የኢየሩሳሌም ገዳማት ስብከተ ወንጌል

የኢየሩሳሌም ገዳማት ስብከተ ወንጌል Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የኢየሩሳሌም ገዳማት ስብከተ ወንጌል, Church, ethiopian Street 10, Jerusalem.

✅መፅሀፉ ስንክሳር የመጋቢት ፳ ቀን !!!🚩መጋቢት 20በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን አሜን አሜን አሜን!!!✅ሐዋርያ ቅዱስ አልዓዛር፦✏ከቀናት በፊት ጻድቅና ሐዋርያ ቅ...
29/03/2022

✅መፅሀፉ ስንክሳር የመጋቢት ፳ ቀን !!!

🚩መጋቢት 20
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን አሜን አሜን አሜን!!!
✅ሐዋርያ ቅዱስ አልዓዛር፦

✏ከቀናት በፊት ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ አልዓዛር አረፈ ብለን ነበር:: ለስም አጠራሩ ስግደት: ክብር: ጌትነት ይድረሰውና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልዓዛር ባረፈ በአራተኛው ቀን ወደ ቢታንያ ደረሰ::

✏ማርታ ቀድማ ወጥታ ከእንባ ጋር ተቀበለችው::
"አዳም ወዴት ነህ" ያለ (ዘፍ. 3:10) የአዳም ፈጣሪ "አልዓዛርን ወዴት ቀበራችሁት" አለ:: ቸርነቱ: ባሕርዩ ያራራዋልና ማርያም ስታለቅስ ባያት ጊዜ አብሮ አለቀሰ::

✏ከዚያም በባሕርይ ስልጣኑ "አልዓዛር! አልዓዛር!" ብሎ አልዓዛርን አስነሳው:: ይሕች ተአምርም በአይሁድ ዘንድ ግርምት ሆነች:: ለጌታም የሞት ምክንያት አደረጉዋት:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርጋ እንዲህ ታስተምራለች::
(ዮሐ. 11:1-ፍጻሜው)

✏ቅዱስ አልዓዛር ጌታችን ካስነሳው በሁዋላ በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ (ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ነውና) : ለ40 ዓመታት ወንጌልን አስተምሮ : በ74 ዓ/ም አካባቢ ቆዽሮስ ውስጥ አርፏል::

🚩የጌታችን ቸርነቱ : የአልዓዛር በረከቱ ይድረሰን::

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ቅዱስ አልዓዛር ጻድቅ ሐዋርያ (የጌታ ወዳጅ)
2.ቅድስትና ብጽዕት ሰማዕት አስጠራጦኒቃ (ከታላላቅ ሰማዕታት አንዱዋ)
3.ቅዱሳን ሰማዕታት (የቅ/አስጠራጦኒቃ ማሕበር)
4.እናታችን ቅድስት ጽጌ-ሥላሴ (ኢትዮዽያዊት)
5.ቅዱስ አስቃራን ሰማዕት
6.አባ ሚካኤል ሊቀ ዻዻሳት

🚩ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት (ሰማዕት)
2.ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
3.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
4.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
5.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
6.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።

አሜን አሜን አሜን!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፱ ቀን!!!🚩መጋቢት 19በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን አሜን አሜን!!!!✅ሀዋርያ አርስጦቦሎስ፦✏በዚች እለት የሀዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ...
28/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፱ ቀን!!!

🚩መጋቢት 19
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን አሜን አሜን!!!!
✅ሀዋርያ አርስጦቦሎስ፦

✏በዚች እለት የሀዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙር አርስጥቦሎስ ሀዋርያ አረፈ። እርሱም ጌታችን ከመረጣቸውና ከመከራው በፊት እንዲሰብኩ ከላካቸው ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ የተቆጠረ ነው።

✏በሀምሳኛው ቀን በአልም መንፈስ ቅዱስ በላዮ በወረደ ጊዜ ከሀዋርያት ጋር ፀጋንና ሀይልን ተመልቶ ህይወት በሚገኝበት በወንጌል ትምህርት ሀዋርያትን ተከትሎ በመሄድ አገለገላቸው።

✏ብዙዎችንም ወደ ድኀነት መንገድ መልሶ የክብር ባለቤት ወደ ሆነ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሀይማኖት አስገባቸው የክርስትና ጥምቀትንም አጥምቆ የአምላክን ህግና ትእዛዝ ከማስጠበቁ የተነሳ ነፍሳቸውን አዳነ።
አባቶቻችን ሀዋርያትም ይህን ቅዱስ አብራጣብያስ በሚባል አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት።

✏ወደርሷም ሂዶ በውስጥዋ ወንጌልን ሰበከ ብዙዎቹንም በቀናች ሀይማኖት እግዚአብሄርን ወደ ማወቅ መለሳቸው። በፊታቸውም ድንቆች ተአምራትን በማድረግ በሀይማኖት አፀናቸው ነገር ግን ከአይሁድና
ከዮናናውያን ብዙ መከራ ደረሰበት።

✏ብዙ ጊዜም ወደ ፈረጆች አደባባይ ወስደው በደንጊያ ወገሩት ጌታችንም ከመከራው ሁሉ ጠብቆ አዳ ነው መልካም ተጋድሎውንም በፈፀመ ጊዜ በሰላም በፍቅር አረፈ። እነሆ ለሮሜ ሰዎች በፃፈው መልእክቱ ሀዋርያ ጳውሎስ አስታውሶታል።በፀሎቱ የምተገኝ በረከቱ ከእኛ
ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።

✅ሰባቱ ቅዱሳን ሰማዕታት፦

✏በዚህችም ቀን ደግሞ የሰባቱ ሰማእታት መታሰቢያቸው ሆነ እንርሱም የግብፅ ሰው እለእስክንድሮስና እስክንድሮስ ከጋዛ መንደር አጋብዮስ ከቡንጥስ ከተማ ኒሞላስ ከጠራልብስ ዲዮናስዮስ ሮሜሎስና ተላስዮስ ከግብፅ አውራጃዎች የሆኑ ናቸው።

✏እነርሱም በመንፈሳዊ ፍቅር ፀንተው ስለ ሀይማኖት ምስክሮች ሊሆኑ ተስማሙ ።በፍልስጥኤም ውስጥ ወደ አለው ቄሳርያ ደር ሰው በመኰንኑ ፍት ቆሙ። በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማመናቸውን ገለጡ መኰንኑም በፅኑእ ስቃይ አሰቃይቶ ገደላቸው። የሰማእትነትንም አክሊል በመንግስተ ሰማያት ተቀበሉ። በረከታቸው ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።

✅ቅዱስ አስከናፍር፦

✏በዚችም ቀን ደግሞ ቅዱስ አስከናፍርና የሚስቱ ማርታ የልጆቹ አርቃድዮስና ዮሀንስ የእረፍታቸው መታሰቢያ ሆነ።ይህም አስከናፍር ብዙ ገንዘብ ያለው ባለጠጋ ነው ለእግዚአብሔርም ህግ የሚጠነቀቅ ነበር ልጆቹንም መንፈሳዊ ምክርና ተግሳፅ በማስተማር አሳደጋቸው።

✏በአደጉም ጊዜ የጥበብንና የተግሳፅን ትምህርት እንዲማሩ ተይሩት ወደምትባል አገር ሰደዳቸውና ትምህርታቸውን በፈፀሙ ጊዜ ሊድራቸውና በሰርጋቸው ደስ ሊለው ሽቶ ያመጡአቸው ዘንድ ላከ በመርከብም ሆነው ሲመጡ ማእበል ተነስቶ መርከቡ ተሰበረ።እግዚአብሔርም ከስጥመት አድኖ በየብስ አወጣቸው ዮሀንስ የተባለውን በአንድ ቦታ
ማእበሉ አውጥቶ ጣለው።

✏ዮሐንስም ተስፋ በቆረጠ ጊዜ ወደ ቅዱሳን ገዳም ሂዶ መነኰሰ።ስለ ወንድሙ ስለአርቃድዪስም እንደሞተ ተጠራጥሮ በፆም በፀሎትና በስግደትም ስጋውን አደከመ።አርቃድዮስም ወደ ዮርዳኖስ ገዳም ገብቶ ከአንድ ቅዱስ አረጋዊ ሰው ዘንድ መንኲሶ እየተጋደለ ሶስት ዓመት ኖረ።

✏አስከናፍር ግን ልጆቹ በማዕበል እንደሰጠሙ በሰማ ጊዜ ከሚስቱ ጋራ ማቅለብሰው አመድ አንጥፈው እያለቀሱ ተቀመጡ ።በአንዲት ሌሊትም አስከናፍር በህልሙ ልጁ ዮሐንስን በራሱ ላይ ከዕንቊ የተሰራ አክሊል ተቀዳጅቶ መስቀል ይዞ አየው።

✏አርቃድዮስንም በኮከብ አምሳል የሆነ አክሊል በራሱ ላይ ደፍቶ አየ ከእንቅልፉም ነቅቶ ለሚስቱ ያየውን ነገራት።ከዚያም በኃላ በየአድባራቱና በየገዳማቱ የልጆቻችንን ወሬ እንመረምር ዘንድ ተነሺ እንሂድ አላትና ወደ ዮርዳኖስ ሂደው ከመጥምቁ ዮሐንስ ገዳም ደረሱ።

