እቅበተ ተዋሕዶ

እቅበተ ተዋሕዶ ነገረ ቤተ ክርስቲያንና ኦርቶዶክሳዊ ዕይታዎች ይቀርቡበታል።

 #የአቡጊዳ ሽፍታ ስትሆን የምትጽፈው ዜና 😂        ስርዋጽ ለፈገግታ ፣ {  #አጀንዳችን  #አሁንም  #አርሲ ነው} --***-- ይህ ዜና እጅ እግር የለውመ። ምን ለማለት እንደተፈለገም...
17/06/2026

#የአቡጊዳ ሽፍታ ስትሆን የምትጽፈው ዜና 😂
ስርዋጽ ለፈገግታ ፣
{ #አጀንዳችን #አሁንም #አርሲ ነው}
--***--
ይህ ዜና እጅ እግር የለውመ። ምን ለማለት እንደተፈለገም ጸሐፊው ራሱ አያውቀውም። በአንድ ዓመት ውስጥ ከMBA ወደ PHD ምርቃት። ወዮ ። በቃ ጮማ ራስ ስትሆን እንዲህ ነው የምታስበው። 😂 ኢዮ ጩፋ በካራቴ የሚዘርረው ሰይጣንን ብቻ ሳይሆን ትምህርትንም መሆኑን እየነገረ ነው መሰል ። 😂

#በእምነት ስም የዋሓኑን ድኃ ሰብስቦ፣ የአዳራሹ ቂጡ እስኪላጥ ሲጨፍር የሚውል ሰውየ ፣ትምህርት ምን እንደሆነ ይገባዋል ማለት በራሱ ዘበት ነው።

አጀንዳችን  #አርሲ ነው ‼️‼️‼️___***--- "ሳልሳዊት አሁንም እንደታሰረች ናት። እስከ ዛሬዋ እለት ድረስ ፍርድ ቤት አልቀረበችም " - የታሳሪ ቤተሰብከዚህ ቀደም በዋልታና ፋና ሚዲያ...
16/06/2026

አጀንዳችን #አርሲ ነው ‼️‼️‼️
___***---
"ሳልሳዊት አሁንም እንደታሰረች ናት። እስከ ዛሬዋ እለት ድረስ ፍርድ ቤት አልቀረበችም " - የታሳሪ ቤተሰብ

ከዚህ ቀደም በዋልታና ፋና ሚዲያዎች የሰራችው ጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ የጸጥታ አካላት ልብስ በለበሱ አካላት ከቤቷ ተወስዳ ከታሰረች ሳምንት ቢሆናትም ፍርድ ቤት አለመቅረቧን ቤተሰብና የታሳሪዋ የቅርብ ሰው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

የታሳሪዋ እህት ሃይማኖት ባይነሳኝ ዛሬ በሰጠችን ቃል፣ ግለሰቧ ከታሰረች ሳምንት እንዳለፋት አስረድታ፣ " አሁንም እንደታሰረች ናት። እስከ ዛሬዋ እለት ድረስ ፍርድ ቤት አልቀረበችም" ብላለች። ፖሊስን ሲጠይቁ የሚሰጣቸው ምላሽ "ጠብቁ" የሚል ብቻ መሆኑን ገልጻለች።

የእስሩን ሁነት ስታስረዳም፣ "ከቤቷ ነው የወሰዷት። ከቤት ሠራተኛዋ ጋር ነው የወሰዷት። የፖሊስ ልብስ የለበሱ ሰዎች ናቸው ይዘዋት የሄዱት። የታሰረችበት ቦታ ፒያሳ አካባቢ ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወይም ማዕከላዊ የሚሉት ጋር ነው " ብላለች። ሠራተኛዋ ግን ከእስር መለቀቋ ተገልጿል።

ለእስር የሚያበቃት ወይም ቀድሞ የደረሳት ማስጠንቀቂያ፣ ሲወስዷት የነገሯት ጉዳይ እንዳለ ስንጠይቃት፣ "ምንም የለም። የአርሲው የግድያ ጉዳይ ይመስላል። እሱንም እርግጠኞች አይደለንም" ስትል ግምቷን ገልጻ፣ "እሷም 'ምንም ነገር አልነገሩኝም' ነው ያለችው" የሚል ምላሽ ሰጥታለች።

ታሳሪዋ፣ ከዚህ ቀደም በዋልታና ፋና ሚዲያዎች መስራቷን ተናግራ፣ " ከጥቂት ወራቶች በኋላ ግን እሱን ለቃው በግሏ መንቀሳቀስ ጀምራለች። በራሷ ዩትዩብ፣ ቲክቶክና ፌስቡክ ነው እየሰራች የነበረችው " በማለት አስረድታለች።

