ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት / Nairobi Meserete Haimanot Sunday School

  • Home
  • Kenya
  • Nairobi
  • ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት / Nairobi Meserete Haimanot Sunday School

ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት /  Nairobi Meserete Haimanot Sunday School ይህ ይፋዊ የደ/መ/መ/ቤተክርስቲያን የመሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት የፌስቡክ ገጽ ነው::

ርደተ መንፈስ ቅዱስ ወይንም የመንፈስ ቅዱስ መውረድ በብሉይ ኪዳን በትንቢት የተነገረና  በሐዲስ ኪዳን የተፈጸመ ነው፡፡ ነቢዩ ኢዮኤል ስለ መንፈስ ቅዱስ ወደዚህ ዓለም መውረድ፣ በመንፈስ ቅዱ...
31/05/2026

ርደተ መንፈስ ቅዱስ ወይንም የመንፈስ ቅዱስ መውረድ በብሉይ ኪዳን በትንቢት የተነገረና በሐዲስ ኪዳን የተፈጸመ ነው፡፡ ነቢዩ ኢዮኤል ስለ መንፈስ ቅዱስ ወደዚህ ዓለም መውረድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ሀብትነት ዓለም እንደሚታነጽና ሃይማኖት እንደሚጸና እንዲህ ሲል ተናግሯል፤ ‹‹ከዚህም በኋላ እንዲህ ይሆናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈሳለሁ፡፡›› (ኢዩ. ፪፥፳፰)
👉በሉቃስ ወንጌል እንደተጻፈው ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ድኅነተ ዓለምን ፈጽሞ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በ፵ኛው ቀን ወደ ሰማየ ሰማያት በሚያርግበት ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን ይዞ ወደ ቢታንያ ከወጣ በኋላ በተስፋ እንዲጠብቁና ከሰማይ የሚወርደውን መንፈስ ቅዱስ እስከሚጎናጸፉ ድረስ የእግዚአብሔርን ትእዛዛ እንዲጠበቁ እንዲህ ሲል አዘዛቸው፤ ‹‹እነሆ፥ እኔ የአባቴን ተስፋ ለእናንተ እልካለሁ፤ እናንተ ግን ከአርያም ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ተቀመጡ፡፡›› ከዚህም መመሪያ በመነሣት አባቶቻችን የአምላካቸውን ትእዛዝ አክባሪዎችና ጠባቂዎች በመሆናቸው ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው በቤተ መቅደስ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ቆዩ፡፡ (ሉቃ. ፳፬፥፵፱)
👉ከዚህም በኋላ ዓለምን ዞረው በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በሁሉም ቋንቋ ተናገሩ፤ አስተማሩም፡፡ ‹‹ኀምሳው ቀንም በተፈጸመ ጊዜ ሁሉም በአንድነት በአንድ ቦታ ተሰብስበው ነበር፡፡ ድንገትም እንደ ዐውሎ ነፋስ ድምፅ ያለ ከሰማይ ድምፅ መጣ፤ የነበሩትንም ቤት ሞላው፡፡ እንደ እሳት የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎችም ታዩአቸው፤ በሁሉም ላይ ተቀመጡባቸው፡፡ ሁሉም መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ፤ ይናገሩ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እንደ አደላቸው መጠንም እየራሳቸው በሀገር ሁሉ ቋንቋ ይናገሩ ጀመር›› እንዲል፤ (ሐዋ. ፪፥፩-፬)
👉ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንም ስለ ወረደው መንፈስ ቅዱስ አምስት መሠረታዊ ትርጓሜ እንዳሉት ያስተምራሉ፡፡ እነርሱም፤