✏ልጃቸውን አርቃዴዎስን ያመነኰሰውን አረጋዊ አባትን አገኙት ችግራቸውን ነገሩት እርሱም የክርስቶስ ወዳጆች አትዘኑ ወደ ቤተ መቅደስ ስትመለሱ ልጆቻችሁን በህይወት ታገኛላችሁ አላቸው ደስ እያላቸውም ተመለሱ።

✏ዮሐንስም በመስቀል በዓል ሊሳለም መጣ አረጋዊውም ጠርቶ ከአርቃድዮስ ከወንድሙ አገናኘው ተያይዘውም አለቀሱ።ደግሞ አስከናፍርን ከሚስቱ ጋራ ጠርቶ ከልጆቻቸው ጋር
አገናኛቸውና በላያቸው ወድቀው እየሳሟቸው አለቀሱ።

✏ከዚህ በኃላ ከዚያ አረጋዊ ዘንድ የምንኲስና ልብስ ለበሱ ሚስቱን ማርታንም ከሴቶች ገዳም አስገባት አገልጋዮችንም ነፃ አውጥቶ አሰናበተ።ገንዘቡንም ለድኆችና ለችግረኞች በተነ
ከገዳምም ገብቶ በፆም በፀሎት ተወሰነ እንዲሁም የተባረኩ ልጆቹ በገደል በትሩፋት የተጠመዱ ሆነው ኖሩ ጌታችንንም ደስ አሰኙት በፍቅር አንድነትም አረፉ።

🚩በረከታቸው ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ቅዱስ አስከናፍር: ሚስቱ ማርታ: ልጆቹ አርቃድዮስና ዮሐንስ
2.ቅዱስ አርስጥቦሎስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት-የቅ/ዻውሎስ ደቀ መዝሙር)
3.ሰባቱ ቅዱሳን ሰማዕታት (ከተለያየ ቦታ ተሰብስበው በክርስቶስ ስም የሞቱ)

🚩ወርሐዊ በዓላት፦
1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት
3.አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ
4.አቡነ ስነ ኢየሱስ
5.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፰ ቀን !!!🚩መጋቢት 18በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!✅ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት፦✏በዚች ቀን የሰማእት ቅዱስ ፃና ጓደኛው የከበረ ...
27/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፰ ቀን !!!

🚩መጋቢት 18
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!
✅ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት፦

✏በዚች ቀን የሰማእት ቅዱስ ፃና ጓደኛው የከበረ ኤስድሮስ በሰማእትነት አረፈ።ፃና ግን ፈርማ በሚባል አገር ለአገረ ገዢው ከጦር ሰራዊቱ ውስጥ ወታደር ነበር እርሱም ከደቅስያ ሰዎች ወገን ነው ከበግ ፀጉር ልብሶችን ለሚሰራ ለኤስድሮስ ወዳጅ ነው።

✏ሁለቱም ሰርተው ከሚያገኙት ለድኆችና ለችግረኞች ይመፀውታሉ።በአንዱት ሌሊትም ከእርሷ ጋር አክሊሎች ያሉ ድንግል ሴት በራሳቸው ላይ ስታኖረው ሁለቱም ራእይን አዩ።ከእንቅልፋቸውም በነቁ ጊዜ ያዩትን እንዴት እንዳዩ ተነጋገሩ ።

✏ምስክሮቹ ሊሆኑ የጠራቸው እግዚአብሔር እንደሆነ አውቀው እጅግ ደስ አላቸው። ከዚያም ተነስተው ሄደው ወደ መኰንኑ ደረሱ ቅዱስ ፃናም ትጥቁን ፈትቶ በመኰንኑ ፊት ጣለው ሁለቱም በጌታችን በክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ማመናቸውን ገለጡ።

✏መኰንኑም ነገራቸውን ሰምቶ አስረው ይደበድቧቸው ዘንድ አዘዘ እግዚአብሄርም መልአኩን ልኮ አዳናቸው። ከዚህም በኃላ መኰንኑ ወደእስክንድርያ ቅዱስ ፃናን ላከው ቅዱስ ኤስድሮስን ግን በዚያው
ተወው ከጥቂት ቀኖችም በኃላ የእስክንድርያው መኰንን ቅዱስ ፃናን ወደ ፊርማ ከተማ መለሰው።ሁለቱ ቅዱሳንም ተገናኙ በመገናኘታቸውም ደስ ብሊአቸው በላያቸው በየአንዳንዳቸው የደረሰውን መከራ ተነጋገሩ።

✏ዳግመኛን በቅዱስ ኤስድሮስ ዐዘቅትን ይቆፍሩለት ዘንድ በዐዘቅቱም ውስጥ እሳትን አንድደው ቅዱስ ኤስድሮስን እንዲጨምሩት መኰንኑ አዘዘ።ቅዱሱም ጥቂት እስቲፀልይ ይታገሱት ዘንድ ወታደሮቹን ለመናቸው ወደ ጌታችንም ነፍሱን ይቀበል ዘንድ ለስጋውም ያስብ ዘንድ
ፀለየ።

✏ከዚያም ወደ እሳቱ ጉድጓድ ቀረበ ወደ እሳቱም ውስጥ ጨመሩት ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ በስጋውም ላይ ምንም ጉዳት አልደረሰም መልኩም አልተለወጠም ።የቅዱስ ፃና እናትም ከሚወደው ጓደኛው ስለመለየቱ ታለቅስለት ነበር በዚያም ስጋውን ተሸክመው ወሰዱ
የስደቱም ወራት እስቲፈፀም በመልካም ቦታ አኖሩት።

✏ቅዱስ ኤስድሮስም ምስክር ሆኖ በሞተ ጊዜ የቅዱስ ፃና እናት ብዙ መላእክት የቅዱስ ኤስድሮስን ነፍስ ይዘው በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ሲያሳርጓት አየች።እግዚአብሄርም ሁላችንን የክርስቲያን ወገኖችን በፀሎቱ ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት

🚩ወርሐዊ በዓላት፦
1.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ
2.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ሰባኬ ሃይማኖት (ረባን)
3.አቡነ አኖሬዎስ ዘደብረ ጽጋጋ
4.ማር ያዕቆብ ግብፃዊ

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።

አሜን አሜን አሜን!!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፯ ቀን !!!!🚩መጋቢት 17በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!!✅አልዓዛር ሐዋርያ፦✏ በዚች ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚወደው በአ...
26/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፯ ቀን !!!!

🚩መጋቢት 17
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!!
✅አልዓዛር ሐዋርያ፦

✏ በዚች ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚወደው በአራተኛውም ቀን ከመቃብር ያስነሣው የከበረ ጻድቅ አልዓዛር አረፈ።ይህም ጻድቅ ሰው ከእስራኤል ልጆች ውስጥ ነው ማርያና ማርታ ኢየሱስ ሁለት እኅቶች አሉት። ማርያም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሸቱ የቀባችው ናት። እነርሱም ለጌታ ደቀመዛሙርቶቹ ናቸው ስለ ምግባራቸውም ጌታችን ይወዳቸዋል ሁሉም ያላገቡ ድናግል ናቸው።

✏በሰው ወገን ሁሉ ላይ የተቆረጠና የተወሰነው ሰዎችም ሊጠጡት ያላቸው የሞት ጽዋን የሚጠጣበትና እጁን ለሞት የሚሰጥበት ለዚህ ጻድቅ ጊዜው ሲደርስ እርሱም እጁን በመስጠት አረፈ።

✏የክብር ባለቤት ጌታችን ግን የሚሠራውን ያውቃልና መጀመርያ ከሞት አላዳነውም አራት እስከሚአሥነሣው ድረስ ሙቶ በመቃብር አራት ቀን እንዲኖር በዚህ በአራት ቀንም የጻድቃንን ማደሪያዎችንና የኃጥአንን የሥቃይ ቦታዎች እንዲያይ ተወው እንጂ አላዳነውም ያን ጊዜም
ታላቅ ምልክት ትሆናለች።

✏ከአራት ቀኖችም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ አልዓዛር አልዓዛር ና ውጣ ብሎ ከመቃብር ውስጥ ጠራው ያን ጊዜ አጆቹና እግሮቹ እንደታሠሩ ሙታኖችንም እንደሚጠቀልሏቸው በሰበን ፊቱ ተጠቅልሎ ወጣ።

✏እጆቹና እግሮቹ እንደ ተጠቀለሉና እንደ ታሠሩ ከመቃብር የመውጣቱ ምክንያት ሰዎች ሁሉ መሞቱን እንዲረዱ ሌሎችም ይህ በመካከላቸው በስምምነት የሆነ ነው ብለው እንዳያሰቡ። ስለዚህም እንደ ገነዙት ሁኖ እንዲወጣ ጌታችን አዘዘው ይችም ምልክት እንድትሆን።

✏ከሀዲዎችም በመቃብር ውስጥ ሕያው እንደ ነበር ቢያስቡም እጆቹና እግሮቹ ፊቱም እንደ ተጠቀለሉ እንዴት ይወጣ ነበር እኛ የክርስቲያን ወገኖች ግን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአራት ቀኖች በኋላ አልዓዛርን ያስነሣው እርሱ እንደሆነ እናምናለን ።እንታመናለንም እርሱ በሥራው ሁሉ ላይ ችሎታ አለውና።

