ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት / Nairobi Meserete Haimanot Sunday School

  • Home
  • Kenya
  • Nairobi
  • ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት / Nairobi Meserete Haimanot Sunday School

ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት /  Nairobi Meserete Haimanot Sunday School ይህ ይፋዊ የደ/መ/መ/ቤተክርስቲያን የመሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት የፌስቡክ ገጽ ነው::

እንኳን አደረሳችሁ 🙏ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን እረፍት ሲያስቡት ሊቃውንት አባቶቻችን “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ፣ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” “መዋቲ ለሆ...
22/08/2026

እንኳን አደረሳችሁ 🙏

ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን እረፍት ሲያስቡት ሊቃውንት አባቶቻችን “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ፣ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” “መዋቲ ለሆነ ሰው ሞት ይገባዋል የማርያም ሞት ግን ለሁሉም ይገርማል” ይላሉ፡፡ ይህስ እንደምን ነው ቢሉ፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በ64 ዓመቷ በጥር በ21 ቀን በ49 ዓ.ም አርፋለች፡፡ ጥር ልደታ ሰኞ ነበር፣ ስምንት፣ አስራ አምስት፣ ሃያ ሁለት እያለ ሰኞ ላይ ይውላል፡፡ እመቤታችን እሁድ በ21 አርፋለች፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት በአጎበር አድርገው ሊቀብሯት ሲሔዱ፣ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ከዚህ ቀደም ልጇን ተነሳ አረገ እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ፡፡ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች አረገች እያሉ ሊያወርኩን አይደለምን? ለምን ስጋዋን በእሳት አናቃጥለውም ብለው ተነሱ፡፡ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊም ተራምዶ አጎበሯን ቢይዘው መልአክ ሁለት እጁን በሰይፍ ቀጣውና ተንጠልጥሎ ቀረ፡፡ ኋላም ማረው ብላ እመቤታችን አማልዳው መልሶለታል፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ደንግጠው ተበታተኑ፡፡

እመቤታችንንም ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ነጥቆ በገነት አኖራቸው፡፡ ቆይቶ ዮሐንስን አግኝተው የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ አሉት። እርሱም በገነት ከእፀ ሕይወት ስር አለች አላቸው፡፡ እነርሱም ዮሐንስ ይህን ድንቅ ነገር አይቶ እኛ ሳናይ ቀረን ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ፡፡ ነሐሴ እንደ ጥር ሁሉ ሰኞ ነው የሚብተው፡፡ ከሰኞ እስከ ሰኞ 8፣ ከሰኞ እስከ ሰኞ 15 ይሆናል፡፡ እሁድ በ14 ጌታችን ቅዱስ ስጋዋን ሰጥቷቸው ቀብረዋታል፡፡

ይህ ሁሉ ሲሆን ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አልነበረም፡፡ ከሦስት ቀን በኋላ በ16 እንደ ልጇ ከሙታን ተነስታ ስታርግ እርሱ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ሲመለስ አገኛት፡፡ በጣም አዘነ፣ ተበጸበጻ “እንደኔ ያለ እድለ ቢስ ማን አለ ቀድሞ የልጅሽን የጌታዬን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን” በማለት ከሚጓዝበት ደመና ሊወድቅ ቃጣው፡፡ እመቤታችንም “አይዞህ አትዘን ወንድሞችህ ትንሣኤዬን እርገቴን አላዩም አንተ ግን አይተሃል፤ እመቤታችን ተነሳች አረገች ብለህ ንገራቸው” ብላ የያዘችውን ሰበን (መግነዝ) ሰጥታ ሰደደችው፡፡

እርሱም ሐዋርያትን ሲያገኛቸው “የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ?” አላቸው፡፡ “አግኝተን ቀበርናት” አሉት፡፡ “ተው ይህ ነገር አይመስልም ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር?” ሲላቸው ቅዱስ ጴጥሮስ ተቆጥቶ አንተ ወትሮውንም መጠራጠር ልማድህ ነው፣ ብቻህን ተጠራጥረህም አትቀርም ሌላውንም ታጠራጥራለህ ብሎ ወደ መቃብሯ እየሮጠ ሔዶ ቢከፍተው አጣት፤ ደንግጦ ቆመ፡፡ ቶማስም አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችንስ ተነሳች አረገች አላቸው፡፡

እነርሱም በዓመቱ ቶማስ ትንሳኤሽን እርገትሽ አይቶ እኛ ሳናይ ቀረን ብለው በነሐሴ አንድ ቀን ጾም ጀምረው ሁለት ሱባኤ ጾመው በአስራ አምስት አጠናቀዋል፡፡ በትንሣኤዋ ቀን በ16 ጌታችን እርሷን መንበር አድርጎ ጴጥሮስን ተራዳኢ ካሕን ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ አቁርቧቸዋል፡፡ እርሷንም እንዲህ አድርጎ አክብሯታል፡፡ ሊቃውንት አባቶች “ወተቄረበት በእደ ወልዳ” እንዲሉ እርሷም በልጇ እጅ ቆርባለች፡፡

የንግስተ ሰማይ ወምድር ልመናዋ፣ ክብራ፣ የልጇ የወዳጇ ቸርነት በኛ ላይ አድሮ ይኑር አሜን!!!

