20/04/2026
ዳግም ትንሣኤ
{ሃሌታ በ፪} በከመ ይቤ እግዚእነ በወንጌል ግብረ ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ
ወነገርኩ ስመከ ለሰብእ፤ {ግ} አባ ወአቡየ ሰብሐኒ በስብሐቲከ ግብረ
ዘወብከኒ ፈጸመኩ ግብረ ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ፡፡
ትርጕም: ጌታችን በወንጌል "ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጸምኩ፡፡
ስምህን ለሰዎች አስተማርኩ፡፡ አባ አባት ሆይ ባንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር
አክብረኝ" እንዳለ፡፡ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጸምኩ{፪} ዮሐ ፲፯፥፬
ሃሌታ በ፬} ይቤ ክርስቶስ ነገርኩ ስመከ ለሰብእ፤ ከመ ያዕምሩከ ለአምላክ
ሕያው ቀድሶሙ አባ ከመ ይኩኑ ቅዱሳነ ዘእምኀቤከ፧ ኀበ ሀሎኩ አነ ህየ
የሀልው ምስሌየ፤ ወይንግሩ ስብሐትየ ወዘአቡየ ዘሀሎ እምቅድመ
ይትፈጠር ዓለም፡፡
ትርጕም
ክርስቶስ {ሲጸልይ} አባት ሆይ! ሕያው የባሕርይ አምላክ
አንተን ያውቁህ ዘንድ ስምክን ለሰዎች ነገርኩ አለ፡፡ {ምእመናን} እኔ
ካለሁበት ከእኔ ጋራ ይኖሩ ዘንድ፤ ዓለም ሳይፈጠር የነበረ የእኔን፣
የአባቴንም ክብር ይመሰክሩ ዘንድ ከአንተ በተገኘ ክብርም ፍጹማን
ይሆኑ ዘንድ አክብራቸው አለ፡፡ ዮሐ ፲፯፥፭