✏ለጌታችን ለፈጣሪያችን ለመድኃኒታችንም ኢየሱስ ክርስቶስ ከቸር አባቱና ሕይወት ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ክብር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።

✅ቅዱስ ቴዎቅሪጦስ አናጉንስጢስ፦

✏በዚችም ዕለት አናጕንስጢስ ቴዎቅሪጦስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ የሮሜ አገር ሰው ነው። ዐላውያንም ለጣዖት እንዲሠዉ ክርስቲያኖችን ይዘው በአስገደዷቸው ጊዜ እርሱንም ከእነርሱ ጋር ያዙት ወደ ንጉሥም አቀረቡት ያንጊዜ የዐሥራ አምስት ዓመት ልጅ ነበር።

✏ንጉሡም በማመጣብህ ሥቃይ ትፈተናለህን ወይስ ለአማልክት ትሠዋለህ አለው። ቴዎቅሪጦስም እኔስ ለክብር ባለቤት ለጌታዬ ለፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እሠዋለሁ አለው። ንጉሡም ቴዎቅሪጦስ ሆይ በክፉ አሟሟት እንዳትሞት ለአማልክት መሥዋዕት አቅርብ አለው ።

✏እርሱም ንጉሥ ሆይ መሥዋዕቴን እንድታይ ና አለው ንጉሡም ወደ ጣዒቱ ቤት እንዲወስዱትና በዚያ እንዲሠዋ አዘዘና እርሱም በበር ቆመ። ቅዱሱም በጸለየ ጊዜ ንውጸውጽታ ሁኖ አጽቀላጽዮስ የሚሉት አምላካቸው ወድቆ ተሰበረ ።

✏ንጉሡም እንደ ዘበተበት አይቶ አፍንጫውን ቆረጠው አሥረው በወህኒ ቤት እንዲአስገቡት አዘዘ። በማግሥቱም አውጥተው በብረት ምጣዶች ውስጥ ጨመሩት ደግመው ጥልቅ ግድጓድ ቆፈሩ በውስጡም እንጨት ረብርበው ሥጋው ከመለያያው እስቲቦጫጨቅና ቅልጥሙም ከአጥንቶቹ እስቲፈስ ድረስ ወረወሩት ። በዚህም ሊአጠቁት አለቻሉም የመንፈስ
ቅዱስ ኃይል ከእርሱ ጋር አለና።

✏ከዚህ በቤት አማልክቶቻቸው የሚበቀሉት መስሏቸው ከአማልክቶቻቸው ቤት አስገብተው በዚያ ዘጉበት ። ቴዎቅሪጦስ ግን ከጣዖታቱ ላይ ያለውን ወርቅ ቀጥቅጦ በሥውር ይዞ እየወጣ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች መጸወተው። ተመልሶ ሲገባም ደጃፉ እንደ ቀድሞው ራሱ ይዘጋል።

✏በስምንተኛውም ቀን ንጉሡ መጣ ከደጃፍም ሁኖ አየ አማልክቶቹም ተጥለው ተሰባብረው የከበረ ቴዎቅሪጦስም ሲዘብትባቸው አገኛቸው። ዕውነተኛ ቴዎቅሪጦስንም የሆድ ዕቃው እስቲታይ እንዲሰነጣጥቁት አዘዘ። ደግመው ወደ ጨዋታ ቦታ እንዲአስገቡትና በላዩ አንበሶችን እንዲአስገቡአቸው አዘዘ። አንበሶችም ቁስሎቹን ላሱለት።

✏ዳግመኛም ሕዋሳቱ እስቲነጣጠል ከሚአጣብቅ ቦታ እንዲአስገቡት መላ አካላቱም ታጥፎ እስቲቆለመም እንዲአሠቃዩት አዘዘ። በዚህም ተሸብሮ አላሸነፉትም ንጉሡም ብርታቱን አይቶ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ።

✏የከበረ ኤጲስቆጶስ ኤሞሬዎስና ህዝብ ሁሉ በጸሎት እየተራዱት ቅዱስ ቴዎቅሪጦስን ተከተሉት በቅዱሳን ሰላምታም ተሳልመውት ተሰናበቱት ባለወግ ወታደርም ሰይፉን አንስቶ አንገቱን ቆረጠው ምስክርነቱንም ፈጸመ አማላጅነቱ በረከቱም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ቅዱስ አልዓዛር ጻድቅ ሐዋርያ
2.ቅዱስ ቴዎቅሪጦስ አናጉንስጢስ (ሰማዕት)
3.ቅዱስ ተላስስ ሰማዕት
4.ቅዱስ ዮሴፍ ኤዺስ ቆዾስ
5.ቅዱስ ጊዮርጊስ መስተጋድል

🚩ወርኀዊ በዓላት፦
1.ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት (ቀዳሜ ሰማዕት)
2.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ ዘብዴዎስ)
3.ቅዱስ ኤዺፋንዮስ ዘቆዽሮስ
4.ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ
5.አባ ገሪማ ዘመደራ
6.አባ ዸላሞን ፈላሢ
7.አባ ለትጹን የዋህ

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፮ ቀን!!!🚩መጋቢት 16በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን አሜን!!!!!✅"አባ ሚካኤል ሊቀ ዻዻሳት"፦✏ በዚች ቀን በእስክንድርያ ከተሾሙ አ...
25/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፮ ቀን!!!

🚩መጋቢት 16
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን አሜን!!!!!
✅"አባ ሚካኤል ሊቀ ዻዻሳት"፦

✏ በዚች ቀን በእስክንድርያ ከተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ሰባተኛ የሆነ የእስክብድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አባ ሚካኤል አረፈ።

✏ይህም አባት በአስቄጥስ በአባ መቃርስ ገዳም መንኲሶ በገደል
ተጸምዶ ኖረ ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎድሮስ
በአረፈ ጊዜ በላዩ የትንቢት መንፈስ ያደረበት አንድ ጻድቅ ሰው
እስከ ሚአስረዳቸው ድረስ ኤጲስቆጶሳት ስብሰባ አድርገው ለዚች
ሹመት ስለሚሻል ሲመክሩና ሲመረምሩ ብዙ ቀኖች ኖሩ።

✏ከዚህም በኋላ ያ ሰው እኔ በአባ መቃርስ ገዳም በነበርኩ ጊዜ
ስጸልይ የሊቀ ጵጵስና ሹመት ለሚካኤል ይገባዋል ለዚች ሹመት
የሚሻል እሱ ነውና የሚል ቃልን ከሰማይ ሰማሁ አላቸው ።
ሁሉም ስለ ትሩፋቱ ተናገሩ ስለ እርሱም ተስማምተው ከገዳሙ
ወደ እስክንድርያ ሊያመጡት ከመስር ገዥ ዘንድ ደብዳቤ
አጽፈው ያዙ።

✏ሊያመጡትም ሲሔዱ ስለ ገዳሙ አገልግሎት ከሽማግሎች
መነኰሳት ራር ወደ ጋዛ ከተማ ሲመጣ በመንገድ አገኙት
ይዘውም አሠሩት። ወስደውም በመስከረም ወር በዐሥራ ሰባት
ሊቀ ጵጵስና ሾሙት ያቺም ዕለት በጌታ ደም የከበረ መስቀል
በዓሉ የሚከበርባት ናት።

✏ይህም የሆነው ከዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በኋላ የሐሚድ ልጅ
እልሲድ በሚገዛበት ዘመን ነው። በሹመቱ ወራትም መርዋን
አልጋዲን ነገሠ። የእስክንድርያም አገር ሰዎች ከጥቂት ካፊያ
በቀር ብዙ ዝናብ ሳይዘንብላቸው ብዙ ዓመታት ኖሩ። በዚያች
እርሱ በተሾ መባት ቀን በሁለተኛውም በሦስተኛውም ብዙ ዝናብ
ዘንቦላቸው እጅግ ደስ አላቸው።

✏በዚህም አባት ዘመን በክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራ
ደረሰ ከምእመናንም ብዙዎች ሸሹ የክብር ባለቤት ክርስቶስንም
የካዱት ሰዎች ቁጥራቸው ሃያ አራት ሺህ ሆነ። ለዚህ ነገር
ምክንያት የሆነውን ከእርሱ እግዚአብሔር እስከአጠፋው ድረስ
ይህ አባት ስለዚህ በታላቅ ኀዘን ውስጥ ነበር።

✏ዳግመኛም በዚህ አባት ዘመን ለመለካውያን ቆዝሞስ ሊቀ
ጵጵስና ተሹሞ ሳለ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ክርስቶስ
ተዋሕዶ ከዚህ አባት ከአባ ሚካኤል ጋራ ተከራክሮ ይህ አባት
አባ ሚካኤል እንዳስረዳው አመነ።

✏እንዲህም ብሎ በእጁ ጻፈ የክብር ባለቤት ክርስቶስ ከተዋሕዶ
በኋላ ሊቀ ጳጳሳት ቄርሎስ እንደተናገረ የመለኮቱና የትስብእቱ
አንድ ባሕርይ በመሆን ጸንቶ ይኖራል ሲል ኤጲስቆጶሳቱም
እንዲሁ ከተዋሕዶ በኋላ ስለ ክርስቶስ የተለያዩ ሁለት ባሕርያት
ሁለት ገጻት አሉት ይሉ ዘንድ የሚገባ አይደለም ሲሉ ጻፉ።