፩ኛ. መንፈስ ቅዱስ ናዛዚ ነው፤ ትርጓሜውም አረጋጊ ወይንም የሚያረጋጋ ማለት ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ያልተረጋጉትን ያረጋጋልና፤ ወንጌል ሲሰበክ የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ ሰዎችን ወይንም ምእመናን የሚያረጋጋ ኃይል ነው፡፡
፪ኛ. መንፈስ ቅዱስ መጽንዒ ወይም የሚያጸና ነው፤ በተለያዩ ዘመናት የተነሡ ነቢያት፣ ቅዱሳን አባቶችና ሐዋርያት እንዲሁም ጻድቃን ሰማዕታትም ሰይፉና ስለቱን የታገሡት፣ መከራና ሥቃዩን የቻሉትና መስቀሉን የተሸከሙት አጽናኒው መንፈስ ቅዱስ በውስጣቸው ስላደረባቸው ነው፡፡
፫ኛ. መንፈስ ቅዱስ መንጽሒ ወይም የሚያነፃ ነው፤ የሰዎችን ኃጢአት የሚያስወግድ፣ ከእድፋችን የሚያነጻ፣ ሰውነትን ለእግዚአብሔር ማደሪያ የሚያዘጋጅ ነው፡፡
፬ኛ. መንፈስ ቅዱስ ከሳቲ ወይም ምሥጢር የሚገልጽ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ነቢዩ ሙሴና ዕዝራን ስንመለከት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በየዘመናቱና በየደረጃው ምሥጢራትን እየገለጸላቸው መጻሕፍትን ጽፈዋል፡፡
፭ኛ. መንፈስ ቅዱስ መስተፍስሒ ወይም የሚያስደስት ነው፤ ያዘኑ ሰዎችን ከኀዘን ያወጣል፤ ኀዘናቸውንም ወደ ደስታ ይቀይራል፤ ሐዋርያት በተዘጋ ቤት ተቀምጠው ያዝኑ ነበር፤ ጌታችን ወደ ሰማይ ባረገ ሰዓት ግን አጽናንቷቸዋል፡፡ ‹‹እስከ ዓለም ፍጻሜ በዘመኑ ሁሉ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ›› እንዲል፤ ምክንያቱም የማይለይ የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ሰጥቷቸዋልና ለዘለዓለም ከእነርሱ ጋር ይኖራል፡፡ (ማቴ. ፳፰፥፳)
እንኳን አደረሳችሁ!

ቤተሰብ እንሁን ለሌሎችም እናጋራ
🔎ዩቱዩብ ቻናል፦https://youtube.com/channel/UCez7ZZH--fX056XMW64P2CA
🔎 ፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday...
🔎 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/MesreteHaimanot27

†ደብረ ምጥማቅ †=>የአርያም ንግሥት: የሰማይና የምድር እመቤት: የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚሕች ዕለት በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::+ጥንተ ነገሩስ እን...
29/05/2026

†ደብረ ምጥማቅ †

=>የአርያም ንግሥት: የሰማይና የምድር እመቤት: የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚሕች ዕለት በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::

+ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:

+ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮዽያ በተሰደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ: ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ አርፎ ነበር:: ቦታውን ባርኮ ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን ብሎም ቃል ኪዳን ገብቶላት ነበር::

+ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት ቤት ሆነ:: እመቤታችንም በልጇ ፈቃድ ግንቦት 21 ቀን አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት መጣች::

+በዚያ ሕዝበ ክርስቲያንም: አሕዛብም ተሰብስበው ለ5 ቀናት ከእመ ብርሃን ጋር ይሰነብታሉ:: እንግዲህ ልብ በሉት:-
እንኩዋን የአርያም ንግስት: የአምላክ እናቱ እመቤታችንን ይቅርና በዚሕ ዓለም ሰይጣን ቤቱ ያደረጋቸውን: የመዝናኛው ኢንዳስትሪ ዝነኛ ሰዎችን ለማየት የዘመናችን ሰው እንዴት እንደሚቸኩል::

+እመቤታችንን በአካል መመልከት አይደለም ስሟን መጥራት ነፍስን ከሥጋ መለየት የሚችል ጣዕምና ደስታ አለው:: ባይሆን ይሔ ለሚገባውና ላደለው ብቻ ነው::

+የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች ከእመቤታችን ጋር የሚቆዩባቸው ቀናት የዘለዓለም የሕይወት ስንቅ የሚይዙባቸው ናቸው:: ፈልገው የሚያጡት: ጠይቀው የማይፈጸምላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት: ሐዋርያት: ጻድቃን: ሰማዕታት: ደናግል: መነኮሳት: መላዕክትና ሊቃነ መላእክት ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበርና:: እመ ብርሃንም እየመላለሰች ትባርካቸው ነበር::

+እነዚያ እርሷን ያዩ ዐይኖች: በፊቷ የቆሙ እግሮች ክብር ይገባቸዋል:: 5ቱ ዕለታት ሲፈጸሙ ሕዝቡ እመቤታችንን በዕንባ ይሰናበቷታል:: እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው ከቅዱሳኑ ጋር ታርጋለች::
@ዝክረ ቅዱሳን

ዕርገተ እግዚእ =>ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዓለ ዕርገትን 2 ጊዜ ታከብራለች:: አንዱ "ጥንተ በዓል": ሁለተኛው ደግሞ "የቀመር በዓል" ይሠኛል:: ጥንተ በዓል ማለት ጌታችን በትክክል ያረገ...
21/05/2026

ዕርገተ እግዚእ

=>ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዓለ ዕርገትን 2 ጊዜ ታከብራለች:: አንዱ "ጥንተ በዓል": ሁለተኛው ደግሞ "የቀመር በዓል" ይሠኛል:: ጥንተ በዓል ማለት ጌታችን በትክክል ያረገበትን ቀን ያመለክታል::

+የክብር ባለቤት መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በኪነ ጥበቡ (በሕማሙ: በሞቱ) ዓለምን አድኖ: 40 ቀን ለሐዋርያቱ መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓትን አስተምሯቸዋል::

+በ40ኛው ቀን 120ውን ቤተሰብ ይዟቸው ወደ ቢታንያ ወጣ:: በዚያም እስከ ሊቀ ዽዽስና ድረስ ሾሟቸው: ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡም አዟቸው የመንፈስ ቅዱስን ተስፋ ጠብቁ ብሏቸዋል:: እየባረካቸው በተዋሐደው ሥጋ ወደ ሰማያዊ ዙፋኑ አርጉዋል::

+ሰማያት: ምድር: ደመናት: ነፋሳት: መባርቅትና መላእክት: ፍጥረት በሙሉ አመስግኗል:: አይሁድ መናፍቃን እርገቱን ምትሐት ነው እንዳይሉ: ጌታችን ትንሳኤውን አማናዊ እንደሆነ ለማስረዳት በ40ኛው ቀን ዐረገ::

+አንድም ራስ ባለበት ሌሎች የሰውነት ክፍሎች ሊኖሩ ይገባልና ጌታችን ዕርገቱን በገሃድ አደረገው:: "ዐርገ እግዚእ ከመ ያለቡ ዕርገተ ጻድቃን ንጹሐን" እንዲል::

(መዝ. 46:6)

=>ከበረከተ ዕርገቱ ይክፈለን::

+"+ እስከ ቢታንያም አወጣቸው:: እጆቹንም አንስቶ ባረካቸው:: ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ:: ወደ ሰማይም ዐረገ:: እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ:: ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ:: +"+ (ሉቃ. 24:50-53)

ዝክረ ቅዱሳን

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ::የእመቤታችን የልደት ክብረ በዓል በናይሮቢ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በሥርዓተ ቅዳሴ በዝማሬ ...
09/05/2026

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ::

የእመቤታችን የልደት ክብረ በዓል በናይሮቢ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በሥርዓተ ቅዳሴ በዝማሬ እና የክበረ በዓል ዝክር በማዘጋጀት በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ዋለ::

የአባቶቻችን አምላክ ቅዱስ እግዚአብሔር የተመስገነ ይሁን::

ልደታ ለማርያምእንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሰን!!!ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከተለዩ የተለየች፣ ከተመረጡ የተመረጠች ክብርት እናታችን ቅድስት ድን...
09/05/2026

ልደታ ለማርያም

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሰን!!!

ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከተለዩ የተለየች፣ ከተመረጡ የተመረጠች ክብርት እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በከበረች ቀን ግንቦት አንድ ቀን ተወለደች፡፡ የመወለዷም ነገር እንዲህ ነው፡፡ በጥሪቃና ቴክታ የተባሉ የእግዚአብሔር ሰዎች ነበሩ፤ ባለጸጎች ቢሆንም ልጅ ግን አልነበራቸውም፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ቴክታ ሕልም አለመች፡፡ ለባሏም እንዲህ ስትል ነገረችው «በራእይ ነጭ ዕንቦሳ ከማሕፀኔ ስትወጣ፤ ያችም ዕንቦሳን እየወለደች እስከ ፮ ትውልድ ስትደርስ ፮ኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃ ደግሞ ፀሐይን ስትወልድ አየሁ» አለችው፡፡ (ውዳሴ ማርያምና ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ)

ባሏ በጥሪቃም «ራእዩስ ደግ ነው፤ የሚፈታልን የለም እንጂ» አላት፡፡ በማግሥቱ ለሕልም ፈቺ ሔዶ ነገረው፡፡ ሕልም ፈቺውም «እግዚአብሔር በምሕረቱ አይቷችኋል፤ በሣህሉ መግቧችኋል» ብሎ ፮ቱ እንስት ጥጆች መውለዳቸው ፯ ሴቶች ልጆች እንደሚወልዱ፤ ፯ኛይቱ በጨረቃ መመሰሏ ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት እንደሚወለዱ፤ የፀሐይ ነገር ግን እንደንጉሥ ያለ ይሆናል አልተገለጸልኝም ብሎ ነገረው፡፡ (ነገረ ማርያም)

በጥሪቃም ለሚስቱ ሔዶ የሕልሙን ፍቺ ነገራት፡፡ በዚያም ወር የመጀመሪያዋ ሴት ልጅ ተፀነሰች፡፡ በተወለደች በ፰ኛው ቀን ሄኤሜን አሏት፤ ወላጆቿም በሥርዓት አሳደጓት፡፡ እርሷም ለአቅመ ሔዋን ስትደርስ ባል አግብታ ሴት ልጅ ወለደች፤ የሄኤሜን ልጅም ዴርዴን ትባል ነበር፡፡ ዴርዴንም እንዲሁ አድጋ ቶና የምትባል ሴት ልጅ ወለደች፡፡ ቶና ደግሞ ሲካርን ወለደች፤ሲካርም ሔርሜላን ወለደች፤ ሔርሜላም በሥርዓት አድጋ ባል ካገባች በኋላ ሐና የተባለች ልጅ ወለደች፤ሐና ማለትም በሃይማኖትና በምግባር የጸናች፤ በንጽሕና በቅድስና የኖረች ቡሩክት ክብርት ልዕልት ማለት ነው፡፡ የሐና ወላጆች ልጃቸውን በሥርዓት አሳደጓት፡፡ ለአካለ መጠን ስትደርስም ኢያቄም የተባለውን ጻድቅ ሰው አጋቧት፡፡ ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑም ኖረዋለወ። በዚያ ወራት የመካኖች መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና፡፡ እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር፡፡ እናም ባልና ሚስቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ፤ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ሐሳባቸውን ተመለከተ፡፡ ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው፡፡

በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ፤ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት። ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች። ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገነች። የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች፡፡

