EOTC UKI Diocese Office

EOTC UKI Diocese Office The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church is the largest of the Oriental Orthodox Churches.

12/04/2026
የሐዘን መግለጫ ለክብር መምህር ዘለዓለም (ከከተማ እስከ ገጠር ወንጌልን ያስተማሩ)---"ሄዱም ወደ ዓለም ሁሉ ተጉዛችሁ ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ" (ማርቆስ 16:15)የክቡር መምህር ዘለ...
08/03/2026

የሐዘን መግለጫ ለክብር መምህር ዘለዓለም (ከከተማ እስከ ገጠር ወንጌልን ያስተማሩ)

---

"ሄዱም ወደ ዓለም ሁሉ ተጉዛችሁ ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ" (ማርቆስ 16:15)

የክቡር መምህር ዘለዓለም ወንድሙን ሞት ስንሰማ ልባችን በከፍተኛ ሐዘን ተሞልቷል። መምህር ዘለዓለም ከከተማ እስከ ገጠር ድረስ የወንጌልን ብርሃን በማስተላለፍ ዘመናቸውን ያሳለፉ ታላቅ አገልጋይ ነበሩ። በከተማም በገጠርም በማይለይ ፍቅር፣ በትህትናና በቅንነት የእግዚአብሔርን ቃል ሲያስተምሩ የኖሩ አርአያ ናቸው።

"እንግዲህ ወደ አሕዛብ ሁሉ ሂዱና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስም ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው" (ማቴዎስ 28:19-20)

መምህር ዘለዓለም ይህንን ትእዛዝ በሕይወታቸው ሁሉ በታማኝነት ተግባራዊ ያደረጉ አገልጋይ ነበሩ። በከተማው ቤተክርስቲያን ብቻ ሳይወሰኑ፣ ወደ ሩቅ ገጠራማ አካባቢዎች በመጓዝ፣ በተራራማ መንገድ፣ በውሃና በደረቅ በመጓዝ የወንጌልን ብስራት ለማዳረስ አልደከሙም። በርካታ ነፍሳት በትምህርታቸው ወደ እግዚአብሔር ቀርበዋል፤ ብዙዎች በምክራቸው ተመርተዋል፤ በርካታ ደቀ መዛሙርትን በማፍራት የወንጌል ዘርን በሰፊው ዘርተዋል።

"እነሆም፥ እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ" (ማቴዎስ 28:20)

ይህ የጌታ ተስፋ ዛሬም እውን ነው። ምንም እንኳ መምህር ዘለዓለም በአካል ከእኛ ቢለዩም፣ በልባችንና በትውስታችን ውስጥ ግን ሁልጊዜ ከእኛ ጋር ናቸው። ያስተማሩን ትምህርት፣ ያሳዩን አርአያ፣ ያሳለፉን ምክር ሁሉ በሕይወታችን መሪ ኮከብ ሆኖ ይኖራል።

"ከሞት ወደ ሕይወት አልፈናል እንድንሆን እናውቃለን፤ ምክንያቱም ወንድሞችን እንወዳለን" (1ኛ ዮሐንስ 3:14)

መምህር ዘለዓለም በሕይወት ዘመናቸው ይህንን ፍቅር በተግባር አሳይተዋል። ከከተማ እስከ ገጠር ያለውን ሁሉ በእኩል ፍቅር ያስተማሩ፣ የድሆችና የተጨቆኑ ደጋፊ፣ የተስፋ ቆራጦች አበረታች፣ የተጠማውን የእግዚአብሔር ቃል ውሃ የሚያጠጣ መምህር ነበሩ።

በዚህ የሐዘን ሰዓት፣ ወደ እርሱ ዘንድ በመቅረብ መጽናናትን እናገኛለን፦

"ንጹሐን ልብ ያላቸው ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያያሉና" (ማቴዎስ 5:8)

መምህር ዘለዓለም ንጹሕ ልብ ይዘው ጌታን ማገልገላቸውን እናውቃለን፤ አሁንም በሰማያዊት መንግሥት ጌታን ፊት ለፊት እያዩ ዕረፍትን አግኝተዋል። በምድር ላይ በትጋት የዘሩት የወንጌል ዘር እስከ መጨረሻው ትውልድ ድረስ ፍሬ ያፈራል።