✏ሐዋርያትም በሰበሰቧት በከበረች በአንዲት ቤተ ክርስቲያን
ውስጥ በአንድነት ጸንተው ሊኖሩ ተስማሙ። ከዚህም በኋላ
ከእስክንድርያ ሰዎች መለካዊ የሆነ ስሙ አንስጣስዮስ የሚባል
ሰው በላያችው ጥፋትን አመጣ እርሱ ኤጲስቆጶስነት
እንዲሾሙት ሽቶ አልሾሙትምና ስለዚህ ወደ እስላሞች ንጉሥ
ሒዶ በአባ ሚካኤል ነገር ሠራበት ከዐመፀኞች ነገሥታትም ብዙ
መከራ ደረሰበት።

✏ጽኑዕ የሆነ ሥቃይም አሠቃዩት ብዙ ግርፋትም ገረፈው ለረጂም
ጊዜ በእግር ብረት አሠሩት። አንገቱንም በሰይፍ ሊቆርጡ ወደ
መኰንኑ አቅርበውት ነበር ስለ መንጋዎቹም ጥበቃ እግዚአብሔር
አዳነው።

✏ዳግመኛም በመርዋን አልጋዲ ዘመነ መንግሥት የሙሴ ልጅ
በሆነ በንጉሥ አገልጋይ አደባባይ በታላቅ ሥቃይ አሠቃዩት።
መኰንኑም ገንዘብ እንዲሰጠው ሽቶ ሊቀ ጳጳሳቱን አባ
ሚካኤልን አሠረው ሰዎችም መጥተው ዋስ ሁነው አወጡት።
ምጽዋትም ጠይቆ ለመኰንኑ ብዙ ገንዘብ አምጥቶ እንዲሰጠው
ወደ ላይኛው ግብጽ ወሰዱት።

✏ይህ አባትም ወደ ላይኛው ግብጽ በሔደ ጊዜ በዚያ ብዙ
ተአምራትን አድርጎ የክብር ባለቤት ክርስቶስን የካዱትን
ምእመናን ብዙዎቹን ወደቀናች ሃይማኖት መልሶ አስገባቸው።
የኢትዮጵያ ንጉሥም ይህን አባት የእስላሞች መኳንንት
እንዳሠቃዩት በሰማ ጊዜ ፍጹም ኀዘንንም አዘነ።

✏መንፈሳዊ ቅናትንም ቀንቶ ወደ ግብጽ አገር ዘምቶ ከላይኛው ግብጽ ደረሰ። ከርሱ ጋርም መቶ ሺህ ፈረሰኞች አርበኞች መቶ ሺህ በበቅሎ
የተቀመጡ አሁንም በግመል የተቀመጡ መቶ ሺህ አርበኞች
ወታደሮች ነበሩ ብዙ አገሮችንም አጠፉ ብዙዎችንም
ማረካቸው።

✏የግብጽ ንጉሥም ይህ ሁሉ የሆነው ስለ ሊቀ ጳጳሳቱ ስለ አባ
ሚካኤል እንደሆነ ዐውቆ ከእሥራቱ ፈጥኖ ፈታው ታላቅ
ክብርንም አከበረው እንዲሁም የክርስቲያንን ወገኖች ሁሉ እጅግ
አከበራቸው።

✏ከዚህም በኋላ ለኢትዮጵያ ንጉሥ ደብዳቤ ጽፎ ይልክ ዘንድ ወደ
አገሩም እንዲመለስ ያዝዘው ዘንድ የግብጽ ንጉሥ ይህን አባት
አባ ሚካኤልን ለመነው ።ይህም አባት ወደ ኢትዮጵያ ንጉሥ እርሱንና መኳንንቱን መሳፍንቱንና ሠራዊቱን እየባረከና እየመረቀ ደብዳቤ ጽፎ ላከ

✏እንዲህም አለው እነሆ በአንተ ምክንያት ከእሥራትና ከዽቃይ
ሁሉ እግዚአብሔር አድኖናልና አሁን ወደ አገርህ በሰላም
በፍቅር ተመለስ ስለ እኔና ስለ ክርስቲያን ወገኖች ሁሉ ስለ
ደከምክ መልካም ዋጋህን እግዚአብሔር በመንግሥተ ሰማያት
ይስጥህ።

✏የኢትዮጵያ ንጉሥም የዚህን አባት የሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤልን
ደብዳቤ በአነበበ ጊዜ ፈጥኖ ተነሥቶ ወደ አገሩ በሰላም በፍቅር
አንድነት ተመለሰ። አባ ቆዝሞስና ወገኖቹም ከሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል ጋራ በተስማሙ ጊዜ አባ ቆዝሞስ በውዴታው ለምስር ኤጲስቆጶስ
ሁኖ ተሹሞ ከዚህ አባት ከአባ ሚካኤል ስልጣን በታች ሆነ።
ይህም አባት መልካም ተጋድሎውን በፈጸመ ጊዜ ወደ ወደደው
እግዚአብሔር ሔደ አማልጅነቱ በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ
ይሁን አሜን።

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦

1.ቅዱስ አባ ሚካኤል ሊቀ ዻዻሳት

🚩ወርኀዊ በዓላት፦
1.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም)
2.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት)
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ (የቅ/ላሊበላ
ወንድም)
4.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ
5.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
6.አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
7.አባ ዳንኤል ጻድቅ

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፭ ቀን!!!!🚩መጋቢት 15በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!!✅ቅድስት ሣራ ጻድቅት (ግብፃዊት)፦ ✏በዚች ቀን የከበረች ተጋዳይ መነኰሳ...
24/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፭ ቀን!!!!

🚩መጋቢት 15
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!!
✅ቅድስት ሣራ ጻድቅት (ግብፃዊት)፦

✏በዚች ቀን የከበረች ተጋዳይ መነኰሳዪት ሣራ አረፈች።
ይቺም ቅድስት ከላይኛው ግብጽ ናት ወላጆቿም የክብር ባለቤት
ክርስቶስን የሚያመልኩ ክርስቲያን ናቸው። እጅግም ባለጸጎች
ነበሩ ነገር ግን ከእርስዋ በቀር ልጆች የሏቸውም በመልካም
አስተዳደግም አሳደጓት ለክርስቲያን የሚገባ ትምህርትን ሁሉ
አስተማሩዋት ደግሞም ጽሕፈትን አስተማሩዋት ሁልጊዜም
የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ታነባለች ይልቁንም የመነኰሳትን
ዜና ታነብ ነበር።

✏መጻሕፍትንም አዘውትራ ስለምታነብ የምንኲስና ልብስ
ለመልበስ ፈለገች በላይኛው ግብጽ ከሚገኙ ገዳማትም ወደ
አንዱ ገዳም ሒዳ ገባች ብዙ ዘመናትም ደናግልን እያገለገለች
ኖረች።

✏ከዚህም በኋላ የምንኲስና ልብስን ለበሰች ሰይጣንን ድል እስከ
አደረገችው ድረስ ሰይጣን የሚያመጣውን ሥጋዊ ፍትወት
እየታገለች ዐሥራ ሦስት ዓመት ኖረች። ንጽሕናን ከመውደዷ
ጽናት በተሸነፈ ጊዜ በትዕቢት ሊጥላት ወዶ በቤት መዛነቢያ
ልትጸልይ ቁማ ሳለች ተገልጦ ሣራ ሆይ ሰይጣንን ድል
አድርገሽዋልና ደስ ይበልሽ አላት እርሷም መልሳ እኔ ደካማ ሴት
ነኝ ከክብር ባለቤት ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ድል አድርጌ
ላበረው አልችልም አለችው።

✏ይህችም ቅድስት አብረዋት ላሉ ደናግል ጥቅም ያላቸውን ብዙ
ትምህርቶችን ታስተምራቸው ነበር እንዲህም ትላቸዋለች ከቀን
ብዛት ጠላት እንዳያስተኝ እኔ እንደምሞት አስቀድሜ ሳላስብ
እግሬን ከአንዱ መወጣጫ ደረጃ ወደ ሁለተኛም አውጥቼ
አላኖራትም።

✏ዳግመኛም ለሰው ርኅራኄ ማድረግ በተሻለው ነበር ይህንንም
በሚያደርግ ጊዜ የኋላ ኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ
ይኖራል በዜና አረጋውያን መነኰሳት መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈ
ሌሎች ብዙ ቃሎችንም ተናግራለች።

✏ታላቅ ተጋድሎም እየተጋደለች በዓቷም በባሕር ዳርቻ ሁኖ ሰባት
ዓመት ኖረች አንዲት ቀን እንኳ ከሰው አንዱም አላያትም እርሷ
ግን ሁሉን ታይ ነበር። ሸምግላ እስከ ሰማንያ ዓመት በደረሰች
ጊዜ ከዚህ ዓለም የሕይወት ማሠሪያ ተፈትታ የዘላለም ተድላ
ደስታ ወደሚገኝበት ሔደች።

