እቅበተ ተዋሕዶ

እቅበተ ተዋሕዶ ነገረ ቤተ ክርስቲያንና ኦርቶዶክሳዊ ዕይታዎች ይቀርቡበታል።

እንጃ ምን እንደሆንኩ ፣ አላውቅም ዘንድሮ፣ዶሮ ዶሮ አይሸትም ፣ የእማምዬ ጓሮ፣ጠጅ ጠጅ አይሸትም ፣ ያባብዬ ደጅ፣እንደሀገር ሰክሬ ፣ ተንገዳገድኩ እንጅ።መቆምና መውደቅ  ፣ መሔድ እስኪያቅተ...
09/09/2026

እንጃ ምን እንደሆንኩ ፣ አላውቅም ዘንድሮ፣
ዶሮ ዶሮ አይሸትም ፣ የእማምዬ ጓሮ፣
ጠጅ ጠጅ አይሸትም ፣ ያባብዬ ደጅ፣
እንደሀገር ሰክሬ ፣ ተንገዳገድኩ እንጅ።

መቆምና መውደቅ ፣ መሔድ እስኪያቅተኝ
ከእማምዬ ጓሮም
ካባብዬ ደጅም ፣ ባሩድ ነው ሚሸተኝ ።

እንጃ ምን እንደሆንኩ ፣ ምንድነው ችግሩ፣
ባሩድ ባሩድ ብቻ ፣ ሚሸተኝ ምድሩ፣
አፍንጫዬ ታሟል ፣ ወይ ታሟል ሀገሩ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ...
ላዲስ ዓመት ብስራት ፣ መድፍ ለመተኮስ፣
ሮኬት ለማፈንዳት ፣ ርችት ለመለኮስ፣
"እንዳትደነግጡ"
የሚል ሀሳብ ያለው ፣ መግለጫ ይወጣል።
የለመዱት ነገር ፣ ምን ያስደነግጣል?

በላይ በቀለ ወያ✍️

የግፉ እውነታ  #ከምናየው በላይ ነው ‼️----***-----"የአይሻ ሰኢድ የፈጠራ ድርሰት ነው ፤ ከሩዋንዳ የተቀዳ ኩረጃ ነው ፤ ሆን ተብሎ ሁለተኛ አማራ አልሆንም የሚል ትርክት ተፈጠረ.....
09/09/2026

የግፉ እውነታ #ከምናየው በላይ ነው ‼️
----***-----
"የአይሻ ሰኢድ የፈጠራ ድርሰት ነው ፤ ከሩዋንዳ የተቀዳ ኩረጃ ነው ፤ ሆን ተብሎ ሁለተኛ አማራ አልሆንም የሚል ትርክት ተፈጠረ.....ወዘተ"
እያሉ ያኔ በጨካኞች ከተጨፈጨፉት ህፃናት ይልቅ ስለ ቃሉ ይጨነቃሉ። ያን ሁሉ ግፍና ሰቆቃ በቃላት ጨዋታ ሊያጣጥሉትን የሺዎችን እልቂት " አኢሻ ያንን ብላለች አላለችም ወደሚል ጨዋታ ሊቀይሩትና ያንን ክፋት ሊያሳንሱት ይሞክራሉ።

እውነታው ግን አንድ አኢሻ ሳትሆን ብዙ አኢሻዎች አልቀዋል። ሙሉ ቤተሰብ ስንት ተጨፍጭፈዋል። ስንት ያፈሩበትንና የደከሙበትን ንብረት ትተው የተገደሉባቸው ቤተሰቦቻቼውን እንኳ ሳይቀብሩ ተሰደው ዛሬ በስደተኞች መጠለያ የሚገኙት ስንትና ስንት ናቸው!

ለምንድነው ከእውነታው ይልቅ ሜካፑ ላይ አተኩራችሁ የህዝብን እንባ የህዝብን ለቅሶ የህዝብን ያልጠገገ ቁስል በእንጨት የምትነካኩት?

አሁን ከደብረብርሃን እስከ ሰሜን ወሎ ከሞት አምልጠው የተሰደዱ በርካታ ወገኖቻችን በችግርና መከራ ውስጥ ነው ያሉት!

ግፍን አታሳንሱ!
ቢቻል ለተበደሉት ድምፅ ሁኑ ካልቻላችሁ ዝም በሉ። በህዝብ ግፍ ግን አትሳለቁ!
አኢሻ ያን አለችም አላለችም ሺህ ንፁሀን ማንነታቸው ተመርጦ አልቀዋል!