በተያያዘ፣ ከቤቷ የወሰዷት አካላት መጥሪያ ደብዳቤ እንዳልያዙ ገልጻ፣ "ሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 7 ሰዓት አካባቢ ከወሰዷት ቀኋላ ቤቱን በፖሊስ እያስጠበቁ ቆይተው ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ተመልሰው ማዘዣ ይዘው መጥተው ቤት ብርበራ አድርገዋል" ነው ያለችው።

የታሳሪዋ ቤተሰብ ባስተላለፈችው መልዕክት፣ "የልጅ እናት ናት። እናት፣ ልጇም እኛ ሙሉ ቤተሰቦቿ ተጨንቀን ነው ያለነው። የቤተሰብም አስተዳዳሪ ናት። በአግባቡና በሥርዓቱ ፍትህ ይሰጠን። ፍትህ አግኝታ ትፈታልን" ስትል ጠይቃለች። ሌላኛው መረጃ አቀባይ ግለሰቧ መታሰሯን ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የግለሰቧን መታሰር እና ፍርድ ቤት አለመቅረብ በተመለከተ ምን ምላሽ እንዳለው ማብራሪያ ለመጠየቅ ወደ ፌዴራል ፖሊስ ያደረገው ሙከራ ስልክ ባለመነሳቱ ለጊዜው አልተሳካም።

በተጨማሪ ለጉዳዩ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ቶማስ እሸቴ፣ "መረጃውን እናጣራ" ብለው፣ "ትክክለኛ ነው ወይ ጋዜጠኛ ናት? የሚለውን ነገር ማረጋገጥ ተገቢነት ያለው ይመስለኛል" ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ/ም
እቅበተ ተዋሕዶ

" #መነኵሴ ከተማ መኖር አለበት" እያለ  #የሚፎገላው ጸጋ ዘአብ ማን ነው 😎----***----ይህ ሰው ጸጋ ዘአብ አዱኛ ይባላል። ይህ እኩይ ፍላጻዊ ሰው ከዚህ ቀደም የሠራውን ጸላየ ቤተ ክ...
16/06/2026

" #መነኵሴ ከተማ መኖር አለበት" እያለ #የሚፎገላው ጸጋ ዘአብ ማን ነው 😎
----***----
ይህ ሰው ጸጋ ዘአብ አዱኛ ይባላል። ይህ እኩይ ፍላጻዊ ሰው ከዚህ ቀደም የሠራውን ጸላየ ቤተ ክርስቲያንነቱን የረሳንለት መስሎት ነው ? ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል የመጽሐፍ መ/ር ነኝ ሲል የኖረ ነው።

ከዚያ ከ4 ኪሎው ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ተመልምሎ ፣ በጥር 14 ቀን በ2015 ዓ.ም እነ #ሳዊሮስ ሕገ ወጥ የጨረቃ ጳጳሳት ሹመት ላይ በመሳተፍ " #የዘር #ጵጵስና" ተሹሞ ቤተ ክርስቲያንን በተቋም ደረጃ ለመናድ ለተደረገው ሙከራ ጉልህ አሻራውን ያሳረፈ የጥፋት ሰው ነው። ባይሳካለትም።

#የሔደበት ሕገ ወጥ መንገድ እንደማያዋጣው ሲያውቅ የሕዝቡንም ቁጣ ፈርቶ ወዲያው በእነ ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ (የአሁኑ አባ ) አስተባባሪነትና መንገድ ቀያሽነት የለበጣ ይቅርታ ጠይቆ ተመለሰ ተባለ።

ከዚያ የምሥራቅ ጉራጌ ሐገረ ብከት ሥራ አስኪያጅ ነኝ ብሎ በጠበጠ አበጣበጠ። ይኼው ዛሬም የክርስቶስን አካል ቤተ ክርስቲያንን ሊያደማ ጦሩን ይዞ ተነሥቷል።

የከተማ #አውደልዳይ መነኮሳትን፣ በከዘራም ቢሆን እያንቆራጠጥን ከተማ እንዲወጡ ማድረግ ካልቻልን የቤተ ክርስቲያን ስደቷና መገፋቷ ተጠናክሮ ይቀጥላል።

