Elsa Hailu

Elsa Hailu እኛ ፍጥረቱ ነንና፣ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን ።

[አምላክ ሰው የሆነበት]
05/01/2024

[አምላክ ሰው የሆነበት]

የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አከባበር ከጥንት እስከ ዛሬ
********************

የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በአብዛኛው የዓለም ሀገራት በጎርጎሮሳዊያኑ የቀን አቆጣጠር ታኅሣሥ 25 ይከበራል።

የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች በብዛት በሚገኙባቸው እንደ ሩሲያ፣ ግሪክ፣ ዩክሬን እና ሮማኒያ ባሉ ሀገራት ደግሞ በዕሉ በጎርጎሮሳዊያኑ ጥር 7 ላይ ያርፋል።

በሀገራችን የልደት በዓል በየዓመቱ ታኅሣሥ 29 (በየአራት ዓመቱ /በዘመነ ዮሐንስ/ ደግሞ ታኅሣሥ 28) ላይ በተለያዩ ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ሥርዓቶች ተከብሮ ይውላል።

የልደት በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ፈጣሪ የሰውን ልጅ ለማዳን አንድያ ልጁን ለቤዛነት የሰጠበት (አምላክ ሰው የሆነበት) መሆኑ ስለሚታመን የሥጦታ በዓል ተደርጎ ይታሰባል።

ይህን መነሻ በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ክርስቲያኖች በዕለቱ የተለያዩ ስጦታዎችን ይሰጣጣሉ።

በሀገራችንም በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለክርስቶስ ልደት በዓል (ለገና) ፖስት ካርድን ጨምሮ ሌሎች ስጦታዎችን መለዋወጥ እየተለመደ መጥቷል።

የገና ዛፍን (ክሪስማስ ትሪ) በቀለማት እና በተለያዩ ጌጣጌጦች አስውቦ መስቀል የተጀመረው በ16ኛው ክፍለ ዘመን ጀርመን ውስጥ መሆኑ ይነገራል።

የልደት በዓልን በገና ዛፍ የማድመቅ ልምድ በእጅጉ እየተስፋፋ የመጣው ቪክቶሪያ ኢራ (ከ1837 እስከ 1901) ተብሎ በሚጠራው የእንግሊዝ ዘመነ መንግሥት ነው።

በአሁኑ ወቅት በዓለማችን በየዓመቱ ከ350 ሚሊዮን በላይ አርቴፊሻል የገና ዛፎች እንደሚሸጡ መረጃዎች ያመላክታሉ።

በኢትዮጵያ የገና መምጣትን ተከትሎ “የገና ጨዋታ” በስፋት ይዘወተራል። በገና ጨዋታ ወቅት ግጥሞችን መደርደር የተለመደ ነው። “በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ”፤ በገና ጨዋታ የለም ሎሌ ጌታ” እየተባለም ይገጠማል።

በተለይ ከበዓሉ ጋር በተያያዘ በየዓመቱ የባህል ስፖርት የሚከናወን ሲሆን ከተለያዩ ቦታዎች የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን በጃንሜዳ ተሰብስበው የገና ጨዋታ ውድድር ያካሂዳሉ።

የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን በዓሉን የማኅበራዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ይጠቀሙበታል። በበዓሉ ወዳጅ ዘመድ ይጠያየቃል፤ ዕለቱን በአብሮነት ያሳልፋል።

የገና አባት መነሻ ታሪክ በ4ኛው ክፈለ ዘመን ኔዘርላንድስ ውስጥ የነበሩ ቅዱስ ኒኮላስ የተባሉ ጳጳስ ናቸው። እኚህ አባት በልግስናቸው ስመ-ጥር እንደነበሩ የሕይወት ታሪካቸው ያስረዳል።

ይህንኑ ምሳሌ በማድረግ የገና አባቶች (ሳንታ ክላውስ) የሚባሉ ሙሉ ቀይ እና ነጭ ልብስ በመልበስ እና ረጅም አርቴፊሻል ነጭ ፂም በማድረግ ለልጆች ከረሜላ ያድላሉ።