ለቤተሰቦች፣ ለዘመዶች፣ ለደቀ መዛሙርትና ለምእመናን ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን፦
የዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት

የዩናይትድ ኪንግደምና  አየርላንድ ሀገረ ስብከት በምስራቅ አርሲ ዞን ባሉ ወረዳዎች በግፍ ለተገደሉት 25 ኦርቶዶክሳውያን የተሰጠ የኀዘን መግለጫ።
02/11/2025

የዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ ሀገረ ስብከት በምስራቅ አርሲ ዞን ባሉ ወረዳዎች በግፍ ለተገደሉት 25 ኦርቶዶክሳውያን የተሰጠ የኀዘን መግለጫ።

የብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የሩቅ ምሥራቅ፣ እንግሊዝ፣ አየርላንድና አካባቢው ሀገራት አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የ 2018 ዓ.ም ዘመነ ማርቆስ ቡራኬና መልእክት። ✝️+++በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ...
10/09/2025

የብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የሩቅ ምሥራቅ፣ እንግሊዝ፣ አየርላንድና አካባቢው ሀገራት አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የ 2018 ዓ.ም ዘመነ ማርቆስ ቡራኬና መልእክት። ✝️
+++
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !

ውድ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ከሁሉ አስቀድመን ምድራችንን በልምላሜንና በፍጹም በረከት እያደሰ ዘመንን በዘመን እየተካ ጸጋውን ያበዛልን እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከሁለት ሺሕ አስራ ሰባት ዓመተ ምሕረት ዘመነ ቅዱስ ማቴዎስ ወደ ሁለት ሺሕ ዐሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ዘመነ ቅዱስ ማርቆስ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ !
+++
"ልበ ንጹሐ ፍጥር ሊተ እግዚኦ ፣ ወመንፈሰ ርቱዐ ሐድስ ውስተ ከርሥየ። አቤቱ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፡ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።"
መዝ 50(51) ፥10
++
በክርስቶስ የተወደዳችሁ ልጆቻችን፣