🚩ጸሎቷ በረከቷ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።

✅ሰማዕቱ ሰለፍኮስ፦

✏ቅዱስ ሰለፍኮስ በዘመነ ሰማዕታት የነበረ ክርስቲያን ወጣት ነው:: በወቅቱ ያ የጭንቅና የመከራ ዘመን ከመምጣቱ በፊት በተቀደሰ ጋብቻ ለመኖር አስጠራጦኒቃ የምትባል ደግ የሆነች ክርስቲያናዊት ወጣት አጭቶ ነበር::

✏በዕጮኝነት ዘመናቸው ጾምን: ጸሎትንና ንጽሕናን በመምረጣቸው ያየ ሁሉ ያደንቃቸው ነበር:: ታዲያ የሠርጋቸው ቀን እየቀረበ ሲመጣ ያ የመከራ ዘመን (ዘመነ ሰማዕታት) ጀመረ::

✏ሁለቱ ንጹሐን ወጣት ክርስቲያኖች ተመካከሩና ወሰኑ:: በምክራቸውም መሠረት ሁለቱም ከነ ድንግልናቸው ሰማዕትነትን ለመቀበል ተዘጋጁ:: በዚች ዕለትም ስለ ቀናች ሃይማኖትና ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር ከብዙ ስቃይ በሁዋላ በከሃዲው ንጉሥ ትዕዛዝ ቅዱስ ሰለፍኮስ በሰማዕትነት አልፏል::

🚩ከቅዱሱ ሰማዕት በረከት አምላከ ቅዱሳን ያድለን::

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ቅዱስ ሰለፍኮስ ሰማዕት
2.እናታችን ቅድስት ሣራ ጻድቅት (ግብፃዊት)
3.አባ ሕልያስ ሰማዕት
4.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሐዲስ

🚩ወርሐዊ በዓላት፦
1.ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ
2.ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ አፈ በረከት
3.ቅዱስ ሚናስ ግብፃዊ
4.ቅድስት እንባ መሪና
5.ቅድስት ክርስጢና

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፬ ቀን !!!🚩መጋቢት 14በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!!!✅ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ፦✏ከ12ቱ ቅዱሳን ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ቶ...
23/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፬ ቀን !!!

🚩መጋቢት 14
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!!!
✅ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ፦

✏ከ12ቱ ቅዱሳን ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ቶማስ ብዙ መከራን በማሳለፉና የጌታችንን ጐን በመዳሰሱ ይታወቃል::

✏ቅዱስ ቶማስ እንደ ሌሎቹ ሐዋርያት በእሥራኤል ተወልዶ በዚያውም በሥርዓተ ኦሪት አድጐ ገና በወጣትነቱ የሰዱቃውያንን ማሕበር ተቀላቅሏል:: ሰዱቃውያን ሰው ከሞተ በሁዋላ አይነሳም (አልቦ ትንሳኤ) የሚሉ ናቸው:: መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማስተማር ሲጀምር ግን ቅዱስ ቶማስ ከነበረበት ማሕበር ወጥቶ ጌታችንን ተከተለ:: ጌታችንም ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ይሆን ዘንድ ሾመው:: የቀደመ ስሙ "ዲዲሞስ" ሲሆን ጌታችን "ቶማስ" ብሎታል::

✏ቅዱስ ቶማስ ጌታ አልዓዛርን ለማስነሳት በሔደ ጊዜ ሌሎች ሐዋርያት ጌታን "አይሁድ ይገድሉሃል ቅር" ሲሉት እርሱ ግን "እንሒድና አብረን እንሙት" ሲል ፍቅሩን አሳይቷል:: (ዮሐ. 11:16)

✏ጌታችን ትንሳኤውን ለደቀ መዛሙርቱ በገለጠ ጊዜ ያልነበረው ቶማስ ካላየሁ አላምንም አለ:: ምክንያቱም:-
1.ለጌታችን ከነበረው ፍቅር የተነሳ እውነት አልመስልህ ቢለው::
2.አንድም ሌሎቹ ሐዋርያት "ትንሳኤውን አየን" እያሉ ሲያስተምሩ እኔ ግን "ሰማሁ" ብየ ማስተማሬ ነው ብሎ በማሰቡ ነበር::

✏ለጊዜው ጌታ ተገልጾ ቢገስጸው "እግዚእየ ወአምላኪየ (ጌታየና አምላኬ)" ብሎ ፍጹም ሃይማኖቱን ገልጿል:: ለፍጻሜው ግን የጌታችንን ጎን (መለኮትን) ይዳስስ ዘንድ ባለቤቱ እንዳደለው ያጠይቃል:: መለኮትን የዳሰሰች ይሕቺ ቅድስት እጁ ዛሬም ድረስ ሕያው ናት:: በሕንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥም በክብር ተቀምጣለች::

✏ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው ሐገረ ስብከት ሲከፋፈሉ ለቅዱስ ቶማስ ሕንድና በዙሪያዋ ያሉ ሃገራት ደረሱት:: ከዚህ በሁዋላ ነው እንግዲህ ዘርዝረን የማንጨርሰውን ተጋድሎ የፈጸመው:: ቅዱሱ በነበረው ፍጹም ትጋት አባቶቻችን "ዘአሠርገዋ ለብሔረ ሕንደኬ (ሕንድን በወንጌል ያስጌጣት)" ሲሉ ያከብሩታል::

✏ቅዱስ ቶማስ ንጉሥ ሉክዮስንና የሃገሩን ሕዝብ ለማሳመን በችንካር መሬት ላይ ወጥረው ቆዳውን ገፈውታል:: ቆዳውንም እንደ ገና ሰፍተው: አሸዋ ሞልተው አሸክመውታል:: በየመንገዱ የተገፈፈ ገላውን ጨው ቢቀቡት በጎች መጥተው ግጠው በልተውታል:: በዚሕ ምክንያት:-
"ኩሉ የአኪ እንዘ የአኪ ዘመኑ::
አባግዒሁ ለቶማስ እስመ አራዊተ ኮኑ::" ብለዋል ሊቃውንቱ::

✏በሁዋላ ግን ከፎቅ ወድቃ የሞተችውን የንጉሡን ሚስት በተገፈፈ ቆዳው በማዳኑ ሁሉም አምነው ተጠምቀዋል::

✏ቅዱሱ ሐዋርያ ልክ እንደ ቅዱስ ዻውሎስ አንዳንዴ በፈሊጥ: ሌላ ጊዜም በመከራ ለወንጌልና ለቤተ ክርስቲያን ተጋድሏል:: ያለ ማቁዋረጥም ከሕንድ እስከ ሃገራችን ኢትዮዽያ ድረስ ለ38 ዓመታት ወንጌልን ሰብኩዋል::

✏በመጨረሻም በ72 ዓ/ም በሰማዕትነት አርፏል:: መቃብሩና ቅድስት እጁ ዛሬ ድረስ ሕንድ ውስጥ አሉ::

🚩ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአገልጋዩ ቅዱስ ቶማስ ጸጋ በረከት ይክፈለን::

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ (ጋኔን ያደረባት ሴትን ፈውሶ አሕዛብን ያሳመነበት)
2.ቅዱስ አባ ባጥል ትሩፈ ምግባር (ባንድ ወቅት ከእስክንድርያ ዝሙትን ለማጥፋት የተጋደሉ ጻድቅና አረጋዊ አባት)
3.ቅዱስ ሲኖዳ (ሺኖዳ) ሰማዕት
4.ቅዱስ ቄርሎስ ሊቀ ዻዻሳት

🚩ወርሐዊ በዓላት፦
1.አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል)
2.ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ
3.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ
4.ቅዱስ ሙሴ (የእግዚአብሔር ሰው)
5.አባ ስምዖን ገዳማዊ
6.አባ ዮሐንስ ጻድቅ
7.እናታችን ቅድስት ነሣሒት

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፫ ቀን!!!🚩መጋቢት 13በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!✅ታላቁ ቅዱስ መቃርስ፦✏ታላቁ ቅዱስ መቃርስ (ቅዱስ መቃሬ) "ጽድቅ እንደ መ...
22/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፫ ቀን!!!