√ የዩቲዩብ ገጻችንን
https://youtube.com/?si=gKXqEbltFIjp0p3h

√ ፌስቡክ ገጻች
https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School

√ የቴሌግራም ገጻችንን
https://t.me/MesreteHaimanot27

ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎች ያጋሩ

ከጌታችን ከመድኃኒታች ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆነው የደብረ ታቦር በዓል በደብራችን ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በድምቀት ተከበረ...
20/08/2026

ከጌታችን ከመድኃኒታች ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆነው የደብረ ታቦር በዓል በደብራችን ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በድምቀት ተከበረ::
ለዚህ ዓመት ያደረን ቸሩ መድኃኔዓለም ከመጪው ዓመት ይደምረ::

🔎ዩቱዩብ ቻናል፦https://youtube.com/channel/UCez7ZZH--fX056XMW64P2CA
🔎 ፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School
🔎 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/MesreteHaimanot27

እንኳን አደረሳችሁ 🙏ደብረ-ታቦር (ቡሄ) የኢትየጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው ዘጠኝ ዓበይት በዓላት አንዱ የደብረ ታቦር በዓል ነው። በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን የሚከበረ...
19/08/2026

እንኳን አደረሳችሁ 🙏

ደብረ-ታቦር (ቡሄ)
የኢትየጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው ዘጠኝ ዓበይት በዓላት አንዱ የደብረ ታቦር በዓል ነው። በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን የሚከበረው ይህ በዓል መሠረቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
ደብረ ታቦር ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ደቀመዛሙርቱን ይዞ ወደ ተራራው የወጣበትና ፊቱ እንደ ፀሐይ የበራበት፣ ልብሱም እንደብርሃን ነጭ የሆነበት፣ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ተራራ ነው።

የማቴዎስ ወንጌል ምዕ፣17÷1--8
"ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ።
እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ። እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው።
በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ። ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር።
ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና፡ ተነሡ አትፍሩም አላቸው። "

፨ዓቢይ መሰረቱ ይህ ሲሆን፣ በቤተ ክርስቲያን ደብረታቦር ከቤተክርስቲያን ውጭ አከባበሩ "ቡሄ" እየተባለ የሚከበረው በዓል በሀገራችን በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡

፨"ቡሄ" ማለት ብራ፣ ብርሃን፣ ደማቅ ገላጣ፣ የተገለጠ ማለት ነው፡፡ ቡሄ ሲመጣ የክረምቱ ጨለማነት አልፎ ወደ ብርሃን፣ ወደ ጥቢ የሚያመራበት፣ ወደ መፀው የሚዘለቅበት ወገግታ ፣ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት፣ የሚሸጋገርበት ወቅት በመሆኑ ከቡሄ በኋላ የጠነከረ ክረምት አይኖርም፡፡

፨በዚህ መሰረት የክረምቱ አፈና ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታየውም በዚህ በዓል አካባቢ ስለሆነ ይቺ ዕለት 'ቡሄ' የሚለውን ስያሜ አገኘ። ቡሄ ማለት ገላጣ፣ የተገለጠ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት፣ ብረሃን የታየበት ድምጸ መለኮት የተሰማበት ስለሆነ፤ ችቦ ስለሚበራ የብርሃን በዓል በማለት የቡሄ በዓልም ይባላል፡፡

በገጠርም ሆነ በየከተማው ልጆች ጅራፋቸውን ገምደው ሲያጮሁ ይሰነብታሉ። እናቶችም ለበዓሉ ዝግጅት ስንዴ ሲለቅሙ፣ ሲፈትጉ፣ ሲፈጩ ይሰነብታሉ። መነሻ የሆናቸው ትውፊት ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ዕለት ጊዜው ምሽት ነበር፡፡ እረኞችም ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጥተዋል
ያንን ለማስታወስ «ቡሄ» ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና ችቦ በማብራት በዓሉን የሚከበረው ከዚህ በመነሣት ነው፡፡

የንጋት ወጋገን ሲፈናጠቅ ልጆች በከባድ ድምጽና በጅራፍ ጩኸት የሚታጀብ፣ በገደላገደል ስር እንዲያስተጋባ ተደርጎ ብዛት ባላቸው ህጻናት በከፍተኛ ድምጽ የሚዘመር ነው ቡሄ ። የጅራፉ ጩኸትም እግዚአብሔር አብ “የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት” ሲል ሐዋርያት ራሳቸውን ስተው የወደቁበትን የመለኮት ድምፅ ለማስታወስ ነው፡፡

✥┈ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ┈✥

√ የዩቲዩብ ገጻችንን
https://youtube.com/?si=gKXqEbltFIjp0p3h

√ ፌስቡክ ገጻች
https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School

√ የቴሌግራም ገጻችንን
https://t.me/MesreteHaimanot27

ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎች ያጋሩ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ማሴኖ ቅዱስ ሚናስ እና አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን::በየዓመቱ የጻድቁ አባታችን የተክለሃይማኖት  በዓ...
15/08/2026

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::

ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ማሴኖ ቅዱስ ሚናስ እና አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን::

በየዓመቱ የጻድቁ አባታችን የተክለሃይማኖት በዓለ እረፍት ምክንያት በማድረግ ለነሐሴ 23 እስከ 25 ይደረጋል በዚህም የበረከት ጉዞ ላይ ከወዲሁ እንድትመዘገቡ፣እንድትሳተፉ እናሳስባለን::

🔎ዩቱዩብ ቻናል፦https://youtube.com/channel/UCez7ZZH--fX056XMW64P2CA
🔎 ፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School
🔎 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/MesreteHaimanot27

በናይሮቢ ደ/መ/መ/ቤ/ክ በመሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ከግንኙነት ክፍል ጀምሮ እስከ ስንበት ት/ቤት ሰብሳቢነት ለረጅም ጊዜ ሲያገለግል  የቆየው ወንድማችን አብዮት በለጠ እና  በመዝሙር...
28/07/2026