እቅበተ ተዋሕዶ

እንዴት አይነት ዘመን ላይ ደረስን ጎበዝ? ምን አይነት ድኩማኖች ናቸው መንግስታዊ ስልጣኑን የተቆጣጠሩት፣ መንግስታዊ አገልግሎት የሚሰጡ ዲፓርትመንቶች እንደ Revenue Center ተወስደው ...
09/09/2026

እንዴት አይነት ዘመን ላይ ደረስን ጎበዝ? ምን አይነት ድኩማኖች ናቸው መንግስታዊ ስልጣኑን የተቆጣጠሩት፣ መንግስታዊ አገልግሎት የሚሰጡ ዲፓርትመንቶች እንደ Revenue Center ተወስደው ስኬታቸውን በሰበሰቡት የገንዘብ መጠን እየተለካ ነው፣

ይህው የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ገቢውን በአስር እጥፋ አሳደገ ተብሎ ከበሮ እየተደለቀ ነው፣

የመንግስት ተቋማት በግል የንግድ ድርጅት መለኪያ (private business metric) የሚለኩበት ዘመን ላይ ደረስን፣

በእርግጥ የግል የንግድ ድርጅቶች ራሳቸው አፈጻጸማቸውን በትርፍ ብቻ መለካት አቁመዋል፣ "Triple Bottom Line (TBL)" የሚባል concept አለ፣ ከትርፉ በተጨማሪ ድርጅቱ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለተፈጥሮ አካባቢ ጥበቃ ያበረከተው አብሮ ይጠቀሳል፣

ካሊጉላን መንግስትን ከ .gov ወደ .com ቀይሮታል፣ ነገርየው ትርፍ ከሆነ ዘርፉን ለግል ባለሀብቶች ክፍት ቢያደርገው ደንበኞች የተሻለ ዋጋና የተቀላጠፈ አልግሎት ሊያገኙ ይችላሉ፣ የፓስፖርት ንግድ ከሞኖፖሊ ይውጣ፣

**** መንግስት በተጨማሪ ግብርና የአገልግሎት ክፍያ ተጨማሪ ገንዘብ ከገበያው ሲሰበስብ ኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ተጽኖ እንደሚፈጥር ከዚህ በፊት በስፋት ስላነሳሁት አሁን አልደግመውም፣
@ካሳ አንበሳው
እቅበተ ተዋሕዶ

 #ደብተራነት ለዶክትሬት ማዕረግ ማሟያ የሚጻፉ "የምርምር ጽሑፎችን" ገለባ የሚያደርግ ሙያ ነው።--------***-----የአመክንዮ ክርክር የራቃቸው አንዳንድ የኦሮሞ ብሔርተኞች፣ የደብተራነ...
08/09/2026

#ደብተራነት ለዶክትሬት ማዕረግ ማሟያ የሚጻፉ "የምርምር ጽሑፎችን" ገለባ የሚያደርግ ሙያ ነው።
--------***-----
የአመክንዮ ክርክር የራቃቸው አንዳንድ የኦሮሞ ብሔርተኞች፣ የደብተራነትን ታላቅነት ለማንቋሸሽ የማይፈነቅሉት የሐሰት ድንጋይ የለም። አቶ ቀጀላም አንዱ የሐሰት ትርክት ፈጣሪ ነው። ይሁን እንጂ ደብተራነት ለዶክትሬት ማዕረግ ማሟያ የሚጻፉ "የምርምር ጽሑፎችን" ገለባ የሚያደርግ ሙያ ነው። አላዋቂዎች ደብተራነትን ቢያናንቁም፣ እውነታው ግን የደብተራዎች ዕውቀት በዘመናዊው የትምህርት ሥርዓት የዶክትሬት ማዕረግ የተገኘበትን ጽሑፍ የሚሞግትና ገለባ የሚያደርግ መሆኑ ነው።

ለዚህ ማሳያ የሚሆነው፣ እውነተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቅ (Doctor of the Church) #መልአከ #ብርሃን #አድማሱ #ጀንበሬ (1885-1962 ዓ.ም.) የጻፉት "መድሎተ አሚን" የተሰኘው የዕቅበተ እምነት (Apologetics) መጽሐፍ ነው። ይህ መጽሐፍ በ1954 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ የታተመ ሲሆን፣ ካቶሊካዊው ዶ/ር አባ አየለ ተክለሃይማኖት በአግባቡ ስለማያውቋት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰነዘሩትን የነገረ ሃይማኖትና የታሪክ ስህተት ሙሉ በሙሉ ያፈረሰ ነው።