🚩መጋቢት 13
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!
✅ታላቁ ቅዱስ መቃርስ፦

✏ታላቁ ቅዱስ መቃርስ (ቅዱስ መቃሬ) "ጽድቅ እንደ መቃርስ" የተባለለት: የመነኮሳት ሁሉ አለቃ: ከ80 ዓመታት በላይ በበርሃ የኖረ: በግብፅ ትልቁን ገዳም (አስቄጥስን) የመሠረተ: ከ50,000 በላይ መነኮሳትን ይመራና ይመግብ የነበረ ፍፁም ጻድቅ ነው::

✏በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በዚሕች ዕለት አርዮሳውያን ደጉን ታላቅ አባት በሰንሰለት አስረው ከግብፅ ወደ እስያ በርሃ ከጉዋደኛው ቅዱስ መቃርዮስ እስክንድርያዊ ጋር አሰድደውታል:: በዚያ ለ2 ዓመታት ስቃይን ከተቀበሉ በሁዋላ በአረማውያን ፊት ድንቅ ተአምር አድርገው አረማውያንን ከነ ንጉሳቸው አጥምቀዋል::

✏በተሰደዱባት ሃገርም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ (ስም አጠራሩ ይክበርና) እመቤታችንን: ቅዱሳን ሐዋርያትን: አዕላፍ መላእክትን: በተለይ ደግሞ ቅዱሳኑን ዳዊትን: ዮሐንስ መጥምቁንና ወንጌላዊውን: ማርቆስን: ዼጥሮስን: ዻውሎስን አስከትሎ ወርዶ ተገልጦላቸዋል::

✏በቅዱስ አንደበቱም የምሕረት ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል:: ታላቁ ቅዱስ መቃርስና ባልንጀራው መቃርዮስ ከ2 ዓመታት ስደትና መከራ በሁዋላ ስደት በወጡባት በዚችው ዕለት መልዐኩ ኪሩብ በክንፉ ተሽክሞ ወደ ግብፅ መልሷቸዋል:: በወቅቱም ጻድቁን ለመቀበል ከ50,000 በላይ የሚሆኑ ልጆቻቸው መነኮሳት በዝማሬ ወጥተዋል::

✅አርባ ሐራ ሰማይ፦

✏አርብዐ ሐራ ሰማይ ማለት በዘመነ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ሰማዕትነትን የተቀበሉ 40 ጭፍሮች ናቸው:: "ሐራ ሰማይ" የተባሉት በምድር ሲሠሩት የቆዩትን የውትድርና ሥራ ትተው የክርስቶስ (የሰማያዊው ንጉሥ) ጭፍራ ለመሆን በመብቃቸው ነው::

✏አርባው ባልንጀሮች ወጣትና ጐበዝ ክርስቲያኖች ነበሩ:: በእርግጥ እነርሱ ሰማዕትነት የተቀበሉበት ጊዜ ዘመነ ሰማዕታት አልነበረም:: ነገር ግን ሰማዕትነት የጊዜ : የቦታ : የሁኔታ : የእድሜ : የጾታ : የዘር . . . ልዩነት አያግደውምና እነዚህ ወጣቶች ለዚህ ክብር በቅተዋል::

✏ነገሩ እንደዚህ ነው:-
በ330ዎቹ አካባቢ የዓለም ንጉሥ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ አንዱን መኮንኑን ወደ ቂሣርያ አካባቢ ይልከዋል:: የተላከው አካባቢውን ለማስተዳደር ሲሆን ቦታው ስብስጥያ (ሴባስቲ) ይሰኛል::

✏መኮንኑ ክርስቲያኖችን እንዲንከባከብ ጥብቅ ትዕዛዝ ከንጉሡ ቢሰጠውም ፍቅረ ጣዖት በልቡ የነበረበት ሰው ነውና ክርስቲያኖችን ይጨቁን : ያሰቃይ : ይገድል : አብያተ ክርስቲያናትን ያፈርስ ገባ::

✏በጊዜው ይህንን የተመለከቱት 40ው ጭፍሮች በአንድነት መክረው መኮንኑን ገሠጹት:: ስመ ክርስቶስንም ሰበኩለት:: እርሱም በፈንታው 40ውን አስሮ ብዙ አሰቃያቸው::

✏በመጨረሻ ግን 40ውንም የበረዶ ግግር አስቆፍሮ: ከነ ሕይወታቸው እስከ አንገታቸው ቀብሮ : ለ39 ቀናት ያለ ምግብ በጽኑ ስቃይ አቆያቸው:: በ40ኛው ቀን ግን ከ40ው አንዱ "ይህን ሁሉ መከራ የምቀበል ለምኔ ነው?" ብሎ "አውጡኝ!" እያለ ጮኸ::

✏ክርስቶስን አስክደው ወደ ውሽባ ቤት (ሻወር ቤት) ሲያስገቡት ፈጥኖ ሞተ:: በነፍስም በሥጋም ተጐዳ:: ነገር ግን ከአረማውያን ወታደሮች አንዱ "እኔን አስገቡኝ" ስላለ እንደገና 40 ሆኑ::

✏በዚህች ዕለትም 40ውን ጭን ጭናቸውን በመጅ እየሰበሩ ሲገድሏቸው ቅዱሳን መላእክት በአክሊል ከልለው : በዝማሬ አጅበው ወደ ገነት ወስደዋቸዋል:: ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስም በጊዜው ነበርና ገድላቸውን ጽፎ ውዳሴ ደርሶላቸዋል:: ቤተ ክርስቲያናቸውንም አንጾ የካቲት 16 ቀን እንዲቀደስ አድርጉዋል::

✏ብጹዕ አባታችን አባ ሕርያቆስም በቅዳሴ ማርያም ድርሰቱ ላይ በቅዱሳኑ ላይ የሆነውን ነገርና ሥልጣነ እግዚአብሔርን እያደነቀ እንዲህ ሲል ተናግሯል::

✏"ኦ አውጻኢሁ ለዘእንተ ውስጥ:: (በውስጥ ያለውን የምታስወጣ)"
"ወአባኢሁ ለዘእንተ አፍአ:: (በውጪ ያለውንም የምታስገባ)"
"ወይእዜኒ ስማዕ አውያቶሙ ለሕዝብከ እለ ይጼውዑከ በጽድቅ:: (እንግዲህ በእውነት የሚጠሩህን የወገኖችህን ጩኸት /ልመና/ ስማ)" ((ቅዳሴ ማርያም ቁ.146))

✏ስለዚህ በውስጥ ያለን አንታበይ:: ያለንበት የእኛ አይደለምና:: እንዳንወድቅም እንጠንቀቅ:: ብዙዎቹ የቆሙ ሲመስላቸው ወድቀዋልና:: ያሉ ሲመስላቸውም ወጥተዋልና::

✏በውጪ ያለንም ተስፋ አንቁረጥ:: ወደ ሁዋላም አንበል:: ወደ ቤቱ ሊመልሰን : በክብሩ ማደሪያ ሊያኖረን የታመነ አምላክ አለንና::

✏ቸሩ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ገብቶ ከመውጣት : አግኝቶ ከማጣት ይሠውረን:: ከሰማዕታቱ በረከትም አይለየን::

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ታላቁ ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት ሁሉ አለቃ-ስደቱ)
2.ቅዱስ መቃርዮስ እስክንድርያዊ
3.40 ቅዱሳን ሰማዕታት (ከሃገረ ስብስጥያ)
4.ቅዱስ ዲዮናስዮስ (ጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት)

🚩ወርኀዊ በዓላት፦
1.እግዚአብሔር አብ
2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት
3."99ኙ" ነገደ መላዕክት
4.ቅዱስ አስከናፍር
5."13ቱ" ግኁሳን አባቶች
6.ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
7.አቡነ ዘርዐ ቡሩክ

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፪ ቀን !!!!🚩መጋቢት 12በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን!!!!✅ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቀ ዻዻሳት፦✏በዚች እለት የከበረና የተመሰገነ የእስክን...
21/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፪ ቀን !!!!

🚩መጋቢት 12
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን!!!!
✅ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቀ ዻዻሳት፦

✏በዚች እለት የከበረና የተመሰገነ የእስክንድርያጨሊቀ ጳጳስ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ ሁለተኛ ተሿሚ የድሜጥሮስ ድንግልናው የተገለጠበት ሆነ።

✏የመገለጡ ምክንያት እንዲህ ነው ከእርሱ በፊት ሊቀ ጳጳሳት ለነበረው ለቅዱስ ዮልያኖስ መንፈቀ ሌሊት በሆነ ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገልጦለት አንተ ወደ ክብር ባለቤት ወደ ክርስቶስ ትሔዳለህ የወይን ዘለላ ይዞ ነገ ወደአንተ የሚገባ ሰው ከአንተ በኋላ ሊቀ ጳጳስ መሆን የሚገባው እርሱ ነው አለው።

✏ማግስት በሆነ ጊዜ የከበረና የተመሰገነ ድሜጥሮስ የወይን ዘለላ ወደ ከበረ ዮልያኖስ ገባ ቅዱስ ዮልያኖስም ያዘው ከእኔ በኋላ ሊቀ ጳጳስታችሁ እነሆ ብሎ ለህዝቡ አስረከባቸው ስለ እርሱም የእግዚአብሔር መልአክ እንደተገለጠ ነገራቸው።

✏አባ ዮልያኖስም በአረፈ ጊዜ በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ከእርሱ በቀር ሚስት ኑራው የተሾመ የለም።

✏ሰይጣን በሰዎች ልቦና አደረ ብእርሱ ላይ በመናገር የሚያሙት ሆኑ ስለዚህ ነገር ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ለቅዱስ ድሜጥሮስ ተገልጦ እንዲህ አለው ከህዝቡ የሚያሙህ አሉና ከልባቸው ጥርጥርን ልታርቅ ይገባሃል አንተ እራስህን አድነህ በአንተ ምክንያት ሌሎች ይጠፉ ዘንድ አይገባህም ቸር ጠባቂ ከሆንክስ ወገኖችህን ለማዳን ታገል

✏ማግስት በሆነ ጊዜ ይህም መጋቢት 12 ቀን የቁርባንን ቅዳሴ ቀደሰ ሕዝቡም እንዲጠብቁት እንጂ ከቤተክርስትያን እንዳይወጡ አዘዛቸው ደግሞ እሳትን እንዲአነዱ ወደ ሴቶች መቋሚያ ልኮ ሚስቱን አስመጣት ከስራው የተነሳ ሕዝቡ ያደንቁ ነበር ምን ሊሠራ እንደፈለገ ሕዝቡ አላወቁምና።