በኢትዮጵያ የገና አባት የሚባሉት የገና ጨዋታን የሚመሩ አባቶች ናቸው፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን በከተማዎች አካባቢ የፈረንጆቹን የገና አባት (ሳንታ ክላውስ) መመልክቱ የተለመደ ሆኗል።

በኢዮብ መንግሥቱ

ዛሬስ ከእውቀት ከፍዬ አውቃለሁ""
04/01/2024

ዛሬስ ከእውቀት ከፍዬ አውቃለሁ""

17/12/2023

ሁሉ ስለዋወጥ አንተ ግን'

14/10/2023
👐
14/07/2023

👐

05/07/2023

ፀሐይ የምታበራው ብርሃን ለመስጠት ቢሆንም ጥላ እንዲከስት ታደርጋለች ። ፀሐይ ጥላ እንዲከስት እንደምታደርግ ሁሉ የክርስቶስም ብርሃን እምቢተኛነትንና ኃጢአትን ይገልጣል፣ኩነኔንም ያመጣል

02/07/2023

እግዚአብሔር ነገሠ፥ ክብርንም ለበሰ፤
እግዚአብሔር ኃይልን ለበሰ፥ ታጠቀም፤
ዓለምን እንዳትናወጥ አጸናት።

📖 እናንተ በመጽሐፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኃልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው ። ነገር ግን ሕይወት እንድሆናላችሁ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም ...
17/05/2023

📖 እናንተ በመጽሐፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኃልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው ። ነገር ግን ሕይወት እንድሆናላችሁ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም አላቸው ዮሐንስ ወንጌል 5÷39 - 40 ) ።

___________________________________
👉 እነዝህ ሰዎች ወደ ኢየሱስ በአካል ይመጡ ነበር ፣ በአጠገቡም ቆሞ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያስተምረውን ትምህርት ይከታተሉ ነበሩ ። ኢየሱስ ግን በአካል እንጅ ' ከእርሱ ጋር እንዳልነበሩ፣ መጽሐፋን እንጅ የመጽሐፋን ጌታ እንዳላወቁ ይናገር ነበር ። አይሁዳውያን ስለ "ቅዱሳት መጻሕፍት" ማለትም ስለ ብሉይ ኪዳን ባላቸው እውቀት ተኩራርተዋል ። ይሁንና የቅዱሳት መጻሕፍትን ምስክርነት አልተቀበሉም ። ብሉይ ኪዳን ስለ ክርሰቶስ በግልጽ ተናግሯል፣ ክርሰቶስ በመጣ ጊዜ ግን ሊቀበሉትም አልወደዱም ። አይሁዳውያን አንድ አሳዛኝ ስህተት ፈጸሙ ። በብሉይ ኪዳን የተጻፈውን የአይሁድ ሕግ ከፈጸምን የዘላለም ሕይወት እናገኛለን ይሉ ነበር ። ከዚህ የተነሣም በአይሁዶች አመለካከት አህዘቦች በመጀመሪያ የአይሁድን እምነት ስቀበሉ እግዚአብሔር ይቀበላቸዋል ይሉ ነበር ። ነገር ግን ይህ የአይሁዶች ሀሳብ የእነርሱ የባህላቸው እምነት እንጅ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሀሳብ አይደለም ። ምክንያቱም ወንጌል እሰከ ዓለም ዳርቻ ሁሉ እንድደርስ ከተፈለገ አህዛብ የራሳቸውን ባህል ትተው ወደ ይሁዳነት መለወጥ አያስፈልጋቸውም፤ የሚያሰፈልጋቸው ጌታ ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው መቀበል ብቻ ነበር ። የዘላለም ሕይወት ማግኘት የሚቻለው ክርሰቶስን በማመንና በማወቅ ብቻ ነው ፨