ከዚህም በኋላ ሐምሌ ፴ ኢያቄም ለሐና ራእይ አየ፤ ነጭ ርግብ ፯ቱን ሰማያት ሰንጥቃ ወርዳ በራሷ ስታርፍ በቀኝ ጆሮዋ ገብታ በማኅፀኗ ስታድር አየ፤ ሐናም ለኢያቄም ፀምራ ሲያስታጥቀህ መቋሚያህ አብባ አፍርታ ፍጥረት ሁሉ ሲመገባት አየሁ ብላ» ነገረቸው፡፡

ነሐሴ በባተ በሰባተኛው ቀን በዕለተ እሑድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተፀነሰች፡፡ በ፶፻፬፻፹፭ ዓመተ ዓለም በግንቦት ፩ ቀንም እመቤታችን ድንግል ማርያም ከሐና እና ከኢያቄም፡፡ በ፰ኛው ቀንም ስሟን ‹ማርያም› ብለው ሰየሟት፤ በዚህ ዓለም ካሉት ምግቦች ሁሉ ጣፋጭ «ማር» በመሆኑ እንዲሁም በገነት ካሉት ምግቦች ደግሞ «ያም»ን የሚያህል ጣፋጭ ባለመኖሩ «ማርያም» አሏት፡፡ ትርጓሜውም ‹እመቤት› ነው። ‹ደግሞም ሀብታና ስጦታ› ማለት ነው፡፡ በእውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ሁላችን በእርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነትን ያገኘንባት ናትና።

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አምላካችን እግዚአብሔር ከበዓሉ ረድኤትና በረከት ይክፈለን!
ከመጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ግንቦት

የሚያዚያ 23 ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ዕረፍቱ ዓመታዊ በዓል በመርሳቤት በዳሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከበረ። በበዓሉም የናይሮቢ ደ/መ/መድኃኔዓለም ቤ/ክ ዋና አ...
01/05/2026

የሚያዚያ 23 ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ዕረፍቱ ዓመታዊ በዓል በመርሳቤት በዳሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከበረ።

በበዓሉም የናይሮቢ ደ/መ/መድኃኔዓለም ቤ/ክ ዋና አስተዳዳሪ ሊቀብርሃናት ቀሲስ ሄኖክ ይግዙ እና ዋና ጸሐፊ ሊቀስዩማን ቀሲስ አክሊሉ ካህናት አባቶች ዲያቆናት ወንድሞች ምእመናን ወምእመናት ተገኝተዋል::

የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በረከትና ረድኤት አይለየን!

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  የትንሣኤ በዓል አደረሳችሁየትንሣኤ ሥርዓተ ማኅሌት ከደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያንሚያዝያ 3/2018 ዓ.ም
12/04/2026

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ

የትንሣኤ ሥርዓተ ማኅሌት ከደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን

ሚያዝያ 3/2018 ዓ.ም

ቀዳሚ ሥዑር ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፣ትንሣኤሁ አግሀደ:
11/04/2026

ቀዳሚ ሥዑር
ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፣
ትንሣኤሁ አግሀደ:

ለምን   ( ) (የስቅለት ማግስት ) ላይ ቄጤማ ይታደላል ወይንም ይደረጋል ???ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰይህቺ ቅዳሜ በእነዚህ ስሞች ትታወቃለች  ( )፤   ፤ ( )   ፤...
11/04/2026

ለምን ( ) (የስቅለት ማግስት ) ላይ ቄጤማ ይታደላል ወይንም ይደረጋል ???
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
ይህቺ ቅዳሜ በእነዚህ ስሞች ትታወቃለች
( )፤ ፤ ( )

