ቶጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተ ክርሰትያን

ቶጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተ ክርሰትያን PREACH GOSPEL
ይህንን የወንጌል አገልግሎት በገንዘባችሁ መደገፍ የምትፈልጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቶጫ ቅርንጫፍ አካውንት ቀጥር 1000193287151

03/04/2026
ቶጫ ያላችሁ በፍጹም እንዳያመልጣችሁ።
26/03/2026

ቶጫ ያላችሁ በፍጹም እንዳያመልጣችሁ።

 "አብርሃም ሆይ! ይስሐቅን በወለድክ ጊዜ በረከትን አገኘህ፤ ነገር ግን ይስሐቅ በልብህ ላይ ከነገሠ፣ አንተ ለፈጣሪ መስዋዕት መሆንህን ትተህ ለበረከትህ ባሪያ ትሆናለህ። ሰውን እግዚአብሔርን...
22/02/2026



"አብርሃም ሆይ! ይስሐቅን በወለድክ ጊዜ በረከትን አገኘህ፤ ነገር ግን ይስሐቅ በልብህ ላይ ከነገሠ፣ አንተ ለፈጣሪ መስዋዕት መሆንህን ትተህ ለበረከትህ ባሪያ ትሆናለህ። ሰውን እግዚአብሔርን እንዳያገለግል የሚያደርገው ሰይጣን ብቻ አይደለም፤ በአግባቡ ያልያዝነው 'በረከታችንም' ጭምር ነው!"

​እውነተኛ መንፈሳዊነት ስጦታዎቻችንን (ይስሐቆቻችንን) ለእግዚአብሔር መሠዊያ አድርገን እንድንሰጥ እንጂ፣ ስጦታዎቻችን እኛን አስረው ጌታን በትጋት ከመፈለግ እና እርሱን ከማገልገል እንዲያደርጉን መፍቀድ የለብንም። ብዙ ጊዜ ሰውን ከፈጣሪው የሚለየው ችግር ሳይሆን በረከት ነው። በችግር ጊዜ ወደ አምላክ እንጮኻለን፤ በበረከት ጊዜ ግን በረከቱ እኛን አስተኝቶን (አጋድሞን) አምላካችንን እንድንረሳ ያደርገናል።

እውነተኛው መሠዊያ ያለው ልብህ ላይ ነው። በረከትህን (ይስሐቅህን) በመሠዊያው ላይ ካላስቀመጥከው፣ በረከትህ አንተን መሠዊያው ላይ ያጋድምሃል።

Christ Followers የክርስቶስ ተከታዮች

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ለአንድ ወር የሚቆይ ሀገር አቀፍ የጾም እና ጸሎት አወጀችየኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ መሪዎች ዛሬ የካቲት 12 ቀን ...
20/02/2026

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ለአንድ ወር የሚቆይ ሀገር አቀፍ የጾም እና ጸሎት አወጀች

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ መሪዎች ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በመላው ዓለም የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አማኞች የሚሳተፉበት ለአንድ ወር የሚቆይ የጾም እና ጸሎት አዋጅ ይፋ አድርገዋል።

መግለጫውን የሰጡት አመራሮች፦

የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ላኮ በዳሶ
ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ለወየው ስንሻው
የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ መጋቢ ተመስገን አዋኖ
የሥራ አመራር ቦርድ ጸሐፊ መጋቢ የኋላሸት ቡኩሉ

የጸሎቱ ዝርዝር መረጃ፦

1. መርሐ-ግብሩ ከየካቲት 30 እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ አንድ ወር ይቆያል።

2. ዓላማው ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ እና ስለ ሀገር ሰላም የሚጸለይበት ሲሆን፤

*የንስሐ፣
* የምስጋና እና
* የምልጃ ጸሎቶችን ያካተተ ነው።

3. በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሚገኙ መሪዎች፣ አገልጋዮችና ምዕመናን በሙሉ በጋራ በጸሎት እንዲተጉ ጥሪ ቀርቧል።

የሥራ አመራር ቦርድ ጸሐፊ ፓስተር የኋላሸት ቡኩሉ እንደገለጹት፣ ለጸሎቱ አጋዥ የሚሆኑ ሳምንታዊ የጸሎት ርዕሶች በቤተ ክርስቲያኒቱ ይፋዊ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ በየጊዜው የሚለቀቁ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን The Ethiopian Full Gospel Believers' Church

27/01/2026

ኢየሱስ ይመጣል!