የመበለት #ፍትፍት፣ የአመዝራዎች #ሽቶ ያነሆለለውን ጎረምሳ ቀኖና ሐዋርያት፣ ሥርዓተ ምንኩስና፣ ሕይዎተ አበው አይገባውም።

#ማሳረጊያ ‼️
* ይማራሉ እንደ አካልየ በተባለላቸው ሊቅ ወንበር ሲያስተምሩ የነበሩት የቦሩ ሜዳው ዓይናማ ሊቅ መ/ር ኃይለ ማርያም ዘውዱ ለዚህ ግብስብስ ሞፈር ሰቀል ሰውየ: የሰጡትን ግሩም መልስ መስታወት በሚባለው የሊቁ ዩቲዩብ ግቡና ስሙት። ነፍሳችሁ ትረካለች።

* ሊንኩን በመጀመሪያው ኮመንት ቦክስ አስቀምጨላችኋለው።
እቅበተ ተዋሕዶ

15/06/2026

" አትግደል፣ አትገደል፣ ተጋደል፡፡''
ጥምረት ለቤተ ክርስቲያን !
ራስን ለማትረፍ የምንከተለው መሪ ቃላችን ነው።

 #በይርጋጨፌ ወረዳ 72 አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ ! EOTCMK TV ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በይርጋጨፌ ወረዳ ቤተ ክህነት የይ...
14/06/2026

#በይርጋጨፌ ወረዳ 72 አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አገኙ !

EOTCMK TV ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በይርጋጨፌ ወረዳ ቤተ ክህነት የይርጋጨፌ ደብረ ታቦር አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ከማኅበረ ቅዱሳን ይርጋጨፌ ወረዳ ማዕከል ጋር በመሆን ከሦስት ወር በላይ የቅድመ ጥምቀት ትምህርት ሲማሩ የቆዩ ሰባ ሁለት አዳዲስ አማንያን በብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል።

ከተጠማቂያኑ መካከል ሠላሳ ስድስት ሴቶች ሠላሳ ስድስት ወንዶች ይገኙበታል።

© ኤክቱስ በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

11/06/2026

አሰኮ ለመሄድ የተነሣው የቤተ ክህነቱ ግብስብስ ፣ ጋዶ ከምትባል ቀበሌ፣ ፊት ኋላ ዙር ተብሎ ከተመለሰ በኋላ፣አቦምሳ ድጋፍ አረግሁ ብሎ ዜና ያሰራል። የማይድን ተቋምና የማይድን በሽታ ሲያጠቃህ የምትሆነው።

Funny fact ‼️🤣
11/06/2026

Funny fact ‼️🤣

 #የጅዋር መሐመድ  #ጅሃዲስት ፓለቲክስ ‼️***ፔድሮ ፓኤዝ  የሚባል የSocity of Jesus አባል የነበረ ስፔናዊ የካቶሊክ ቄስ እና ግራኝ አህመድ የሚባል ሱማሊያዊ የአዳል ሱልጣኔት የ...
11/06/2026

#የጅዋር መሐመድ #ጅሃዲስት ፓለቲክስ ‼️
***

ፔድሮ ፓኤዝ የሚባል የSocity of Jesus አባል የነበረ ስፔናዊ የካቶሊክ ቄስ እና ግራኝ አህመድ የሚባል ሱማሊያዊ የአዳል ሱልጣኔት የጦር መሪ በ15ኛው እና 16ኛው መቶ ክፍለዘመን ላይ የተነሱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውድመት ላይ ስማቸው ገዝፎ የሚነበብ ሰዎች ናቸው።

ፔድሮ ፓኤዝ ትንሽም መንፈሣዊ ስልጣን ያለው ሲሆን በተለምዶ ግራኝ አህመድ ተብሎ የሚጠራው አህመድ ኢብን ኢብራሂም አልጋዚ ግን በእስልምና ውስጥ መንፈሣዊ ስልጣን የሌለው የጦር አዛዥ ብቻ ነበር።

ሁለቱም በተለያዬ መንገድ ስልት እና ዘመቻ በኩል እልፍ ኦርቶዶክሳውያንን ገ*ለዋል፣አብያተክርስቲያናት እና ገዳማትን አውድመዋል።

ስለፔድሮ ክፋት፣ሴራ እና ሸር ሲዘገብ የሚቆጣ የኢትዮጵያ ካቶሊክ አማኝ ብዙም አይታይም። ስለግራኝ አህመድ ስትጽፍ ግን ጩኸቱ ጣሪያ ነክቶ ሊመለስ ይሞክራል። እርሱ ያወደመውን እንደ ጽድቅ ፣የገደላቸውን እንደ ድል የሚቆጥሩ አክራሪ ዋሃቢስት ሙስሊሞች ብዙ ናቸው። [ተከባብሮ የሚኖረው ነባሩ ሙስሊምን ከእዚህ ሐሳብ አውጡልኝ]