በእግዚአብሔር ምሕረትና ቸርነት ወደዚህ አዲስ ዓመት ስንሻገር፣ እውነተኛ ለውጥ የሚጀምረው ከውጫዊ ምድራዊ ሁኔታዎች ሳይሆን ከእያንዳንዳችን ልብ መሆኑን ማስታወስ ይገባናል። አባታችን ልዑል እግዚአብሔር በቅዱስ ቃሉ “አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ፣ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ” (ሕዝቅኤል 36:26) በማለት ትክክለኛና ዘላቂ የሆነ ለውጥ የሰው ነፍስ ለእግዚአብሔር መለኮታዊ ትዕዛዝ፣ ሀሳብና ፈቃድ ሲታዘዝና ከጨለማ ወደ ብርሃን ሲመለስ የሚገኝ የእግዚአብሔር ስጦታ መሆኑ አስገንዝቦናል።
++
የሕይወታችን፣ የቤተሰቦቻችንና የሀገራችን ትልቁ ጥንካሬ የሚመነጨው በእግዚአብሔር ጸጋ ከተለወጠ ልብ ነው። ያልተለወጠ ልብ ጥላቻን፣ ስግብግብነትንና መለያየትን ሲወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ልብ ግን የሕይወት ምንጭ ይሆናል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣ እምነት፣ የዋህነት፣ ራስን መግዛት ነው” (ገላቲያ 5፡22–23) በማለት ይመሰክራል።
ስለዚህ፣ ወንጌል መጀመሪያ ሌሎችን እንድንኮንን ሳይሆን፣ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን እንዲሠራ እንድንፈቅድ ይጠራናል። ራሳችንን እንድንመረምር፣ ከልብ ክፋትን ትተን ንስሐ እንድንገባ እና የእግዚአብሔር ሕያው ቤተ መቅደስ እንድንሆን ያሳስበናል። መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ሲኖርት፣ ውድመት ለፈውስ፣ ራስ ወዳድነት ለጋስነት፣ መለያየት ለአንድነት፣ እና ተስፋ መቁረጥ ለተስፋ ቦታቸውን ይለቅቃሉ። እንዲህ ያሉት ልቦች ቤተሰባችንን፣ ማኅበረሰባችንን እና በመጨረሻም የተወደደችውን ሀገራችንን ይለውጣሉ።
++
እኛ ኢትዮጵያውያንም ታሪካችን በብዙ ፈተናዎች ውስጥ የክርስቶስን ብርሃን በተሸከሙና ቤተክርስቲያናችንንና ሀገራችንን ባስጌጡ ቅዱሳን የከበረ ነው። ዛሬም ያ መንፈስ በእኛ ውስጥ ሕያው ነው። ልባችን በትሕትና፣ በአንድነትና በፍቅር ሲመራ፣ ሀገራችንም ብሎም ዓለማችን ያብባሉ። ሁለንተናዊ ለውጥ የሚመጣው እያንዳንዳችን በእግዚአብሔር ፊት በጽድቅ፣ በትህትናና በፍቅር ለመኖር ኃላፊነት ስንወስድና ስለ ኃጢአታችን ንስሐ ስንገባ ብቻ ነው።
++
ሀገራዊ መታደስ ሩቅ ሕልም ሳይሆን እያንዳንዳችን ለእግዚአብሔር የሰላም፣ የጽድቅና የፍቅር መሣሪያ እንድንሆን ራሳችንን ስንሰጥ፣ እውን የሚሆን ሕያው ተስፋ ነው።
ስለዚህ፣ የተወደዳችሁ ልጆቼ፣ አዲስ ዓመትን ስንጀምር ለውጥን ከውጪ መፈለግን አቁመን ይልቁንም በመጀመሪያ በጸሎት፣ በጾም፣ በይቅርታና በመታረቅ እንፈልገው። የእያንዳንዳችን ልብ የሰላም መሠዊያ ከሆነ፣ ቤተሰቦቻችን ይፈወሳሉ፣ ቤተሰቦቻችን ከተፈወሱ፣ ማኅበረሰባችን ይፈወሳል። ማኅበረሰባችን ከተፈወሰ ደግሞ የተወደደች ሀገራችን ኢትዮጵያም ብሎም ዓለማችን ይፈወሳሉ።
++
ሁሉን ነገር አዲስ የሚያደርግ (ራእይ 21:5) ጌታ በዚህ ዓመት አዲስ መንፈስን ይስጠን።
++
✝️ የአብ በረከት፣ የወልድ ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስም ኃይል በዚህ አዲስ ዓመት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።
+++
አባ ያዕቆብ ሊቀጳጳስ

+++
✝️ In the Name of the Father, and of the Son, and of the Holy Spirit, One God. Amen.

To my beloved Children in Jesus Christ,
Peace and blessing be unto you from God the Father, grace be unto you from His Only-Begotten Son, and sanctification be unto you from the Holy Spirit, who renews all creation and makes all things new. Amen.

Beloved children, first and foremost, I greet you with the apostolic blessing of our holy Church: “Peace be to you all.” May the Lord, who renews the face of the earth and sustains all by His providence, grant that you joyfully pass from the year 2017 E.C. into the year 2018 E.C. in health, peace, and spiritual prosperity.

“Create in me a pure heart, O God, and renew a steadfast spirit within me.”
(Psalm 51:10)

As we cross into this new year through the mercy and kindness of our Lord, we must remember that true transformation does not begin with external change, but within the heart. The Lord promises through His prophet: “I will give you a new heart and put a new spirit in you” (Ezekiel 36:26). This renewal is not the work of human will alone, but a gift of divine grace received when we obey His commandments, renounce sin, and walk in His light.

The strength of our lives, our families, and our nation is rooted in hearts renewed by God. An unchanged heart breeds hatred, greed, and division, but a heart filled with the Holy Spirit becomes a fountain of life and blessing. The Apostle Paul testifies: “The fruit of the Spirit is love, joy, peace, forbearance, kindness, goodness, faithfulness, gentleness, and self-control” (Galatians 5:22-23).

