17/06/2026
🔔 የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ የክብረ በዓል ጥሪ 🔔
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” (መዝ 33፡7)
በኳታር የምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን በሙሉ፤ የሞት ደብዳቤን ወደ ሕይወት የለወጠው የታላቁ ሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ የክብረ በዓል ደርሷል።
በመሆኑም በዚህ አርብ ሰኔ 12 ቀን (June 19, 2026) ከጠዋቱ 4:00 (10:00 AM) ጀምሮ በኳታር የኤርትራ ደብረ ሳሕል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በሚደረገው ታላቅ የክብረ በዓል መርሐ-ግብር ላይ ተገኝታችሁ የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ የደብሩ አስተዳዳሪ አባታችን መልአከ ሳሕል ቀሲስ ሐዱሽ ሙሴ ጥሪያቸውን በታላቅ መንፈሳዊ ፍቅር አስተላልፈዋል ።
🕊️ የቅዱስ ሚካኤል አማላጅነትና ረድኤት አይለየን! 🕊️
(ለወዳጅዎ ሼር በማድረግ የመልአኩን የበረከት ጥሪ ያድርሱ)