የእዚህ ጩኸት ፊደል ቀራጭ ደግሞ የማይታዬው የእነ ጅዋር መሐመድ ጅሃዲስ ፓለቲካ ነው። ተረፈ ጅዋር የሆኑ ተንኮል እና ስራቸውን እንዳይታወቅባቸው ወደ መንግስት ተጠግተው ለሰይፍ ማንሻ ምቹ ቀን የሚጠብቁ ደግሞ የእዚህ ሐሳብ አውድማ ሆነው በስውር እያገለገሉ ናቸው።

ጅዋር መሐመድ ጅሃዲስት ፓለቲከኛነቱን የሚገልጥበት ቆንጆ ቀናት እስኪመጡለት ድረስ ሴኩላር ፓለቲከኛ ሆኖ በፓለቲካ ሜዳው ላይ "ተቃዋሚ" በሚል ስም ይሯሯጣል። ፍትህ በማያውቀው ዕሳቤው፣እኩልነትን ባለመደው መሻቱ፣ስርዓት በሚቀፈው ቆዳው ፣ ስለሀገሪቷ በደል ሊፈትት ሲጥር ስመለከተው ነፍሴን ይጨንቃታል።

ሜንጫ አንስተው የአምልኮ መሰዋት አድርገው የሰው ነፍስን የሚሰዋ ፣ በአምላካቸው ስም ባርከው የሚ*ርዱ፣ መግደል ሕይወት የሚያስገኝ የሚመስላቸው ሞኞች በእነ ጅዋር መሐመድ የተደበቀ የጅሃዲስት ፓለቲካ ተረግዘው የተወለዱ እንግዴዎች ናቸው።

አርሲ ከፓለቲካ ይልቅ እምነት ጦር ሆኖ የሚዋጋባት ስፍራ ናት። የእዚህ ጦር መስራች እና አብዢ፣ሰሪ እና ጠጋኝ ደግሞ ይህኝው ሰዎች ናቸው።

Kune Demelash kassaye -Arba Minch

እናንተ ‼️  #ቅድሚያ  #ራሳችሁን ሥሩና ትክክለኛ  #እረኛ ሁኑ።🤭_____****______የአዲስ አበባ አድባራት አስተዳዳሪዎች እና ጳጳሳቱ ዛሬ ተሰብስበው በአርሲ የወደመውን ቤተ ክርስቲያ...
09/06/2026

እናንተ ‼️ #ቅድሚያ #ራሳችሁን ሥሩና ትክክለኛ #እረኛ ሁኑ።🤭
_____****______
የአዲስ አበባ አድባራት አስተዳዳሪዎች እና ጳጳሳቱ ዛሬ ተሰብስበው በአርሲ የወደመውን ቤተ ክርስቲያን ሊሠሩ ወስነዋል አሉ ። እኛ #የምንፈልገው እሱን አይደለም። ቤተ ክርስቲያኑን እኛ እንሠራዋለን፤ እናንተ ቅድሚያ ራሳችሁን ሥሩና ትክክለኛ እረኛ ሁኑ።

እንኳን የአርሲውን የአዲስ አበባን ግዙፍ አድባራት የሚሠሩት ምእመናን አይደሉምን? የአዲስ አበባን አብያተ ክርስቲያናት እና እናንተን የገነባ ምእመን የአርሲው እንዴት ይከብደዋል። ይልቁንስ ራሳችሁን ሥሩ፤ ገዳዮቻችንን አስቁሙልን፣ ልጆቻችንን አትግደሉ ብላችሁ ሕዝባችሁን ጠብቁ።

የሚያኖራችሁን ሕዝብ ለመጠበቅ #ራሳችሁን ሥሩ እንጂ ቤተ ክርስቲያኑን እኛ እንሠራዋለን።
@ታደለ ሲሳይ
እቅበተ ተዋሕዶ

💊እነዚህ ሊቃውንት ሊታሰሩ ቀርቶ፣በክፉ ዓይን ሊታዩ የሚያስፈሩ ናቸውና፣  #ፍቱልን።‼️-----***----ከማኅበራዊ ሚዲያው በዘለለ ሁለቱንም በቅርበት አውቃቸዋለው። በጥቂቱም ይህን ይመስላሉ...
09/06/2026