Therefore, the Gospel calls us not first to condemn others, but to allow the Spirit to work within us—to examine our lives, repent of our sins, and become temples of the living God. Where the Spirit dwells, destruction gives way to healing, selfishness to generosity, division to unity, and despair to hope. Renewed hearts bring renewal to our families, to our communities, and to our beloved Ethiopia.
Our history is sanctified by the witness of holy fathers, mothers, martyrs, and saints who, through many trials, bore the light of Christ and adorned both the Church and our country. Today, that same Spirit is entrusted to us. When we live in humility, unity, and love, our Church flourishes and our nation is lifted. National renewal is not a distant hope, but a living reality when each one of us offers ourselves as an instrument of God’s peace, love, and righteousness.
++
Therefore, my beloved children in Jesus Christ, as we begin this new year, let us not seek change merely from the outside, but within our own souls—through prayer, fasting, forgiveness, repentance, and reconciliation. If every heart becomes an altar of peace, our families will be healed; if our families are healed, our communities will be strengthened; if our communities are strengthened, Ethiopia—and indeed, the world—will be renewed.
May the Lord, who declares, “Behold, I make all things new” (Revelation 21:5), grant each of you a renewed spirit in this blessed year of grace.

✝️ Through the prayers of our Lady the Theotokos, St. Mary, and the intercessions of all the saints who have shone forth in Ethiopia and throughout the world, may Christ our true God bless this year, grant you health, peace, and spiritual joy, and make you steadfast in His love—now and always, and unto the ages of ages. Amen.

Yours in Christ,

+ Abba Yacob, Archbishop

03/05/2025

በዛሬው ዕለት በሚድልስቦሮ ደብረ ጸሐይ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ፣ የሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ድምቀት ተከብሯል። እግዚአብሔር የተመሠገነ ይሁን።

03/05/2025

የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ በዓል፣ በሚድልስቦሮ ደብረ ጸሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ።

ብፁዕ አባ ያዕቆብ የሩቅ ምሥራቅ፣ ዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰላም አምባሳደር በዓለ ትንሣኤን አስመልክተው በአህጉረ ስብከታቸው ለሚገኙ ሊቃወንተ ቤተክርስቲ...
20/04/2025

ብፁዕ አባ ያዕቆብ የሩቅ ምሥራቅ፣ ዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰላም አምባሳደር በዓለ ትንሣኤን አስመልክተው በአህጉረ ስብከታቸው ለሚገኙ ሊቃወንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት፣ ዲያቆናት፣ ዘማርያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ ምዕመናንና ምዕመናት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ብፁዕ አባ ያዕቆብ የሩቅ ምሥራቅ፣ የዩናይትድ ኪንግደምና አየር ክንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በጃፓን ቅዱስ ሚካኤል በመገኘት የስቅለት በዓል ተከብሯል።የብፁዕነታቸው ቡራኬያቸው ...
18/04/2025

ብፁዕ አባ ያዕቆብ የሩቅ ምሥራቅ፣ የዩናይትድ ኪንግደምና አየር ክንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በጃፓን ቅዱስ ሚካኤል በመገኘት የስቅለት በዓል ተከብሯል።
የብፁዕነታቸው ቡራኬያቸው ይድረሰን።

 #ዓርብ “የስቅለት ዓርብ” ይባላል ምክንያቱም እንዲህ ነው ተብሎ ሊነገር በማይቻል ፍቅር የወደደን በደሙም የዋጀን ጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ...
18/04/2025

#ዓርብ “የስቅለት ዓርብ” ይባላል ምክንያቱም እንዲህ ነው ተብሎ ሊነገር በማይቻል ፍቅር የወደደን በደሙም የዋጀን ጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ መዋሉን ለማስታወስ ነው (ማቴ ፳፯፡፴፭)።

ይህ እለት “መልካሙ ዓርብ” ተብሎም ይጠራል። ይህም የሆነበትን ምክንያት ስንመለከት ከስቅለተ ክርስቶስ በፊት አንድ ሰው ሲያጠፋ በመስቀል ተሰቅሎ እንዲሞት ይደረግ ነበር፤ በሮማውያን ሕግም መስቀል የወንጀለኞች መቅጫ ምልክት ነበር። በዕለተ ዓርብ ግን የወንጀለኞች መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል ጌታችን በደሙ ቀድሶ የምሕረት ምልክት፣ የሕይወት ዓርማ፣ የዲያብሎስ ድል መንሻ ስላደረገው፣ በክቡር ሞቱ መልካሙን ሕይወት ለእኛ በቸርነቱ እና በምሕረቱ ስላደለን “መልካሙ ዓርብ” ተብሏል።
ይህን ታላቅ ዕለት በዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ ሀገረ ስብከት የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት በታላቅ ድምቀት በጸሎት፣ በመዝሙር፣ በሰጊድ አክብረውት ውለዋል።