ሊቁ አድማሱ ጀንበሬ #በመጽሐፋቸው የአባ አየለን ስህተት ቃል በቃል እየጠቀሱ፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን ነገረ ክርስቶስ ትምህርት የሰጡትን ትንታኔ ያላነበባችሁት እንድታነቡት አሳስባለሁ። መጽሐፉ የሙግት ስልትና ዘዴን የምንማርበት ከመሆኑም በላይ፣ የ20ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያን ደብተራዎች በሃይማኖት ትምህርት ምን ያህል የተራቀቁ እንደነበሩ ማረጋገጫ ነው።

ከዚህ መጽሐፍ ጀርባ ያሉትን የመልአከ ብርሃን አድማሱ መምህራንን ማሰቡ ተገቢ ነው። የእኛ የአብነት ትምህርት ቤቶች ምን ያህል በሃይማኖት ትምህርት የበሰሉ ደብተራዎችን እንደሚያፈሩ እሳቸው አንዱ ትልቅ ማሳያ ናቸው።

ሊቁ አድማሱ ጀንበሬ ያበጠሩትና ስህተቱን ያረሙት የአባ አየለ "ጥናት" ለዶክትሬት ማዕረግ ማሟያ የቀረበ ነበር። ነገር ግን ምንም ዓይነት ዘመናዊ ትምህርት ሳይማሩ፣ #በዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዩኒቨርሲቲ (መካነ አእምሮ) በመጻሕፍትና በቅኔ ትምህርት ተመርቀው እዚያው ያስተማሩት ሊቁ አድማሱ ጀንበሬ የዶክተሩን የሐሰት ክምር በቀላሉ ንደውታል። ለዚህ ነው ደብተራነት ለዶክተርነት ማዕረግ ለመቀበል የተጻፈ ጽሑፍን ገለባ የሚያደርግ ሙያ ነው ሊባል የሚገባው።

አቶ #ቀጀላና መሰሎቹ የኦሮሞ ብሔርተኞች ግን ደብተራነትን በሐሰት ከማንቋሸሽ ባለፈ፣ ደብተራዎች የጻፉትን መጽሐፍ አንብበው የሚረዱበት አቅም ያላቸው አይመስለኝም።

ደብተራነት ይለምልም። ደብተራዎች ገና ያብባሉ።
Yosef Fisha
እቅበተ ተዋሕዶ

 #እኛ  #ደብተራዎች ነን ‼️---**---ምድረ ገመድ አፍ ደብተራን የመተቸት ሞራላዊም ፣ሥነ ልቦናዊም ሰብአዊም አቅም የለውም። ፊደል ያላጠኑ ፣ የፊደልን ሰዋሰዋዊ እና ፎክለራዊ ትርጉም የ...
07/09/2026

#እኛ #ደብተራዎች ነን ‼️
---**---
ምድረ ገመድ አፍ ደብተራን የመተቸት ሞራላዊም ፣ሥነ ልቦናዊም ሰብአዊም አቅም የለውም።
ፊደል ያላጠኑ ፣ የፊደልን ሰዋሰዋዊ እና ፎክለራዊ ትርጉም የማያወቁ ፣ ፊደል ይቀነስ ይሉ የነበሩ የዘመናችን ደናቁርት ናቸው እኮ ሀገር እያጠፉ ያሉት። አሁን የሚጮሁት የዕውቀት አክፍሎተኞችም እነዚህ ተረፈ ናዚ ናቸው።

#ደብተራዎች ባስተማሩት የግዕዝ ቋንቋ ውሉድ በሆነው አማርኛ ቋንቋ እየተግባባና እያወራ፣ ደብተራን የሚተች ድንዙዝ ፍጥረት እኮ ነው የገጠመን ። ደብተራነትን ከጠላህ ለምን የደብተራ ፍጡር የሆነውን ቋንቋ ትጠቀማለህ። ለምን በዛው በላኩህ አውሮፓዊያን ቋንቋ አትንተባተብም ነበር ።

#ደብተራነት ልዕለ ሊቃውንትነት ነው። #ደብተራነት ጥንቅቅ ያለ ሰይፍ ክልኤ አፉነት ነው። ደብተራነት የሰብአዊነትን ክብር እና የሞራል ከፍታን ያጎናጸፈን ክብራችን ነው።
ደብተራነት የምሁርነት ጣሪያን አርቀን እንድንሰቅለው ያደረገን ማንነታችን ነው።

ደብራነት ሀገርን መውደድ ነው። ደብተራነት ዓለም አቀፍና ሀገራዊ እውቀትን ያጣመርንበት ከሰው አልፎ ከመላዕክት ጋር ተግባብቶ የመኖር ጥበብ ነው። እኛም የደብተራው የጋሞው ሊቅ የአባ ባሕርይ የግብር ልጆች ነን።