___________________________________
💪 እዚህ ላይ ኢየሱስ ግን ለአይሁዶች " #ወደ እኔ መምጣት አትፈልጉም" እንዳለ ልብ እንበል ። ሰዎች ወደ ክርሰቶስ መምጣት የማይፈልጉት ባለማወቃቸው ወይም የማስተዋል አቅማቸው ደካማ ስለሆነ አይደለም ። ሰዎች ወደ ክርሰቶስ የማይመጡት ፣ መምጣት " #ስለማይፈልጉ" ነው ።ምክንያቱም ብቻውን ሕይወት የሆነውን ጌታ ኢየሱስን ቅዱሳት መጽሐፍት እንደተናገረው ለመኖር ወይም ለማወቅ አለመፈለጋቸው ነው ። ምክንያቱም አይሁዶች የአእምሮ. እውቀት ብቻ ነበራቸው ። በአእምሮም የብሉይ ኪዳን 39 መጻሕፍትን ሸምደድዋል ። አዚህ ላይ አንድ ነገር ልንገርህ የአእምሮ እውቀት መጽሐፍ ቅዱሳን እንደማንኛውም መጽሐፍ እንደ ታሪክና ፈዚክስ በማጥናት በማንበብ በመሸምደድ የሚገኝ እውቀት ብቻ ነው ። የአእምሮ እውቀት ያለው ሰው ስለ እግዚአብሔር ያለው እወቀት ከሰዎች የሰማ፡ በታሪክ የተረዳ፡ ለራሱ መጽሐፍትን በማንበብ የሸምደድ ወዘተ. . . ስለዚህ ሰውየው ሰሚ እወቀት አለው ። ሰለዚህ ሰውየው የሚመራው. . . በታሪክ እና በአእምሮም በማንበብ በሸመደደው እውቀት ብቻ ነው ። እወቀቱ ደግሞም ከህይወቱ ጋር አልተዋሂደም ። ስለዚህ ሰውየው እያወቀ እየመሰለው ራሱን ያታልላል ። እወቀት እያለ እየመሰለው ራሱን ለተግባራዊው እወቀት ይዘጋል ። ይናገራል፣ ያሰተምራል ፣ ይሰበካል ፣ ይዘምራል ፣ የምናገረው ቃል የሰውን መንፈስ አይነካሙ ። በአካል እንጅ በመንፈስ ኢየሱስ ክርሰቶስ አላወቀም ። በልብ መንፈስ ከኢየሱስ ጋር አይመራሙ ፣ ኢየሱስ ደግሞ በአካል እንጅ በልብ በመንፈስ ከእርሱ ጋር የለም ፡ ስለዚህ ሰዎች ክርስቶስን አንፈልግም ሲሉ ሕይወትንም አንፈልግም ማለታቸው እንደነበር አላስተዋሉም ። እነርሱ የሚወዱት ጨለማን ነው ። ኃጢአታቸውን መተው አይፈልጉም ። ትመረምራለችሁ የአይሁድ መሪዎች ቅዱሳን መጽሐፍትን የሚያጠኑት ዝርዝር ጉዳይ ውስጥ ገብተው ነበር ። ይሁን እንጁ መጻሕፍቱ ከሁሉም አብልጠው የመሰከሩለትን በአእምሮ እንጁ በልብ በመንፈስ አላወቁትም ። በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ ለማግኘት ሲባል በውጫዊ ሁኔታ ሕግን ፈጽሚ በመምሰል በልብ ውስጥ ግን ሕግን ተላላፈ ሆኖ መገኘት ነው ። ይህ ዓይነቱ የሕግ አፈጽጸም የሕጉን መንፈስ ችላ በማለት ለጥሬ ትርጒሙ ትኲረት ይሰጣል ። ኢየሱስ የፈሪሳውያንን የሕግ አተሪጓጉምንና በሥራቸው ለመጽደቅ ያላቸውን አመለካከት አጥብቆ ታቃወሞአል ። አበክሮ ያስተማረውም በእርሱና በፈጸመው ሥራ ብቻ በማመን የሚገኘውን ጽድቅ ብቻ ነው ።

10/05/2023

እኔም አይቻለሁ እርሱም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ መስክሬአለሁ ፣ እመሰክራለሁ ።

Address

Nairobi

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Elsa Hailu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Elsa Hailu:

Share