በናይሮቢ ደ/መ/መ/ቤ/ክ በመሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ከግንኙነት ክፍል ጀምሮ እስከ ስንበት ት/ቤት ሰብሳቢነት ለረጅም ጊዜ ሲያገለግል የቆየው ወንድማችን አብዮት በለጠ እና በመዝሙር ክፍል ስታገለግል የቆየችው እህታችን ፍሬሕይወት የመጡበት ዓላማ ተሳክቶ ወደ ሦስተኛ ሀገር ሲሄዱ በግንኙነት ክፍል የምስክር ሰርተፌኬት እና ስጦታ በመስጠት ከአባላት ጋር ማስታወሻ ፎቶ በመነሳት የሽኝት መርሃ ግብር ተከናውኗል። በምትሄዱበት ቦታ ሁሉ ያገለገላችሁት መድኃኔዓለም የልባችሁን መልካም ሃሳብ እንዲፈጽምላችሁ እንመኛለን።

🔎ዩቱዩብ ቻናል፦https://youtube.com/channel/UCez7ZZH--fX056XMW64P2CA
🔎 ፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School
🔎 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/MesreteHaimanot27

የሊቀ መላዕክት የቅዱስ ገብርኤል፣ የቅድስት እየሉጣ እና የቅዱስ ቂርቆስ  ዓመታዊ ክብረ በዓል በናይሮቢ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም  ቤተክርስቲያን በዚህ መልኩ በድምቀት ተከበረ።ሐምሌ 19/...
26/07/2026

የሊቀ መላዕክት የቅዱስ ገብርኤል፣ የቅድስት እየሉጣ እና የቅዱስ ቂርቆስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በናይሮቢ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በዚህ መልኩ በድምቀት ተከበረ።

ሐምሌ 19/2018 ዓ.ም

√ የዩቲዩብ ገጻችንን
https://youtube.com/?si=gKXqEbltFIjp0p3h

√ ፌስቡክ ገጻች
https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School

√ የቴሌግራም ገጻችንን
https://t.me/MesreteHaimanot27

ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎች ያጋሩ

ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ፡፡በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሮም ግዛት ክርስትና ቢስፋፋም...
26/07/2026

ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ

ሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ፡፡
በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሮም ግዛት ክርስትና ቢስፋፋም በዚያው በጣዖት አምልኮ የተያዙ ብዙዎች ነበሩ፤ ይህም ለዘመኑ ክርስቲያኖች ፈታኝ ነበር፡፡ ይገርማችኋል ልጆች! ማንኛውም ክርስቲያን መሠረታዊ ፍላጎቶቹ እንዲሟሉለት ከፈለገ በጣዖት የሚያመልኩ ሰዎቸ ላቆሟቸው ጣዖቶች መንበርከክ (መስገድ) ግዴታው ነበር፡፡ ሰብአዊ መብቱን ከመገፈፉ ባሻገር ‹‹ተበድያለው›› ብሎ ወደ ፍርድ ቤት ሄዶ መብቱን የማስከበር ፍትሕ የማግኘት ዕድል አልነበረውም፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ በየጊዜው ለክርስቲያኖች ፈታኝ የሆኑ አዋጆች ይወጣሉ፤ የክርስትናን ጎዳና ይበልጥ የሚያጠቡ ሕጎችም ዕለት ዕለት ይደነገጉ (ይወሰኑ) ነበር፡፡ ስለዚህም በወቅቱ የነበረ አንድ ክርስቲያን ሃይማኖቱን ከወደደ ይከሰሳል፤ እስከ መሰደድም ይደርሳል፡፡
በዚህ አስጨናቂ ዘመን እግዚአብሔርን የሚያመልኩ በክርስትና ሃይማኖት የጸኑ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣ የተባሉ ክርስቲያኖች ነበሩ፤ የዚህ ዘመን (የዘመነ ሰማዕታት) መልካም ፍሬዎች ናቸው፡፡ በዚህ በሮም ግዛት እለእስክድሮስ የተባለ ጨካኝ በጣዖት የሚያመልክ ንጉሥ ነበር፤ እናም ክርስቲያኖችን ጣዖት እንዲያመልኩ ያስገድዳቸው ጀመር፤ በዚህም የተነሣ ብዙዎች ጣዖትን ላለማምለክ ሀገር ጥለው ተሰደዱ፡፡ቅድስት ኢየሉጣም ባሏ በሕይወት ባለመኖሩ ከሕፃን ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ጋር ትኖር ነበር፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስም ምንም እንኳን ገና ሦስት ዓመቱ ቢሆንም ነገረ ሃይማኖትንና ፍቅረ ክርስቶስን ታስተምረው ነበር፡፡ እለ ስክድሮስ ለጣዖት እንዲሰግዱ የክሕደት አዋጅን ሲያውጅ ቅድስቲቱ ለሕፃን ልጇ ራርታ ሽሽትን መረጠች፡፡ ሀብት ንብረቷን፣ ወገንና ርስቷንም ትታ ሕፃን ልጇን ተሸክማ ተሰደደች፡፡ መከራው ግን በሄደችበት አልተዋትም፡፡ እለስክንድሮስ ተከትሎ ባለችበት ቦታ አገኛት፡፡ ወታደሮች ልጇን ሳያገኙ እርሷን ብቻ ይዘው ወደ መኮንኑ አቀረቧት መኮንኑ፤ ‹‹ስምሽን ንገሪኝ›› ሲላት ‹‹ስሜ ክርስቲያን ነው›› አለችው፡፡ ‹‹ትክክለኛ ስምሽን ተናገሪ›› ቢላት ‹‹እውነተኛ ስሜ ክርስቲያን ነው፤ የዓለም መጠሪያ ስሜን ከፈለግህ ‹‹ኢየሉጣ ይባላል›› አለችው፡፡ እለእስክድሮስ የተባለ ጨካኝ በጣዖት የሚያመልክ ንጉሥ ‹‹ለጣዖት ልትሰግጂ ይገባል›› ባላት ጊዜ ‹‹እውነትን ይነግረን ዘንድ የሦስት ዓመት ሕፃን ልጄን ፈልገህ አምጣና ተረዳ›› አለችው፡፡ ንጉሡም ወታደሮቹን ፈልገው እንዲያመጡት ላካቸው፤ የሀገሩ ሰዎችም ልጆቻቸውን ስለ ደበቁ የተገኘው ቅዱስ ቂርቆስ ነበር፡፡
ቅዱሱ ሕፃን በወታደሮች ተይዞ ሲቀርብ መልኩ ያበራ ነበርና መኮንኑ ‹‹ደስ የተሰኘህ ሕፃን እንዴት ነህ›› አለው፤ ቂርቆስም መልሶ ‹‹ትክክል ነህ! እኔ በጌታዬ ክርስቶስ ዘንድ ደስታ ይጠብቀኛል፡፡ አንተ ግን ወደ ገሃነም ትወርዳለህ›› በማለት ተናገረ፡፡ በሕፃኑ ድፍረት የደነገጠው መኮንኑ በብስጭት ‹‹እሺ ስምህን ንገረኝ›› ብሎ ጠየቀው፤ ያን ጊዜም ‹‹ከንጹሕ ምንጭ የተቀዳ ስሜ ክርስቲያን ነው፡፡ እናቴ የሰየመችኝ ግን ቂርቆስ ብላ ነው›› ሲል መለሰለት፡፡ ከዚያም እየደጋገመ ‹‹እኔ ክርስቲያን ነኝ›› ብሎ በመመሥከሩ መኮንኑ ቅዱስ ሕፃን ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣን እንዲያሠቃዩአቸው ወታደሮቹን አዘዘ፡፡
ልጆች! ከዚህ በኋላ በእነርሱ ላይ የተፈጸመባቸው ግፍ እና የደረሰባቸው መከራ እጅግ አስከፊና የሚዘገንን ነው:: መኮንኑ በትልቅ በርሜል ውኃ አስፈልቶ ከዚያም ውስጥ ኬሚካል በውስጡ ጨመረ፤ በዚህን ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ የልጇን ነገር አስባ በውስጧ ፍርሃት አደረ፤ ሆኖም ግን በዚህን ጊዜ ሕፃን ቂርቆስ በእምነቱ ጽኑ ስለነበር በመከራው ብዛት አልፈራም፡፡ ይገርማችኋል እንዲያውም የእናቱን ጭንቀትና ለእርሱ ስትፈራ ሲመለከት ‹‹እናቴ ሆይ ከብረቱ ጋን ትልቅነት የተነሣ አትፍሪ! ድንጋጤም አይደርብሽ! አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ከእቶን እሳት ያዳነ እኛንም ያድነናል፤ ሶስናን ከኃጢአተኞች እጅ ያዳናት፣ ዳንኤልን ከአንበሳ ጉድጓድ ያወጣ እኛንም ያድነናል›› አላት፤ ወደ እግዚአብሔርም ጸለየ፤ የዚያን ጊዜ እናቱ ተጽናናች፤ በረታችም፤ ፍርሃት ተወገደላት፤ ስለ እምነታቸው መስክረው ከፈላው የብረት ጋን ውስጥ ጨመሯቸው፤ በዚህን ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና በብረቱ ጋን የፈላውን ውኃ እንደ ውርጭ ውኃ አቀዘቀዘው፤ ኬሚካል ተጨምሮበት ሰውነታቸውን እንዲበጣጥሰው የተዘጋጀውን አቀዝቅዞ ውኃ አደረገው፤ ከመከራም አዳናቸው፡፡ እናቱም ለልጇ ‹‹እኔ የወለድኩህ እናትህ ነኝ፤ አንተ ደግሞ በእምነት ጽናትህ በመንግሥተ ሰማያት አባት ሆንከኝ›› አለችው፤ እግዚአብሔርንም አመሰገኑ፤
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ብዙ ቃል ኪዳን ገባላቸው፤ ‹‹እኔን መከተል የሚወድ ራሱን ይናቅ፤ መስቀሌንም ተሸክሞ ይከተለኝ›› ያለውን አማናዊ ቃል ሰምተው ለሙሽራው ለክርስቶስ ፍቅር ራሳቸውን አሳልፈው ሰጡ፡፡ (ማቴ.፲፮፥፳፬) ስለዚህ እኛም አምላክን ያከበሩ ቅዱሳንን እናከብራቸዋለን፤ ፈለጋቸውን እንከተላለን፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እኔ ክርስቶስን እንደ ምመስል እናንተም እኔን ምሰሉ›› በማለት እንደመከረን ቅዱሳን ሰማዕታትን በእምነት በምግባር ልንመስላቸው ይገባል፤ (፩ኛ ቆሮ. ፲፮፥፩) ከቅዱስ ቂርቆስና ከቅድስት ኢየሉጣ ታሪክ ብዙ ነገር እንማራለን! በሥነ ምግባር የታነጽንና እምነታችን የጸና ልጆች ሆነን ማደግ አለብን፡፡ ቅዱስ ቂርቆስ እናቱ የምታስተምረውን የክርስትና ትምህርት በደንብ ያደምጥ ነበር፤ መከራ በገጠማቸው ጊዜ ከእርሱ ቀድመው እንደነበሩት ቅዱሳን ሰማዕታት በእምነት መጽናት እንዳለበት ተረዳ፤ እናቱንም በእምነትና በጸሎት አጸናት፤ የተማረውን ትምህርት ሳይረሳ በሕይወቱ ተገበረው፤ የሃይማኖት ጽናትን ለእናቱ አስተማረ፤ እኛም እንደ ቅዱስ ቂርቆስ ቅዱሳት መጻሕፍትን በማንበብ ከእኛ በፊት የነበሩ ክርስቲያኖች እንዴት ይኖሩ እንደነበረ ጠይቀን በመረዳት እንደነርሱ ልንሆን ይገባል፡፡
የቅዱስ ቂርቆስና የቅድስት ኢየሉጣ አምላክ በረከቱን ያድለን አሜን።
ምንጭ፡- eotcmk