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
፤ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ ከፈጸመ በኋላ ያረፈባት ስለሆነች፤ የእግዚአብሔር የዕረፍት ዕለት፤ ቀዳሚት ሰንበት (የዕረፍት ቀን) ትባላለች፡፡
(ታላቋ ሰንበት)፤ የመጀመሪያዋ ሰንበት በመሆኗ ታላቋ ሰንበት ትባላላች፡፡
( )፤ እግዚአብሔር ሥነ ፈጥረትን ከመፍጠር ዕረፍት እንዳደረገባት ዅሉ፣ የፍጥረት ርእስ የኾነውን አዳምን ለማዳን ሕማምና ሞት የተቀበለው አምላካችን ክርስቶስ በከርሰ መቃብር አርፎባታል፡፡ (ማቴ. ፳፯፥፷፩)፡፡
፠ ‹ሥዑር› የተባለችበት ምክንያትም በዓመት አንድ ቀን ስለምትጾም (የጾም ቀን በመኾኗ) ነው፡፡
የጌታችን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያትና ሌሌችም የጌታ ወዳጆች ጌታችን ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት ጀምሮ ብርሃነ ትንሣኤውን እስኪያዩ ድረስ እህል ውኃ በአፋቸው አልዞረም፡፡ ይመኩበትና ተስፋ ያደረጉት የነበረ አምላካቸው በመቃብር ስላረፈ ዕለቷን ሞቱን በማሰብና ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡
፠ የቻልን ሕዝበ ክርስቲያንም ይህን መነሻ በማድርግ ከዐርብ ጀምረን በማክፈል (በመጾም) እህል ውኃ ሳንቀምሱ ለሁለት ቀናት እናድራለን (እንካፍላለን)፡፡ እንደ ዋልድባና ማኅበረ ሥላሴ ባሉ ገዳማት ያሉ ታላላቅ አባቶችና ወንድሞች ደግሞ ከሆሳዕና አንዳንዶችም ከዕለተ ረቡዕ ጀምረው ለ7ት ቀናት ወይም ለ3ት ቀናት ያከፍላሉ፡፡

፤ ( )
ቅዳሜ የጠዋቱ ጸሎት ሲፈጸም ካህናቱ ‹‹ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፤ (በመስቀሉ ሰ
ላምን አደረገ፥ መሠረተ)›› እያሉ በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰቡ ምእመናን የምሥራች ቄጠማ ያድላሉ፡፡
፠ ቄጠማው በኖኅ ዘመን በንፍር ውኃ ምደር በተጠለቀለቀች ጊዜ፤ ኖኅ ወደ መርከብ ይዟቸው ከገባው እንስሳት መካከል የውኃውን መጉደል ለመረዳት ርግብን በመርከብ መስኮት አሾልኮ ልኮ እርሷም ቄጠማ በአፏ ይዛ በመመለስ የምሥራች ምልክት፥ የውኃውን መድረቅ እንደተነገረችውና እንደተደሰተ ሁሉ (ዘፍ. ፱፥፩-፳፱)፡፡ ‹‹በክርስቶስ ሞት፤ ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ፤›› ስንል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ጠዋት ደባትር መዘምራን ዝማሬን ካቀረቡ በኋላ ለልጆቿ ቄጠማ ታድለናለች፡፡ የምሥራች ተምሳሌት የኾነውን ቄጠማም፤ ከሲኦል ቃጠሎ ወደ ጥንተ ማኅደራችን ገነት መመለሳችንን ለመመስከር በግንባራችን እናስረዋለን፡፡
፤ ለ5500 በሲኦል ሲማቅቁ የነበሩ ነፍሳትን ሰላም ለሁላችሁን ይሁን ብሎ ወደ ገነት አስገብቷቸዋልና፤ ይህች ቅዳሜ ቅዱስ (የተለየች) ቅዳሜ ትባላለች፡፡
አውረድዎ፥ አውረድዎ፥ አውረድዎ እምዕፅ፤
ወአምጽኡ አፈዋተ ከርቤ ሕዉስ፡፡

ቤተሰብ እንሁን ለሌሎችም እናጋራ

🔎ዩቱዩብ ቻናል፦https://youtube.com/channel/UCez7ZZH--fX056XMW64P2CA
🔎 ፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School
🔎 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/MesreteHaimanot27

Address

Nairobi

Telephone

+254740111336

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት / Nairobi Meserete Haimanot Sunday School posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share