✏ከዚህ በኋላ ቅዱስ ድሜጥሮስ ተነስቶ ተንቀሳቀሰ ከእሳቱም መካከል ገብቶ በመቆም እሳቱ እየነደደ በውስጡ ጸለየ ከእሳቱም ፍህም በእጁ ዘግኖ በልብሰ ተክህኖው ላይ አኖረ በእሳቱም ውስጥም ቁሞ ለረጅም ጊዜ ጸለየ በልብሰ ተክህኖ ውስጥ ያለ እሳትም አይቀጣጠልም።

✏ከዚህ በኋላ ሚስቱን ጠርቶ ያንን እሳት በመጎናጸፊዋ ውስጥ ጨመረ ረጅም ጸሎትን ጸለዬ እሳቱም ከልብሶቻቸው ምንም ምን አላቃጠለም ሕዝቡም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

✏ሕዝቡም ይህን ስራ በምን ምክንያት እንደሰራ ያስረዳቸው ዘንድ የከበረ ድሜጥሮስን ለመኑት እርሱም ከሚስቱ ጋር ያለውን ገድል ገለጠላቸው ያለ ውዴታው እርሷም ጋብቻን ሳትሻ እንዳጋቡት እንዲህም አለ።

✏እነሆ በአንድነት እኛ 38 አመት ስንኖር በጋብቻ ስርአት ከተገናኘንበት ጊዜ ጀምሮ በአንድ አልጋ አንድ ልብ ለብሰን እንተኛለን ግን ወንዶች ሴቶችን በግብር እንደሚአውቋቸው ሴትጨእንደሆነች አላውቃትም።

✏በዚህ ሁሉ ዘመን በየ ሌሊቱ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ እየወረደ በክንፎቹ ይሸፍነናል ይህንንም በዚህ ሁሉ ዘመን መግለጥ አልፈልግም ነበር ግን እናንተ ከበደል ትድኑ ዘንድ እርሱ እግዚአብሔር አዘዘኝ እንጂ።

✏ከአዩትና ከሰሙት የተነሳ ሕዝቡም አደነቁ እርሱን ከማማታቸው የተነሳ ይቅር ይላየው ዘንድ ቅዱስ ድሜጥሮስን እያለቀሱ ለመኑት እርሱም ሰሕተታቸውን ይቅር ብሎ በጎ ስራን ከሚሰራ ከሰይጣን እንጂ ከእናንተ አይደለምና አትዘኑ አላቸው።

✏ከዚህ በኋላ ባረካቸው ከአዩት ተአምር የተነሳ እግዚአብሔር እያመሰገኑ ወደ ቤታቸው ገቡ

🚩በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቀ ዻዻሳት (ደንግልናው የተገለጠበት)
2.ቅድስት ልዕልተ ወይን
3.ቅዱስ መላዚ ሰማዕት

🚩ወርኀዊ በዓላት፦
1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላዕክት (ጠንቁዋዩን በለዓምን የገሰጸበትና አህያዋን እንድትናገር
ያደረገበት)
2.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
4.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት)
5.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
6.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፩ ቀን !!!🚩መጋቢት 11በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!✅ቅዱስ ቴዎቄጤኖስ ሰማዕት፦✏በዚች ቀን በንጉስ መክስምያኖስ ዘመን ቅዱስ ቴ...
20/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲፩ ቀን !!!

🚩መጋቢት 11
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!
✅ቅዱስ ቴዎቄጤኖስ ሰማዕት፦

✏በዚች ቀን በንጉስ መክስምያኖስ ዘመን ቅዱስ ቴዎቄጤኖስ በሰማዕትነት አረፈ ይህም ቅዱስ አስቀድሞ ወታደር ነበር ትጥቁን በንጉስ ፊት ጥሎ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ ከእርሱም ጋር ብፅዕት እስክንድራ አለች።

✏ንጉሡም ሰምቶ ተቆጣ ልብሱን አስወልቀው የሴቶችን ልብስ አልብሰው ከሚፈትሉ ሴቶች ጋር እንዲጨምሩት ከዚያም የጋለ የብረት መንኮራኩር በላዩ አድርገው ዘቅዝቀው ቁልቁል እንዲሰቅሉት አዘዘ።

✏ሁለተኛም እንዲህ ብሎ አዘዘ የፈላ ቅጥራን የተመላ ወጭት አምጥታችሁ ወደ ጆሮው አስቲደርስ በራሱ ላይ ድፉበት ደግሞ ከተሰቀለበት አውርደው ከእስረኛዋ እስክንድራ ጋር በፊቱ እንድያቆሙት አዘዘ።

✏ከዚህ በኋላ ምላሱን እንዲቆርጡት አዘዘ በሊህ ቅዱሳን በአንገቶቻቸው የሚካበዱ ድንጋዮችን አስረው በኤፍራጠስ ወንዝ ውስጥ እንዲጥሏቸው አዘዘ በዚያም ተጋድሏቸውንና ምስክርነታቸውን ፈጸሙ ሥጋቸውንም ምዕመናን አግኝተው ስውር ቦታ ቀበሩት

🚩በረከታቸው ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ይኑር አሜን

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.አባ አሌፍ ጻድቅ (ከተስዓቱ ቅዱሳን)
2.ቅዱስ ቴዎቄጤኖስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ባስሊዖስ (ዻዻስና ሰማዕት)
4.አባ ኤፍሬም ሰማዕት
5.አባ ኤልያስ ሰማዕት

🚩ወርሐዊ በዓላት፦
1.ቅዱስ ያሬድ ካህን
2.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
4.ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና
5.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲ ቀን !!!!🚩መጋቢት 10 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!!✅በዓለ መስቀል (ቅዱስ ዕፀ መስቀል) ፦✏በዚች እለት የክብር ባለቤት ጌ...
19/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፲ ቀን !!!!

🚩መጋቢት 10
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!!
✅በዓለ መስቀል (ቅዱስ ዕፀ መስቀል) ፦

✏በዚች እለት የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት ነው ። የዚህም የከበረ ዕፀ መስቀል መገለጡና መገኘቱ ሁለት
ጊዜ ሆኗል።መጀመሪያ የፃድቁ ንጉስ የቆስጠንጢኖስ እናት በሆነች በንግስት ህሌኒ እጅ ነው።

✏«እርሷ ለእግዚአብሄር ተስላ ነበርና ልጇ ቆስጠንጢኖስ ወደ
ክርስቲያን ሀይማኖት ቢገባ ወደ ኢየሩሳሌም ሄዳ መስቀሉን እስከ አገኘችው ድረስ ልትፈልግው በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ልታንፃቸው ነው።

✏ከዚህ በኃላ ልጇ አምኖ የክርስትና ጥምቀትን በተጠበቀ ጊዜ እሌኒ ቅድስት ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች ከእረሷ ጋርም ብዙ ሰራዊት ነበር ደርሳም ስለ ከበረ መስቀል መረመረች የሚያስረዳት አላገኘችም የአይሁድ ወገን የሆነ አንድ ሽማግሌ ሰው አስራ በርሀብና በጥማት አሰቃየችው ።

✏በተጨነቀም ጊዜ ለንግስት እሌኒ የጉልጎታን ኮረብታ አስጠርጊ ብሎ ነገራት እርሷም ይጠርጉ ዘንድ አይሁድን አዘዘቻቸው። ቤቱን የሚጠርግ ሰው ሁሉ ጥራጊውን በውስጡ የከበረ መስቀል በአለበት በጌታችን መቃብር ላይ እንዲጥል አይሁድ አስቀድመው አዝዘው ነበርና ንግስት እሌኒ እስከ ደረሰችበት ጊዜ ከሁለት መቶ አመት በላይ ጥራጊያቸውን ሲጥሉበት ኖሩ ኮረብታም ሆነ።

✏አይሁድም በጠረጉ ጊዜ ሶስት መስቀሎች ተገለጡ የክብር ባለቤት ክርስቶስ የተሰቀለበት የትኛው እንደሆነ አላወቁም። የሞተ ሰውም አግኝተው አመጡ ። አንዱንም መስቀል አምጥተው በሞተው ሰው ላይ አኖሩት አልተነሳም ደግሞ ሌላውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ
አኖሩ አሁንም አልተነሳም ከዚህም በኃላ ሶስተኛውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አደረጉት ያንጊዜ የሞተው ሰው ተነሳ እሌኒም የክርስቶስ መስቀል እንደሆነ አውቃ ሰገደችለት የክርስቲያንም ወገኖች ሁሉ ሰገዱለት።

✏ለልጅዋ የላከችው ይህ መስቀል ነው የሚል በሌላ መፅሀፍ ይገኛል የቀረው ግን ግንዱ በውስጡ ተተክሎበት የነበረው ከእርሱም እኩሌታውን ከቅንዋቱ ጋራ ወደ ልጅዋ የላከችው ነው። ከዚህም በኃላ ስራአታቸውና የህንፃቸው ነገር በመስከረም ወር በአስራ ሰባት ተፅፎ የሚገኝ አብያተ ክርስቲያናትንና የከበሩ ቦታዎችን አነፀች።