█►             𝗣𝗔𝗦𝗦𝗜𝗢𝗡  𝗪𝗘𝗘𝗞  𝗥𝗜𝗧𝗘𝗦          ◄█𝗣𝗥𝗔𝗬𝗘𝗥 𝗔𝗡𝗗 𝗣𝗥𝗢𝗦𝗧𝗥𝗔𝗧𝗜𝗢𝗡 𝗢𝗡 𝗚𝗢𝗢𝗗 𝗙𝗥𝗜𝗗𝗔𝗬       ✞  ሥርዐተ ጸሎት ወስግደት ዘዓርብ (ስቅለት)...
18/04/2025

█► 𝗣𝗔𝗦𝗦𝗜𝗢𝗡 𝗪𝗘𝗘𝗞 𝗥𝗜𝗧𝗘𝗦 ◄█
𝗣𝗥𝗔𝗬𝗘𝗥 𝗔𝗡𝗗 𝗣𝗥𝗢𝗦𝗧𝗥𝗔𝗧𝗜𝗢𝗡 𝗢𝗡 𝗚𝗢𝗢𝗗 𝗙𝗥𝗜𝗗𝗔𝗬
✞ ሥርዐተ ጸሎት ወስግደት ዘዓርብ (ስቅለት) ✞
✞ ▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬ ✞

ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ ለዓለም ዓለም።
𝗙𝗼𝗿 𝗧𝗵𝗶𝗻𝗲 𝗶𝘀 𝘁𝗵𝗲 𝗣𝗼𝘄𝗲𝗿, 𝘁𝗵𝗲 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆, 𝘁𝗵𝗲 𝗕𝗹𝗲𝘀𝘀𝗶𝗻𝗴, 𝗮𝗻𝗱 𝘁𝗵𝗲 𝗠𝗮𝗷𝗲𝘀𝘁𝘆, 𝗳𝗼𝗿𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿.
ኃይል ክብር ጌትነት ገዥነት ለዘላለሙ ለአንተ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ዐማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ ለዓለም ዓለም።
𝙀𝙢𝙢𝙖𝙣𝙪𝙚𝙡 𝙢𝙮 𝙂𝙤𝙙, 𝗙𝗼𝗿 𝗧𝗵𝗶𝗻𝗲 𝗶𝘀 𝘁𝗵𝗲 𝗣𝗼𝘄𝗲𝗿, 𝘁𝗵𝗲 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆, 𝘁𝗵𝗲 𝗕𝗹𝗲𝘀𝘀𝗶𝗻𝗴, 𝗮𝗻𝗱 𝘁𝗵𝗲 𝗠𝗮𝗷𝗲𝘀𝘁𝘆, 𝗳𝗼𝗿𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿.
ፈጣሪዬ ዐማኑኤል ሆይ ኃይል ክብር ጌትነት ገዥነት ለዘላለሙ ለአንተ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ ለዓለም ዓለም።
𝙊 𝙈𝙮 𝙇𝙤𝙧𝙙 𝙅𝙚𝙨𝙪𝙨 𝘾𝙝𝙧𝙞𝙨𝙩, 𝗙𝗼𝗿 𝗧𝗵𝗶𝗻𝗲 𝗶𝘀 𝘁𝗵𝗲 𝗣𝗼𝘄𝗲𝗿, 𝘁𝗵𝗲 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆, 𝘁𝗵𝗲 𝗕𝗹𝗲𝘀𝘀𝗶𝗻𝗴, 𝗮𝗻𝗱 𝘁𝗵𝗲 𝗠𝗮𝗷𝗲𝘀𝘁𝘆, 𝗳𝗼𝗿𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿.
ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ኃይል ክብር ጌትነት ገዥነት ለዘላለሙ ለአንተ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ኃይልየ ወፀወንየ ዉእቱ እግዚእየ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል ወአኮቴት
አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ
𝗧𝗵𝗲 𝗟𝗼𝗿𝗱 𝗶𝘀 𝗺𝘆 𝗽𝗼𝘄𝗲𝗿, 𝘀𝘁𝗿𝗲𝗻𝗴𝘁𝗵 𝗮𝗻𝗱 𝘀𝗵𝗲𝗹𝘁𝗲𝗿; 𝗳𝗼𝗿 𝘆𝗼𝘂 𝗯𝗲𝗰𝗮𝗺𝗲 𝗺𝘆 𝗛𝗼𝗹𝘆 𝗦𝗮𝗹𝘃𝗮𝘁𝗶𝗼𝗻, 𝗜 𝘀𝗮𝘆 𝘄𝗶𝘁𝗵 𝘁𝗵𝗮𝗻𝗸𝘀- 𝗴𝗶𝘃𝗶𝗻𝗴 𝗟𝗼𝗿𝗱’𝘀 𝗽𝗿𝗮𝘆𝗲𝗿: 𝗢𝘂𝗿 𝗙𝗮𝘁𝗵𝗲r
ኃይሌና አምባ መጠጊያዬ ጌታዬ ነህ ረዳት ሁነኸኛልና በምሥጋና
እንዲህ እላለሁ : በሰማያት ያለህ አባታችን ሆይ ስምህ ይመስገን
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