19/10/2025

/ቤት_

ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም
‎በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የዳውሮ እና አከባቢ ሙሉ ወንጌል ክልል ጽ/ቤት የፕሬዝዳንት ሹመት አጽድቋል።

‎በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የዳውሮ እና አከባቢ ሙሉ ወንጌል ክልል ጽ/ቤት ለቀጣይ 5 ዓመታት የሚያገለግል የክልል ጽ/ቤት ፕሬዝዳንት ሹመትን አጸድቋል።

‎የዳውሮ እና አከባቢ ሙሉ ወንጌል ክልል ጽ/ቤት በ2008 ዓ.ም እውቅና ያገኘ ስሆን እንደ ቤተእምነቱ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ከዚህ በፍት 2ዙሪ ምርጫ አካሂዷል ።
‎ አሁን ለ3 ዙሪ ምርጫ የተካሄደ ስሆን /ቤት ተወክለው የመጡ ለቀጣይ 5 ተከታታይ ዓመታት የዳውሮ እና አከባቢ ሙሉ ወ/ል ክልል ጽ/ቤትን እንዲመሩ ዘንድ ወ/ዊ የክልል ፕሬዝዳንት እንዲሆን ሹመቱን ጸድቋል።በተጨማሪም በስራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ ክፍተት ባለበት ቦታ ወ/ዊ የወ/አስ/ሪ የማሟያ ምርጫ በማድረግ የመተካት ሥራ ተሰርቷል ።
አደራ ለተሰጣቸውም ሰዎች እጅ ከመጫን ጋር ጸሎት ተደርጓል።እንዲሁም በተለያዩ አጀንዳዎች ውይይትም ተደርጓል ለወንድሞቻችን መልካም የሥራ ዘመን ይሁንላቸው።

                      :00_ጀምሮ እሁድ ሙሉ ቀን"ስለ ወንጌል" በሚል ርዕሰ ልዩ የሆነ የአምልኮ ፕሮግራም ከጥቅምት 1-2/2018 በቶጫ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ስለተዘጋጀ በ...
07/10/2025



:00_ጀምሮ እሁድ ሙሉ ቀን
"ስለ ወንጌል" በሚል ርዕሰ ልዩ የሆነ የአምልኮ ፕሮግራም ከጥቅምት 1-2/2018 በቶጫ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ስለተዘጋጀ በቶጫ እና አከባቢው የምትገኙ ቅዱሳን ዕለተ ቅዳሜ ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ እሁድ ሙሉ ቀን ስለሚኖርን መጥታችሁ የበረከቱ ተካፋዮች እንድትሆኑ በጌታ ፍቅር እንጋብዛችኋለን ።


ቶጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተ ክርሰትያን
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን The Ethiopian Full Gospel Believers' Church
በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ን የማሪ አጥቢያ ቤ/ን
Christ Followers የክርስቶስ ተከታዮች
ኢየሱስ ይመጣል Jesus is coming

25/09/2025

በክርስቶስ ኢየሱስ
ጌትነትና አዳኝነት በማመን
ከሞት ወደ ህይወት
ከኃጢአት ወደ ጽድቅ
ከፍርድ ወደ ነጻነት ተሻገሩ

24/09/2025

በኃጢአት ላይ ድል የሚገኘው በክርስቶስ ጸጋ ብቻ ነው ። ኑ በእግዚአብሔር ልጅ እመኑ በኃጢአት ላይ ድል አግኙ።

23/09/2025

ለእኛ ግን መሸሸጊያችን
እግዚአብሔር 🙌🏼

19/09/2025

ኢየሱስ ያድናል!

18/09/2025

ወደ እግዚአብሔር የሚያደርስ ብዙ መንገድ የለም ። መንገዱ አንድ ነው እርሱም ጌታ ኢየሱስ ነው ።

Endereço

Tocha

Notificações

Seja o primeiro a receber as novidades e deixe-nos enviar-lhe um email quando ቶጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተ ክርሰትያን publica notícias e promoções. O seu endereço de email não será utilizado para qualquer outro propósito, e pode cancelar a subscrição a qualquer momento.

Entre Em Contato Com O Local De Adoração

Envie uma mensagem para ቶጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተ ክርሰትያን:

Compartilhar

Categoria