ቤተሰብ እንሁን ለሌሎችም እናጋራ

🔎ዩቱዩብ ቻናል፦https://youtube.com/channel/UCez7ZZH--fX056XMW64P2CA
🔎 ፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School
🔎 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/MesreteHaimanot27

ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት Nairobi Mesrete Haimont Sunday School:በየዓመቱ ሐምሌ ፭ ቀን በአንድ በኩል የጾመ ሐዋርያት ፋሲካ የሚከበርበት ዕለት ሲኾን፣ በ...
11/07/2026

ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት Nairobi Mesrete Haimont Sunday School:
በየዓመቱ ሐምሌ ፭ ቀን በአንድ በኩል የጾመ ሐዋርያት ፋሲካ የሚከበርበት ዕለት ሲኾን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ በዓለ ዕረፍትም በዚሁ ዕለት ይዘከራል፡፡ በዛሬው ዝግጅታችን የእነዚህን ቅዱሳን ታሪክ በቅደም ተከተል በአጭሩ ይዘንላችሁ ቀርበናል፤
+++++++++++++++++++++++
ቅዱስ ጴጥሮስ
ቅዱስ ጴጥሮስ በአባቱ የሮቤል፣ በእናቱ የስምዖን ነገድ ሲኾን፣ የተወለደውም በገሊላ አውራጃ በቤተ ሳይዳ ነው፡፡ ወላጆቹ ያወጡለት ስም ‹ስምዖን› ነበር፡፡ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹ጴጥሮስ› ብሎ ጠርቶታል፡፡ ትርጕሙም በግሪክ ቋንቋ ዓለት (መሠረት) ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ የሚተዳደረው በዓሣ አጥማጅነት የነበረ ሲኾን፣ ሰዎችን በወንጌል መረብ እያጠመደ ወደ ክርስትና ሕይወት ይመልስ ዘንድ ጌታችን ለሐዋርያነት ጠርቶታል (ሉቃ. ፭፥፲፤ ማር. ፩፥፲፮)፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ በመንፈሳዊ ቅንዓቱና ለጌታችን በነበረው ፍቅር የሐዋርያት አለቃ ኾኖ ተሹሟል፡፡ ለአገልግሎት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮም በእስያ፣ በሮም፣ በሰማርያ፣ በልዳ፣ በኢዮጴ፣ በአንጾኪያ፣ በገላትያና በሌሎችም አገሮች እየተዘዋወረ ወንጌልን ሰብኳል፡፡ በስብከቱ ምክንያትም ልዩ ልዩ መከራን ተቀብሏል፡፡ በክርስቶስ ኀይል አጋዥነት ብዙ ድንቆችንና ተአምራትን አድርጓል፡፡ ከተሰጠው ጸጋ ብዛት የተነሣ በጥላው ሕሙማን ይፈወሱ ነበር (ሐዋ. ፭፥፲፭)፡፡ ሐዋርያው በቃል ካስተማረው ትምህርት በተጨማሪ በመጽሐፍ ቅዱስ በስሙ የተመዘገቡ ሁለት መልእክታትን ጽፏል (፩ኛ እና ፪ኛ ጴጥሮስ)፡፡
የቅዱስ ጴጥሮስ ምድራዊ የአገልግሎት ዘመኑ ሊፈጸም ሲቃረብም እንዲህ ኾነ፤ በዘመኑ የክርስቲያኖች ጠላት የነበረው የሮም ንጉሥ ወደ አካይያ ዘምቶ ድል አድርጎ በደስታ ወደ ሮሜ ሲመለስ መኳንንቱን ለማስደሰት፤ ጣዖታቱንም ለማክበር ሲል በቅዱስ ጴጥሮስና በሌሎችም ክርስቲያኖች ላይ የሞት ፍርድ ዐወጀ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም በሮም ሲያስተምር ቆይቶ የሮም መኳንንት እንዳይገድሉት ትጥቁን ለውጦ ከሮም ሲወጣ ጌታችን መስቀል ተሸክሞ ተገለጸለት፡፡
በዚህ ጊዜ ‹‹አቤቱ ጌታ ሆይ ወዴት ትሔዳለህ?›› ሲል ቢጠይቀው ጌታችንም ‹‹ልሰቀል ወደ ሮም እሔዳለሁ›› አለው፡፡ ‹‹ዳግመኛ ትሰቀላለህን?›› ባለው ጊዜም ‹‹አንተ ስትፈራ ጊዜ ነው እንጂ›› ሲል መለሰለት፡፡ ያን ጊዜም ‹‹ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን ታጥቀህ ወደ ወደድኸው ትሔድ ነበር፡፡ ስትሸመግል ግን እጅህን ታነሣና ሌላ ሰው ያስታጥቅሃል፤ ወደማትወደውም ይወስድሃል፤›› (ዮሐ. ፳፩፥፲፰) በማለት ጌታችን የነገረው ቃል አሟሟቱን የሚያመለክት መኾኑን አስታውሶ ወደ ሮም ተመልሶ ስብከቱን ቀጠለ፡፡
በሮማውያን ሕግ ቅጣት የተፈረደበት ወንጀለኛ የሮም አገር ተወላጅ ከኾነ የወንጀሉ ክብደትና ቅለት እየታየ ግርፋት ወይም ሞት ይፈረድበታል እንጂ በአንድ ወንጀል ሁለት ቅጣት አይቀጣም ነበር፡፡ ወንጀለኛው የውጪ አገር ዜጋ (ከሮም ውጪ) ከኾነ ግን ለምሳሌ ቅጣቱ ግርፋት ከኾነ ከተገረፈ በኋላ እስራት ይጨመርበታል፤ ቅጣቱ ሞት ከኾነም ከገረፉት በኋላ በመስቀል ወይም በሌላ መሣርያ ይገድሉት ነበር፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ዜግነቱ ሮማዊ አልነበረምና በግርፋትም፣ በእስራትም በሞትም እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡
እንደ ሥርዓታቸውም ቅዱስ ጴጥሮስን ከገረፉት በኋላ ሊሰቅሉት ሲሉ ወታደሮቹን ‹‹እንደ ክብር ንጉሥ እንደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አቁማችሁ ሳይኾን፣ ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ›› አላቸው፡፡ እነርሱም እንዳላቸው አድርገው ሐምሌ ፭ ቀን ዘቅዝቀው ሰቅለውታል፡፡ በመስቀል ላይ ሳለም ተከታዮቹን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ ካዘዛቸው በኋላ ነፍሱን ለእግዚአብሔር ሰጠ፡፡ ሥጋውንም መርቄሎስ የሚባለው ደቀ መዝሙሩ ሽቱ ቀብቶ፣ በነጭ ሐር ገንዞ ዛሬ ቫቲካን በምትባለዋ ስፍራ በክብር ቀብሮታል፡፡
ሊቃኦንያ፣ ሦርያ፣ ግሪክና ልስጥራን ካስተማረባቸው አገሮች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ

ቅዱስ ጳውሎስ ለአገልግሎት ከመጠራቱ በፊት ‹ሳውል› ይባል ነበር፡፡ ከኦሪቱ ምሁር ከገማልያል ሕገ ኦሪትንና መጻሕፍተ ነቢያትን ተምሯል፡፡ ለሕገ ኦሪት ቀናኢ ከመኾኑ የተነሣም የክርስቶስ ተከታዮችን ዅሉ ያሳድድ ነበር፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ ተደብድቦ በሰማዕትነት በሞተ ጊዜ ቅዱስ ጳውሎስ የገዳዮቹ ልብስ ጠባቂ ነበር (ሐዋ. ፯፥፶፰፤ ፳፪፥፳)፡፡ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ወደ ደማስቆ ሲሔድ ከመንገድ ላይ ለሐዋርያነት ተጠርቷል (ሐዋ. ፱፥፩-፴፩፤ ፳፪፥፩-፳፩)፡፡
ለሐዋርያነት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮም በመላው ዓለም እየተዘዋወረ ወንጌልን በመስበክ ብዙዎችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሳምኗል፡፡ ሲሰብክም ጣዖት አምላኪ፣ ሕመምተኛ፣ ችግረኛ፣ አረማዊና አይሁዳዊ እየመሰለ ብዙዎችን አስተምሮ ለእግዚአብሔር መንግሥት አዘጋጅቷል (፩ኛ ቆሮ. ፱፥፲፱-፳፫)፡፡ ዐረብ፣ አንጾኪያ፣ እልዋሪቆን፣ ሊቃኦንያ፣ ሦርያ፣ ግሪክና ልስጥራን ካስተማረባቸው አገሮች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
ወንጌልን በመስበኩ ምክንያትም ከአይሁድና ከአረማውያን ዘንድ ብዙ መከራና ስቃይ ደርሶበታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ከእግዚአብሔር በተሰጠው ጸጋ ብዙ ድንቆችንና ተአምራትን አድርጓል፡፡ በልብሱ ቅዳጅም ሕሙማን ይፈወሱ ነበር (ሐዋ. ፲፱፥፲፩)፡፡ ሐዋርያው በቃል ካስተማረው ሌላ በመጽሐፍ ቅዱስ በስሙ የተመዘገቡ ፲፬ መልእክታት አሉት፡፡
አገልግሎቱን ሊፈጽም ሲልም የሮም ንጉሥ ኔሮን ቄሣር የክርስቲያኖች ቍጥር እየጨመረ የመጣው በቅዱስ ጳውሎስ ትምህርት በመማረካቸው ምክንያት መኾኑን ተረድቶ፤ ይልቁንም የቤተ መንግሥቱ ሰዎች ሳይቀር በቅዱስ ጳውሎስ በመማረካቸው ተቈጥቶ ቅዱስ ጳውሎስን ወደ ፍርድ ሸንጎው አስቀረበው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በቀኝ እጁ ከሰንሰለቱ ጋር መስቀሉን ይዞ ንጉሡንና ወታደሮችን ሳይፈራ የኢየሱስ ክርስቶስን የእግዚአብሔር ልጅነትና አምላካዊ ሥልጣን ይመሰክር ነበር፡፡
ንጉሡም በቍጣ ይሙት በቃ ፈረደበት፡፡ ከላይ እንደ ተገለጸው ሮማውያን የሞት ፍርድ ሲፈርዱ የሚቀጣው ሰው የሌላ አገር ዜጋ ከኾነ ከፍርዱ ውጪ ተጨማሪ ቅጣት ይቀጡትና ይገድሉት ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ግን የሮም ዜግነት ስለ ነበረው ሳይገርፉ በአንድ ቅጣት ብቻ በሰይፍ እንዲገደል ወስነውበታል፡፡ ወደሚገደልበት ስፍራ ሲወስዱትም በንግግሩና በአስተያየቱ ዅሉ ምንም ፍርኀት አይታይበትም ነበር፡፡ እንዳውም በጦርነት ድል አድርጎና ማርኮ እንደ ተመለሰ ወታደር ይደሰት ነበር እንጂ፡፡ ለሚገድሉትም ይቅርታን ይለምን ነበር፡፡
በገዳዮቹና በተከታዮቹ ፊትም የክርስትና ሽልማቱ የእግዚአብሔር መንግሥት መኾኑን የሚያስገነዝብ ቃል እያስተማረ እግዚአብሔር የሚሰጠውን የጽድቅ አክሊል ለመቀበል ይቻኮል ነበር (፪ኛ ቆሮ. ፬፥፮-፲፰)፡፡ ወታደሮች ሊገድሉት ሲወስዱትም ከንጉሥ ኔሮን ወገን የኾነችውን የአንዲት ብላቴና መጐናጸፊያ ‹‹ዛሬ እመልስልሻለሁ›› ብሎ ከተቀበላት በኋላ ‹‹መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፤ ሩጫዬን ጨርሻለሁ፡፡ ሃይማኖቴን ጠብቄአለሁ፤ ወደፊትም የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፤›› በማለት ራሱ በመልእክቱ እንደ ተናገረው (፪ኛ ጢሞ. ፬፥፯-፰)፣ ፊቱን በብላቴናዋ መጐናጸፊያ ተሸፍኖ አንገቱን በሰይፍ ተቀልቶ አገልግሎቱን በሰማዕትነት ፈጽሟል፡፡