አቡነ ዘበሰማያት / አባታችን ሆይ / 𝙊𝙪𝙧 𝙁𝙖𝙩𝙝𝙚𝙧

አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ትምጻእ መንግሥትከ ወይኩን ፈቃደከ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር ሲሳየነ ዘለለ ዕለትነ ሀበነ ዮም ንኅድግ ለዘአበሰለነ ወጌጋየነ ከመ ንሕነኒ ንኅድግ ለዘአበሰለነ ኢታብአነ እግዚኦ ውስተ መንሱት አላ አድኅነነ ወባልሐነ እምኵሉ እኩይ እሰመ ዚአከ ይእቲ መንግሥት ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም አሜን

𝙊𝙪𝙧 𝙁𝙖𝙩𝙝𝙚𝙧 𝙬𝙝𝙤 𝙖𝙧𝙩 𝙞𝙣 𝙃𝙚𝙖𝙫𝙚𝙣 , 𝙃𝙖𝙡𝙡𝙤𝙬𝙚𝙙 𝙗𝙚 𝙩𝙝𝙮 𝙣𝙖𝙢𝙚. 𝙏𝙝𝙮 𝙆𝙞𝙣𝙜𝙙𝙤𝙢 𝙘𝙤𝙢𝙚 . 𝙏𝙝𝙮 𝙬𝙞𝙡𝙡 𝙗𝙚 𝙙𝙤𝙣𝙚 𝙊𝙣 𝙀𝙖𝙧𝙩𝙝 𝙖𝙨 𝙞𝙩 𝙞𝙨 𝙞𝙣 𝙃𝙚𝙖𝙫𝙚𝙣 . 𝙂𝙞𝙫𝙚 𝙪𝙨 𝙩𝙝𝙞𝙨 𝙙𝙖𝙮 𝙤𝙪𝙧 𝙙𝙖𝙞𝙡𝙮 𝙗𝙧𝙚𝙖𝙙 𝘼𝙣𝙙 𝙛𝙤𝙧𝙜𝙞𝙫𝙚 𝙪𝙨 𝙤𝙪𝙧 𝙩𝙧𝙚𝙨𝙥𝙖𝙨𝙨𝙚𝙨 𝘼𝙨 𝙬𝙚 𝙛𝙤𝙧𝙜𝙞𝙫𝙚 𝙩𝙝𝙤𝙨𝙚 𝙬𝙝𝙤 𝙩𝙧𝙚𝙨𝙥𝙖𝙨𝙨 𝙖𝙜𝙖𝙞𝙣𝙨𝙩 𝙪𝙨 𝘼𝙣𝙙 𝙡𝙚𝙖𝙙 𝙪𝙨 𝙣𝙤𝙩 𝙞𝙣 𝙩𝙤 𝙩𝙚𝙢𝙥𝙩𝙖𝙩𝙞𝙤𝙣 𝘽𝙪𝙩 𝙙𝙚𝙡𝙞𝙫𝙚𝙧 𝙪𝙨 𝙛𝙧𝙤𝙢 𝙚𝙫𝙞𝙡 𝙤𝙣𝙚 𝙞𝙣 𝘾𝙝𝙧𝙞𝙨𝙩 𝙅𝙚𝙨𝙪𝙨 𝙊𝙪𝙧 𝙇𝙤𝙧𝙙 . 𝙁𝙤𝙧 𝙩𝙝𝙞𝙣𝙚 𝙞𝙨 𝙩𝙝𝙚 𝙆𝙞𝙣𝙜𝙙𝙤𝙢 𝙏𝙝𝙚 𝙋𝙤𝙬𝙚𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙩𝙝𝙚 𝙂𝙡𝙤𝙧𝙮 𝙁𝙤𝙧𝙚𝙫𝙚𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙚𝙫𝙚𝙧. 𝘼𝙢𝙚𝙣 .
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለአምላክ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝗛𝗼𝗻𝗼𝘂𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆 𝗯𝗲 𝘁𝗼 𝗚𝗼𝗱 𝗳𝗼𝗿𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿.
ለአምላክነቱ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለሥሉስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝗛𝗼𝗻𝗼𝘂𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆 𝗯𝗲 𝘁𝗼 𝘁𝗵𝗲 𝗛𝗼𝗹𝘆 𝗧𝗿𝗶𝗻𝗶𝘁𝘆 𝗳𝗼𝗿𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿
ለሦስትነቱ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለማሕየዊ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝙃𝙤𝙣𝙤𝙪𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙂𝙡𝙤𝙧𝙮 𝙗𝙚 𝙩𝙤 𝙩𝙝𝙚 𝙇𝙞𝙛𝙚 𝙜𝙞𝙫𝙚𝙧 𝙛𝙤𝙧𝙚𝙫𝙚𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙚𝙫𝙚𝙧.