💊እነዚህ ሊቃውንት ሊታሰሩ ቀርቶ፣በክፉ ዓይን ሊታዩ የሚያስፈሩ ናቸውና፣ #ፍቱልን።‼️
-----***----
ከማኅበራዊ ሚዲያው በዘለለ ሁለቱንም በቅርበት አውቃቸዋለው። በጥቂቱም ይህን ይመስላሉ።
1. #ቀሲስ ዶ/ር መዝገቡ ካሳ
የባሕር ማዶ ድሎትን ጥለው ሀገርና ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል ወደ ቅድስት ሥላሴ ዩንቨርሰቲ የመጡ የተባ ብዕርና የቀና ሰብእና ያላቸው ሰይፍ ክልኤ አፍሁ የሚባሉ አባት ናቸው። #በትረ #ሃይማኖት የተሰኘው የደለበ መጽሐፋቸውን ያየ በእውቀት ይመሰጣል።

በሥነ ምግባር ዙሪያ ያጋጠመን ትውልዳዊ ልምሾ የሚያስጨንቃቸው፣ የቤተ ክህነቱ አስተዳደራዊ ድቀት የሚያሳስባቸው ናቸው። ባልተቋረጠ ሐዋርያዊ ቅብብል (Uninterrupted Apostolic Succession ) በተገኘ ሐዋርያዊ መንበር የተሰየሙ የዘመናችን አበው የሕይዎት ጉድለት የሚያሳስባቸው ሊቅ ናቸው። ይህንን ቁጭታቸውን በቅድስት ሥላሴ ዩንቨርስቲ Patrology course ከእሳቸው የተማረን ተማሪዎቻቸው እናውቅላቸዋለን።

አሁንም በቅድስት ሥላሴ ዩነቨርስቲ መ/ር ሲሆኑ ፣ሊያሳስራቸው የሚያስገባ ወንጀል ይኖርባቸዋል ቢባል ማንም የሚያምን አይሆንም። ለቤ/ያን ስደት ማሰባቸው አልያም በኮሌጁ የውስጥ ሽኩቻ ከሆነም የታሰሩት ሚዛን አይደፋምና ፍቷቸው።አትጎዱም።

2. #መ/ር በትረ ማርያም አበባው
የጅማ ግቢ ጉባኤ ዕንቁ ፍሬ ነው። ማኅበረ ቅዱሳን የሰጠውን የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ነጻ የትምህርት መርሐ ግብር (Scholarship) ተጠቅሞ ራሱን ለዚህ የሊቅበት ማዕረግ የበቃ ትጉ ወንድም ነው።

በወቅቱ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የሰጠውን የ2ኛ ዲግሪ ት/ት ንቆ ወደ ጉባኤ ቤት የመነነ ወጣት ዓይናማ ሊቅ ነው። አሁን ላይ 4ኛውን የመጽሐፍት ትርጓሜ ት/ት እየተማረ ይገኛል። በቅርቡ የዐራቱ ጉባኤያት መ/ር ሆኖ ይመረቃል። ሊቀ ሊቃውንት ለመባልም የተገባው ሥነ ምግባር ከትጋት ጋር የታደለው ወንድም ነው።

ማኅበራዊ ሚዲያን ለበጎ ነገር የመጠቀም በኩራችን እሱ ነው። የማንም እንቶ ፈንቶ ስብስብ፣ ብጣሽ ኮርስ በገንዘብ በሚሸጥበት ዘመን ፣ እርሱ ግን ያለ ዕረፍት 24 ሰዓት በማኅበራዊ ሚዲያ ተከታታይ ኮርስ ያስተምራል። ያስተማረውንም ጽፎና ሰንዶ ለምእመናን በነጻ ያቀርባል። በቁጥር 4 አካባቢ መጽሐፍትን አሳትሟል።

1. መሠረታዊ የግዕዝ አጠናን
2. ኦርቶዶክሳዊ ተዋስኦ ቁ 1 እና 2
3. ከሌሎች ጋር ያዘጋጃቸው በተቋማት የታተሙ መጽሐፍትም አሉት።

ታዲያ ይህ ወጣት ሊቅስ ምኑ ነው በደሉ ? በቃ ምንም አታገኙበትም ። ፍቱት ። ጉባኤው አታስታጉሉበት ።

ሁለቱም ሊቃውንት ቢበደሉ፣ እንጂ ሊበድሉ አይችሉምና እባካችሁ ፍቱልን ‼️

እቅበተ ተዋሕዶ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when እቅበተ ተዋሕዶ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share