ደቀ መዛሙርቱም ራሱን ከአንገቱ ጋር ቢያደርጉት እንደ ቀድሞው ደኅና ኾኖላቸው በክብር ገንዘው ቀብረውታል፡፡ ሰያፊው ቅዱስ ጳውሎስን እንደ ገደለው ለመናገር ወደ ንጉሡ ሲመለስም ያቺ መጐናጸፊያዋን የሰጠችው ብላቴና ‹‹ጳውሎስ ወዴት አለ?›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ራሱን ተቈርጦ በመጐናጸፊያሽ ተሸፍኖ ወድቋል›› ሲላት ‹‹ዋሽተሃል፤ እነሆ ጴጥሮስና ጳውሎስ በእኔ በኩል አልፈው ሔዱ፡፡ እነርሱም የመንግሥት ልብስ ለብሰዋል፡፡ በራሳቸውም በዕንቍ ያጌጡ አክሊላትን አድርገዋል፡፡ መጐናጸፊያዬንም ሰጡኝ፡፡ ይህችውም እነኋት፤ ተመልከታት›› ብላ ሰጠቸው፡፡ ከእርሱ ጋር ለነበሩትም አሳየቻቸው፡፡ አይተውም አደነቁ፤ ስለዚህም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ፡፡
ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ በስብከተ ወንጌል አገልግሎታቸው ጨለማውን ዓለም በማድመቃቸው ‹ብርሃናተ ዓለም› ተብለው ይጠራሉ፡፡ የቅዱሳኑ አገልግሎት፣ ገድላቸው እና ተአምራቸው በመጽሐፈ ስንክሳር፣ በዜና ሐዋርያት እና በገድለ ሐዋርያት በሰፊው ተጽፎ ይገኛል፡፡ እኛም በዓለ ዕረፍታቸውን ለማስታወስ ያህል ታሪካቸውን በአጭሩ አቀረብን፡፡
ቅዱሳን ሐዋርያት ያቆዩልንን የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጠብቀን፣ በክርስቲያናዊ ምግባር ጸንተን እንድንኖር፤ በመጨረሻም የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ እንድንበቃ የቅዱሳኑ ጸሎት ይርዳን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

ምንጭ፡-
መጽሐፈ ስንክሳር፣ ሐምሌ ፭ ቀን፤
ዜና ሐዋርያት፤
ገድለ ሐዋርያት፡

በማሕበራዊ ሚዲያዎች ቤተሰብ ይሁኑና ይከታተሉን ለወዳጆም ያጋሩ

🔎ዩቱዩብ ቻናል፦https://youtube.com/channel/UCez7ZZH--fX056XMW64P2CA
🔎 ፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School
🔎 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/MesreteHaimanot27

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: ሰኔ ፴ (30) በዚህች ዕለት በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል (ሉቃ1፥14) ተብሎ የተነገረለት መጥምቀ መለኮተ ቅዱስ ዮሐንስ ተወለ...
07/07/2026

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::

ሰኔ ፴ (30) በዚህች ዕለት በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል (ሉቃ1፥14) ተብሎ የተነገረለት መጥምቀ መለኮተ ቅዱስ ዮሐንስ ተወለደ :: የቅዱስ ዮሐንስ ጸሎቱና በረከቱ ይደርብን አማላጅነቱ ይደረግልን አሜን ::