ለአዳኝነቱ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለእዘዙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝗛𝗼𝗻𝗼𝘂𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆 𝗯𝗲 𝘁𝗼 𝗛𝗶𝘀 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆 𝗳𝗼𝗿 𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿
ለጌትነቱ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለመንግሥቱ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝙃𝙤𝙣𝙤𝙪𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙂𝙡𝙤𝙧𝙮 𝙗𝙚 𝙩𝙤 𝙃𝙞𝙨 𝙆𝙞𝙣𝙜𝙙𝙤𝙢 𝙛𝙤𝙧𝙚𝙫𝙚𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙚𝙫𝙚𝙧.
ለመንግሥቱ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለዕበዩ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝙃𝙤𝙣𝙤𝙪𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙂𝙡𝙤𝙧𝙮 𝙗𝙚 𝙩𝙤 𝙃𝙞𝙨 𝙈𝙖𝙟𝙚𝙨𝙩𝙮 𝙛𝙤𝙧𝙚𝙫𝙚𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙚𝙫𝙚𝙧.
ለገናናነቱ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለሥልጣኑ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝗛𝗼𝗻𝗼𝘂𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆 𝗯𝗲 𝘁𝗼 𝗛𝗶𝘀 𝗣𝗼𝘄𝗲𝗿 𝗳𝗼 𝗿𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿.
ለሥልጣኑ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለምኲናኑ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝙃𝙤𝙣𝙤𝙪𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙂𝙡𝙤𝙧𝙮 𝙗𝙚 𝙩𝙤 𝙃𝙞𝙨 𝘼𝙪𝙩𝙝𝙤𝙧𝙞𝙩𝙮 𝙛𝙤𝙧𝙚𝙫𝙚𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙚𝙫𝙚𝙧.
ለፈራጅነቱ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለኢየሱስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝙃𝙤𝙣𝙤𝙪𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙂𝙡𝙤𝙧𝙮 𝙗𝙚 𝙩𝙤 𝙅𝙚𝙨𝙪𝙨 𝙛𝙤𝙧𝙚𝙫𝙚𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙚𝙫𝙚𝙧.
ለኢየሱስ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁🍁----------------- ✞

ለክርስቶስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝗛𝗼𝗻𝗼𝘂𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆 𝗯𝗲 𝘁𝗼 𝗖𝗵𝗿𝗶𝘀𝘁 𝗳𝗼𝗿𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿
ለክርስቶስ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለሕማሙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝗛𝗼𝗻𝗼𝘂𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆 𝗯𝗲 𝘁𝗼 𝗛𝗶𝘀 𝗦𝘂𝗳𝗳𝗲𝗿𝗶𝗻𝗴 𝗳𝗼𝗿𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿
ለመከራው ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለመስቀሉ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም።
𝙃𝙤𝙣𝙤𝙪𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙂𝙡𝙤𝙧𝙮 𝙗𝙚 𝙩𝙤 𝙃𝙞𝙨 𝘾𝙧𝙤𝙨𝙨 𝙛𝙤𝙧𝙚𝙫𝙚𝙧 𝙖𝙣𝙙 𝙚𝙫𝙚𝙧
ለመስቀሉ ክብር ምስጋና ጌትነት ለዘላለሙ ይገባል።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

ለከ ይደሉ ኃይል ለከ ይደሉ ስብሐት ወለከ ይደሉ አኮቴት
ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም።
𝗣𝗼𝘄𝗲𝗿, 𝗚𝗹𝗼𝗿𝘆 𝗮𝗻𝗱 𝗯𝗹𝗲𝘀𝘀𝗶𝗻𝗴 𝗯𝗲 𝘁𝗼 𝗺𝘆 𝗟𝗼𝗿𝗱 𝗝𝗲𝘀𝘂𝘀 𝗖𝗵𝗿𝗶𝘀𝘁 𝗳𝗼𝗿𝗲𝘃𝗲𝗿 𝗮𝗻𝗱 𝗲𝘃𝗲𝗿.
ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለአንተ ከሀሊነት ይገባሃል
ለአንተ ክብር ይገባሃል ለአንተ ምስጋና ይገባሃል ለዘላለሙ።
✞ ----------------🍁🍁🍁----------------- ✞

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምድረ ቻይና የመጀመሪያዋን ደብር በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ አከናወነች።የሩቅ ምሥራቅ፣ የዩናይትድ ኪንግደምና  አየርላንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳ...
08/12/2024

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምድረ ቻይና የመጀመሪያዋን ደብር በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ አከናወነች።

የሩቅ ምሥራቅ፣ የዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በቻይና የመጀመርያዋን ቤተ ክርስቲያን ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ብለው በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ በመፈጸም ምእምናንን አቁርበዋል።

በዕለቱም አንዲት በሌላ ሃይማኖት ትኖር የነበረችን እህት እና ሕፃን በማጥመቅ የሥላሴን ልጅነት እንዲያገኙ ያደረጉ ሲሆን በቻይና የመጀመሪያውን አንድ ኢትዮጵያዊ ዲያቆን ሾመዋል።

በተጨማሪም ከቻይና የተለያዩ ክፍላተ ግዛት የተሰባሰቡ ምእመናን፣ ቻይናውያን እና ትውልደ ቻይናውያን በሥርዓተ ቅዳሴው ተሳትፈዋል፡፡

የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት

የሩቅ ምሥራቅ፣ ዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ  አኅጉራተ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የዓለም የሰላም ፌደሬሽን አምባሳደር ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ መንበረ ጵጵስናቸው ቻይና...
06/12/2024

የሩቅ ምሥራቅ፣ ዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ አኅጉራተ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የዓለም የሰላም ፌደሬሽን አምባሳደር ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ መንበረ ጵጵስናቸው ቻይና ገቡ።

ብፁዕነታቸው የቻይና ዋና ከተማ ቤጂንግ አየር ማረፊያ Beijing Capital Airport (PEKING) ሲደርሱ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር በኾኑት አምባሳደር ተፈራ ደርበው እንዲሁም አምባሳደር ደዋኖ ከድርን የሚስዮኑ ምክትል ኃላፊን ጨምሮ የኢምባሲ ተወካይ ዲፕሎማቶች፣ የሩቅ ምሥራቅ ሀገረ ስብከት ተወካዮች እና በቦታው በተገኙ ምእመናን ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በመቀጠልም ወደ ቲያንጅን ከተማ ጉዞ አድርገው ከተያዘላቸው ማረፊያ በሰላም ገብተዋል።
የብፁዕነታቸው ሐዋርያዊ ተልዕኮ እንዲሆን የዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት መልካም ምኞቱን ይገልጻል ።

Address

London

Telephone

+447944141513

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EOTC UKI Diocese Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to EOTC UKI Diocese Office:

Share

Category