበሻ የውበት ሳሎን ከቁጥር 1 እስከ 3 ቅርንጫፎችን በተለያየ ቦታ በመክፈት ደማቅ ስኬት አስመዝግቧል። ይህ ብርቱዋ እህታችን ፀዲ ያስመዘገበችው ውጤት ለሁላችንም ኩራት ከመሆኑም በላይ፣ ከውበት ሳሎን በተጨማሪ በሀበሻ ትሬዲንግ የውበት መጠበቂያ መሸጫ ሱቅ ስራዋን ማስፋቷ ለሌሎች ኢትዮጵያውያን ትልቅ መነሳሳትን ይፈጥራል። ለዚህ ትልቅ ስኬት ስለበቃሽ እግዚአብሔር ይመስገን ሥራሽን ይባርክልሽ ሰርተሽ ምትጠቀሚ ያድርግሽ እንኳን ደስ አለሽ፤ በርቺ!!

Address

Doha
90945

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሊቀ ዲያቆናት ጎርፉ ስጦታው " ዘኳታር ቅድስት ሥላሴ " posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ሊቀ ዲያቆናት ጎርፉ ስጦታው " ዘኳታር ቅድስት ሥላሴ ":

Share