ቤተሰብ እንሁን ለሌሎችም እናጋራ

🔎ዩቱዩብ ቻናል፦https://youtube.com/channel/UCez7ZZH--fX056XMW64P2CA
🔎 ፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School
🔎 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/MesreteHaimanot27

ሰኔ 21  ሰኔ ጐልጐታ ወሕንፀተ ቤተክርስቲያን እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም ሰኔ ጐልጐታና ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን (ለመጀመሪያ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ለታነ...
28/06/2026

ሰኔ 21 ሰኔ ጐልጐታ ወሕንፀተ ቤተክርስቲያን
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም ሰኔ ጐልጐታና ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን (ለመጀመሪያ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ለታነጸበት) ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ፡፡

‹‹ሰኔ ጐልጐታ ፤
ችግር የምትፈታታ፡፡››

ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም በዚህች ቀን (ሰኔ 21) ልጇን ወዳጇን ጐልጐታ በሚባል ቦታ ላይ እንባዋ እንደ ጅረት እስኪፈስ ድረስ ለኃጥአን ምሕረትን ለምናዋለች:: ጌታችንም ‹‹ስምሽን የጠራውን፤ በቃል ኪዳንሽ ያመነውን ሁሉ እምርልሻለሁ፡፡›› ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ሰኔ ጐልጐታን ተመልከት

✤✤ ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን፤

ሰኔ 21 ከእመቤታችን #33ቱ በዓላት አንዱ ሲኾን፤ ሕንጸተ ቤተክርስቲያን ይባላል፡፡ በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን በአምላክ እናት ስም የታነጸችው በዚሁ እለት በሰኔ 20 ቀን ነው፡፡
አናጺውም ደግሞ እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ቦታው በፊልጵስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው፤ ጥንተ ነገሩስ (ታሪኩ) እንደምን ነው ቢሉ፤
ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን መደኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ‹‹ሑሩ ወመሐሩ ኵሎ አሕዛበ፤ አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ፡፡›› /ማቴ. 28፥19/ ባላቸው ቃል መሠረት ሐዋርያት በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል::

የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና (ዮሐ. 6፥ 56) አበው ሐዋርያት ቊርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን፣ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲህ ይከናወን ነበር፡፡ ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኵራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቊጥር እጅጉን በመብዛቱ /በተለይ ቅዱስ ዻውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ::/ በዚህ ምክንያት መምህራን ሕዝቡን ‹‹ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?›› ቢሏቸው ‹‹እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት ቤት የለን››ሲሉ መለሱላቸው:: ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ዻውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች ቤት ‹‹ለምን አናንጽም?›› ብለው ነበር:: ቅዱስ ዻውሎስ ግን ‹‹ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም›› አለ:: (ለዚህ ነው ዛሬም ሊቀ ዻዻስ ካልፈቀደ ቤተክርስቲያን የማይታነጸው፡፡) ከዚያ ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ዼጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ #ዼጥሮስም ‹‹የጌታችን ፈቃዱመኾኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ›› ብሎ አዋጅ ነገረ::

በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔያቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መላአክትን አስከትሎ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ፤እመቤታችን በቀኙ ነበረች፡፡ ኹሉንም ሐዋርያት በሩቅም በቅርብም ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ በሚባል ሃገር ሰበሰባቸው፡፡ ከዚያም በስተምሥራቅ ከከተማ ወጣ ወዳለ ሥፍራ ወሰዳቸው፡፡

በዚያም ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፡፡ 3ቱንም ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቦ አንሥቶ ጎተታቸው፡፡ ድንጋዮቹም እንደሰም ተለጠጡ፣ እንደ ግድግዳም ሆኑ፡፡ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡
እነርሱም እሳት እንዳየው ሰም በእጃቸው እየለመለሙ (እየሳቡ) ቁመቱን 24፥ ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ዕጽብት፥ ግርምት የምትኾን 3 ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተክርስቲያን በ52 ዓ/ም ሰኔ 20 ቀን አነጹ፡፡
ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ፤ ጌታችንም በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድርጎ አነጻት፤ ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ለሐዋርያቱ ‹‹እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ፡፡›› ብሏቸው ዐረገ፡፡

✜ በማግስቱ ሰኔ 21 ዕለት ደግሞ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን፣ ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዞ ወረደ:: ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት 2 ነገሮችን አሳየ፤ አስቀድሞ ቤተክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዐተ ቤተክርስቲያንን አሳየ:: ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን ከመካከል አቁሞ ‹‹አርሳይሮስ›› ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ‹ ‹‹አክስዮስ››(አክዮስ)እያሉ 3 ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: አክዮስ ማለት በግዕዙ ‹‹ይደልዎ›› በአማርኛው ደግሞ ‹‹ይገባዋል፤ ያስምርለት›› እንደ ማለት ነው::

ጌታችን ይህን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ:: አማናዊት ማኅደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ኾኖ፣ ሐዋርያት ድንግልን ከበው፣ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቆመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ::
በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው:: ‹‹ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን አንጹ፤ ይህችን እለት የሚያከብራትን አከብረዋለሁ::›› ብሏቸው ከድንግል እናቱና ከመላእክቱ ጋር ዐረገ::

ቤተሰብ እንሁን ለሌሎችም እናጋራ

🔎ዩቱዩብ ቻናል፦https://youtube.com/channel/UCez7ZZH--fX056XMW64P2CA
🔎 ፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/Nairobi-Meserete-Haimanot-Sunday-School
🔎 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/MesreteHaimanot27

Address

Nairobi

Telephone

+254740111336

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት / Nairobi Meserete Haimanot Sunday School posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share