✏ሁለተኛው በሮሙ ንጉስ በህርቃል ዘመን የሆነው ሲሆን የፋርስ ሰዎች በግብፅ አገር ሳሉ ወደ አገራቸው ሊመለሱ ወደዱ። ከሹማምንቶቻቸው አንዱ የጦር መኰንን ተነጥሎ ወደ
ኢየሩሳሌም አልፎ ደረሰ ወደ ከበረ መስቀል ቤተ ክርስቲያንም ገባ። መስቀሉም በላዮ በተተከለበት ግንድ ፊት ታላቅ ብርሀን ሲበራ አይቶ ሊያነሳው እጁን ዘረጋ። እሳትም ወጥታ እጁን አቃጠለችው።

✏ከክርስቲያን በቀር ማንም ሊነካው እንደማይችል የመስቀልን የክብሩን ነገር ሰዎች ነገሩት። ሁለት ዲያቆናትንም ይዞ የከበረ መስቀልን እንዲሸከሙ አዘዛቸው ከኢየሩሳሌምም ብዙ ሰዎችን
ማርኮ ወደ አገሩ ተመለሰ።

✏የፋርስ ሰዎች ኢየሩሳሌምን እንዳጠፏት ብዙዎች ሰዎችንም እነድ ማረኩና የከበረ የክርስቶስንም መስቀሉን እንደ ወስዱየሮም ንጉስ ህርቃል በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። ስለርሱም እንዲፆሙ ምእመናንን አዝዞ ወደፋርስ ዘምቶ ወጋቸው ብዙዎችንም ገደላቸው የከበረ እፀ መስቀልንም እየፈለገ
በሀገራቸው ሁሉ ዞረ ግን አላገኘውም።

✏ያ ዲያቆናቱና መስቀሉን የወሰደ መኰንን ከቦታዎች በቤቱ አነፃር ባለ በአንድ ቦታ ላይ ወስዷቸው ጥልቅ ጉድጓድእንዲቆፍሩ አዝዞ በዚያ የከበረ መስቀልን አስቀበረ እነዚያንም ዲያቆናት ገደላቸው።

✏ነገር ግን ያ መኰንን የማረካት የካህናት ወገን የሆነች በእርሱ ቤት የምትኖር አንዲት ብላቴና ነበረች። እርሷም የከበረ መስቀልን ሲያስቀብርና ሁለቱን ዲያቆናት ሲገድላቸው በቤቱ ውስጥ ሁና በመስኮት ትመለከት ነበር ወደ ንጉስ ሕርቃልም ሂዳ መኰንኑ ያደረገውን ሁሉ ነገረችው።

✏ይህንንም ንጉስ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ያቺ ብላቴናም መራችው ከእርሱም ጋራ ብዙ ሰራዊት ሆኖ ኤጲስቆጶሳትና ካህናትም ነበሩ ።ወደ ቦታውም እስከምታደርሳቸው ያቺን ልጅ ተከተሏት ቆፍረውም የከበረ እፀ መስቀልን አገኙት ከአዘቅቱም አወጡት ንጉሱና ሰራዊቱም ሰገዱለት።

✏በልብሰ መንግስቱም አጐናፀፈው ታላቅ ክብርንም አከበረው እጅግም ደስ አለው ከሰራዊቱ ጋር። የዚህም መስቀል ሁለተኛ የተገለጠበትና የተገኘበት በዚች ቀን በመጋቢት አስር ነው። ከዚህ በኃላ ንጉሱ የከበረ እፀ መስቀልን ተሸክሞ ወደ ቁስጥንጥንያ ከተማ ወሰደው።

✏መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ካረገ ከዓመታት በሁዋላ አይሁድ በአንድ ነገር ተቸገሩ:: የክርስቶስን ሐዋርያት እያሳደዱ ቢገድሉም ከመስቀሉና ሥጋ ክርስቶስ አርፎበት ከነበረው ጐልጐታ ላይ የሚደረገውን ተአምር ግን መግታት አልተቻላቸውም::

✏መቼም ለተንኮል አያርፉምና ቅዱስ መስቀሉን ሽፍቶቹ ከተሰቀሉባቸው ጋር ደርበው አርቀው ቀበሩት:: አካባቢው የጉድፍ መጣያ እንዲሆንም አዋጅ ነገሩ:: ለክፋት ሲሆን ተባባሪው ብዙ ነውና ለ300 ዓመታት ያህል ቆሻሻ ቢጥሉበት ተራራ ሆነ::

✏ከዚህ ሁሉ ነገር በሁዋላ እናታችን ቅድስት እሌኒ (ሔለና)
በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነት: በቅዱስ ኪራኮስ መሪነት: በቅዱስ
ሚካኤል ረዳትነት ደመራ አስደምራ: እጣን አጢሳ መካነ
መስቀሉን አገኘች::

✏መስከረም 17 ቀን የተጀመረው ቁፋሮ መጋቢት 10 ቀን
ተጠናቆ: ንጹሕ መስቀሉ ወጥቶ ብርሃን በርቷል: ሙታን
ተነስተዋል:: ከ10 ዓመት በሁዋላም የመስቀሉ ቤተ መቅደስ
ታንጾ መስከረም 17 ቀን ተቀድሷል::

✏ይህ ቅዱስ ዕፀ መስቀልም በደጉ አፄ ዳዊት ዘመን ወደ
ሃገራችን መጥቶ: በጻድቁ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ አማካኝነት በደብረ
ከርቤ (ግሸን ማርያም) ተለብጦ ተቀምጧል::

🚩የቅዱስ መስቀሉ ጥበቃ አይለየን አሜን

🚩 ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ቅዱስ ዕፀ መስቀል
2.ቅድስት ዕሌኒ ንግሥት
3.ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ
4.ቅዱስ መቃርስ ዘኢየሩሳሌም

🚩 ወርሐዊ በዓላት፦
1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
2.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
3.ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ጻድቅ ንጉሥ
4.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
5.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ)

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!!

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፱ ቀን!!!🚩መጋቢት 9በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን!!!!✅ቅዱስ አውሳብዮስ ሰማዕት ፣ ቅዱስ ኩትን ሐዋርያ✏ዚች ቀን የከበሩ የእንድርያይ...
18/03/2022

✅መፅሀፈ ስንክሳር የመጋቢት ፱ ቀን!!!

🚩መጋቢት 9
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን!!!!
✅ቅዱስ አውሳብዮስ ሰማዕት ፣ ቅዱስ ኩትን ሐዋርያ

✏ዚች ቀን የከበሩ የእንድርያይና ሚስቱ አውሳብዮስና አርማ ሌሎች አርባ ሰዎችም በሰማዕትነት አረፉ።

✏እሊህም ምርጦችለረከሰ ከወርቅና ከብር ለተሰራ ጣዖት ማምለክን አምቢ ስላሉ የክብር ባለቤት ለሀነ ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ስሙ አላውያን ጽኑ የሆነ ስቃይን አሰቃዩአቸው።

✏ከዚህ በኋላ እራሳቸውን በሰይፍ ቆረጡ የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግስተ ሰማያትተቀበሉ በረከታቸው ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ይኑር አሜን።

✅ቅዱስ ኩትን ሐዋርያ፦

✏ቅዱስ ኩትን በዘመነ ሐዋርያት የነበረ: ከአሕዛብ ወደ ክርስትና በቅዱስ ዻውሎስ አማካኝነት የተመለሰ: ከቅዱሳን ሐዋርያት እግር ሥር ቁጭ ብሎ ይማር ዘንድ የታደለ: በፍፁም ድንግልናው የተመሰገነ ሐዋርያዊ አባት ነው::

✏ይህ ቅዱስ ሚስት ነበረችው:: ግን በትዳር ውስጥ ሆኖ ድንግልናን መጠበቅ እንደሚቻል ያሳየ የሐዲስ ኪዳን ሰው ነው:: ቅዱስ ኩትን በንጽሕናው: በአገልግሎቱና በጣዕመ ስብከቱ በሐዋርያትና ምዕመናንም ተወዳጅ ነበር:: ለብዙ ዘመናት በወንጌል አገልግሎት ኑሮ በዚሕች ቀን በመልካም ሽምግልና አርፏል::

🚩ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦
1.ቅዱስ ኩትን ሐዋርያ
2.ቅዱስ እንድርያኖስ ሰማዕት
3.ቅዱስ አውሳብዮስ ሰማዕት
4."2,000" ሰማዕታት (የአባ ኖብ ማሕበር)

🚩ወርሐዊ በዓላት፦
1.አባ በርሱማ ሶርያዊ (ለሶርያ መነኮሳት ኁሉ አባት)
2.አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ (ኢትዮዽያዊ)
3."318ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት (ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ)
4.የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
5.አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ (ኢትዮዽያዊ)
6.ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ (ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት)

✅ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
አሜን አሜን አሜን!!!!

Address

Ethiopian Street 10
Jerusalem

Opening Hours

Monday 06:00 - 18:00
Tuesday 06:00 - 18:00
Wednesday 06:00 - 18:00
Thursday 06:00 - 18:00
Friday 06:00 - 18:00
Saturday 10:00 - 18:00
Sunday 10:00 - 18:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኢየሩሳሌም ገዳማት ስብከተ ወንጌል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category