#ደብተራነት #ይለምልም።
#ደብተራነት #ያብብ።
#ደብተራነት #ይፋፋም።
እቅበተ ተዋሕዶ

07/09/2026

አዲሱ ዓመት የማይቀይረው ነገር ቢኖር፣ የሥርዓቱን ኦርቶዶክስ ጠልነት ነው። ጥያቄው በአዲሱ ዓመትም የሚፈጸምብን መዋቅራዊ ጥቃት በደነዘዘ ማንነታችን ታጅቦ ይቀጥላል ወይስ ራሳችንን ለማትረፍ እንሠራለን ?

የኢትዮጵያ  #ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ» የተሰኘው  #መጽሐፍ በደኅንነት አባላት ተሰበሰበ‼️----***-----ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት...
05/09/2026

የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ» የተሰኘው #መጽሐፍ በደኅንነት አባላት ተሰበሰበ‼️
----***-----
ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ «የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ» የተሰኘው መጽሐፌ ማከፋፈያ ድርጅት በበርካታ የደኅንነት አባላት ከተከበበ በኋላ፣ በመጋዘን ውስጥ የነበሩ መጻሕፍት ተሰብስበው መወሰዳቸውንና ደንበኞችን በማስተናገድ ላይ የነበረ ሠራተኛ «ለጥያቄ ትፈለጋለህ» በሚል መወሰዱን የመጽሐፉ ደራሲ ቀሲስ ዶ/ር መንግስቱ ጎበዜ በይፋዊ ማህበራዊ ገጻቸው ተናገሩ።

መጽሐፉ #ቤተ ክርስቲያንን እና ተያያዥ የሀገራችንን ታሪክ ብቻ መሠረት ያደረገ ሙያዊ ሥራ በመሆኑ ለምን በዚህ ደረጃ የመንግሥትን ትኩረት እንደሳበ እንዳስገረማቸው ተናግረዋል።

መጽሐፉ ከኢትዮጵያ የአእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን (ጉዳዩ ከሚመለከተው ከፍተኛ የመንግሥት መሥሪያ ቤት) ፈቃድ አግኝቶ የታተመ መሆኑን የተናገሩት ቀሲስ ዶ/ር መንግስቱ የፈቃዱ የምስክር ወረቀትም አብሮ ስለታተመ ከመጽሐፉ የመጨረሻ ገጽ ላይ ማዬት እንደሚቻል አረጋግጠዋል።

የመናገርና ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ ሕገመንግስታዊ መብትን የጣሰ በመሆኑ መጽሐፉንም የተያዙት ሠራተኛ እንዲለቀቁ እጠይቃለሁ።

 #ሰውነት  #ይቀድማል‼️ ***የእኒህ ዋርካ የሆኑ አባት፣ የሕይዎት ታሪክ በዚህ መልክ መሰናዳቱን ዲ/ን ዶ/ር አረጋ አባተ ሹክ ብሎናል። ታሪካቸውን የጻፈው ሰው፡ እጁ ይለምልም። ሕሊናውን ...
02/09/2026

#ሰውነት #ይቀድማል‼️
***
የእኒህ ዋርካ የሆኑ አባት፣ የሕይዎት ታሪክ በዚህ መልክ መሰናዳቱን ዲ/ን ዶ/ር አረጋ አባተ ሹክ ብሎናል። ታሪካቸውን የጻፈው ሰው፡ እጁ ይለምልም። ሕሊናውን ያርታለት። ልቦናውን ያቅናለት።

ለገበያ ሲውል ንገሩን። በገፍ እየገዛን ሁሉም ሰው እንዲያነበው እናረጋለን። ውብአህያዎች እዛው ከአዲሱ አራጅ ቡድናችሁ ጋር ተንጫጩ። ገዳዮችን አወዳድሱ።

02/09/2026

ቤተ ክህነት እኮ፣ በ2006 ዓ.ም ባለሙያዎች በስንት ድካም ሠርተን የሰጠነውን የለውጥ ሰነዶች አቃጥሎ ያጠፋ ባርባሪክ የሆኑ ሌቦች ያሉበት ነው። የቅርቡ የ10 ዓመት መሪ እቅድስ የት ገባ ? 😂

02/09/2026

ጉልቻ ቢቀየር ወጥ አያጣፍጥም። የቤተ ክህነት ችግር የሚፈታው ሥርዓታዊ ለውጥ በማድረግ ብቻ ነው።
Organizational change always relay on Systemic thought.

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when እቅበተ ተዋሕዶ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share