Jesus Is Muslim

Jesus Is Muslim Jesus Is Muslim

12/06/2024
ዒሣ ቃል አይደለምበአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።4፥71 "የመርየም ልጅ አል-መሲሕ ዒሣ የአላህ መልእክተኛ ብቻ ነው፣ ወደ መርየም የጣላት «የኹን» ቃል ነው፣ ከ...
29/04/2024

ዒሣ ቃል አይደለም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

4፥71 "የመርየም ልጅ አል-መሲሕ ዒሣ የአላህ መልእክተኛ ብቻ ነው፣ ወደ መርየም የጣላት «የኹን» ቃል ነው፣ ከእርሱ የኾነ መንፈስ ነው”*፡፡ إِنَّمَا الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ اللَّهِ وَكَلِمَتُهُ أَلْقَاهَا إِلَىٰ مَرْيَمَ وَرُوحٌ مِّنْهُ

ከላም” كَلَام የሚለው ተባታይ መደብ "ከለመ" كَلَّمَ ማለትም "ተናገረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ንግግር"speech" ማለት ነው፥ "ከሊማህ" كَلِمَة ደግሞ የከላም አንስታይ መደብ ነው። አምላካችን አሏህ "ሙተከለም” مُتَكَلِّم ማለትም "ተናጋሪ"speaker ሲሆን አንድ ነገርን ማስገኘት ሲፈልግ በቃሉ "ኩን" كُن ይለዋል ወዲያውኑ ይሆናል፦
16፥40 ለማንኛውም ነገር መኾኑን በሻነው ጊዜ "ቃላችን" ለእርሱ “ኹን” ማለት ብቻ ነው፥ ወዲውም ይኾናል፡፡ إِنَّمَا قَوْلُنَا لِشَيْءٍ إِذَا أَرَدْنَاهُ أَن نَّقُولَ لَهُ كُن فَيَكُونُ

"ቃላችን" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! ክርስቲያኖች፦ "ፈጣሪ ልጅ አለው" ሲሉ አምላካችን አሏህ፦ “ነገርንም ማስገኘት በሻ ጊዜ ለእርሱ የሚለው “ኹን” ነው፥ ወዲያውም ይኾናል” የሚል ምላሽ ሰጠ፦
19፥35 ለአላህ ልጅን መያዝ አይገባውም፡፡ ከጉድለት ሁሉ ጠራ፡፡ ነገርን በሻ ጊዜ ለእርሱ የሚለው «ኹን» ነው ወዲያውም ይኾናል፡፡ مَا كَانَ لِلَّهِ أَن يَتَّخِذَ مِن وَلَدٍ ۖ سُبْحَانَهُ ۚ إِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ

መርየምም፦ "ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል?” ስትል፥ መለኮታዊ መልስ፦ "አላህ የሚሻውን ይፈጥራል፥ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል" የሚል ነው፦
3፥47 ፡-ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል? አለች፡፡ ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አላህ የሚሻውን ይፈጥራል፥ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል አላት*፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ ۖ قَالَ كَذَٰلِكِ اللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ إِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ

አንድ ጊዜ የየመን ክርስቲያኖች፦ "ዒሣ የአላህ ልጅ ካልሆነ እንግዲያውስ አባቱ ማን ነው? ብለው ጠየቁ፥ አምላካችን አሏህም ይህንን አንቀጽ አወረደ፦
3፥59 አላህ ዘንድ የዒሣ ምሳሌ እንደ ኣደም ብጤ ነው፡፡ ከአፈር ፈጠረው፡፡ ከዚያም ለ"እርሱ" «ኹን» አለው፤ ኾነም፡፡ إِنَّ مَثَلَ عِيسَىٰ عِندَ ٱللَّهِ كَمَثَلِ ءَادَمَ ۖ خَلَقَهُۥ مِن تُرَابٍۢ ثُمَّ قَالَ لَهُۥ كُن فَيَكُونُ

“ኸለቀ” خَلَقَ ማለትም “ፈጠረ” በሚለው ግሥ መዳረሻ ቅጥያ ላይ “ሁ” هُۥ ማለት “እርሱ” የሚል ተሳቢ ተውላጠ-ስም አለ፥ ይህም የስም ምትክ “ኣደም” ءَادَم የሚለውን የተጸውዖ ስም ተክቶ የመጣ ነው። አደም እና ዒሣ የተመሳሰሉበት ነጥብ የተፈጠሩበት ንጥረ-ነገር ሳይሆን የተፈጠሩበት ሁኔታ ነው፥ ሁለቱም በታምር ኹን በሚለው ቃል መፈጠራቸው ነው። አሏህ ዒሣን ከመርየም ለመፍጠር ወደ እርሷ የጣላት ቃል "ኩን" كُن የምትል ናት፦
4፥71 "የመርየም ልጅ አል-መሲሕ ዒሣ የአላህ መልእክተኛ ብቻ ነው፣ ወደ መርየም የጣላት «የኹን» ቃል ነው፣ ከእርሱ የኾነ መንፈስ ነው”*፡፡ إِنَّمَا الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ اللَّهِ وَكَلِمَتُهُ أَلْقَاهَا إِلَىٰ مَرْيَمَ وَرُوحٌ مِّنْهُ

የመጀመሪያው ዓረፍተ-ነገርን ላይ “ኢነማ” إِنَّمَا ማለት “ብቻ” ማለት ሲሆን ይህ ገላጭ ቅጽል ዒሣ የአሏህ መልእክተኛ እንጂ ሌላ እንዳልሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
፨ሁለተኛው ዓረፍተ-ነገርን ላይ "ወ" وَ የሚል አርፉል አጥፍ ከመጀመሪያ ዓረፍተ-ነገርን ለመለየት የመጣ ነው፥ "ወ-ከሊመቱሁ አልቃሃ ኢላ መርየም" وَكَلِمَتُهُ أَلْقَاهَا إِلَىٰ مَرْيَم ማለትም "ወደ መርየም የጣላት የይኹን ቃላት ናት" ማለት ነው። "ከሊማህ" كَلِمَة አንስታይ መደብ ናት፥ የከሊማህ ብዙ ቁጥር ደግሞ "ከሊመት" كَلِمَت ወይም "ከሊማት كَلِمَات ነው። ይቺ ቃሊት አንስታይ መደብ ስለሆነች “አልቃሃ” أَلْقَاهَا ማለትም “የጣላት” ተብላለች፥ ዒሣ ቃል ቢሆን ኖሮ በተባታይ መደብ “አልቃሁ” أَلْقَاهُ ማለትም “የጣለው” ይባል ነበር። ቅሉ ግን ይህቺ የይኹን ቃላት መንስኤ ስትሆን ዒሣ ደግሞ ውጤት ነው። ቀደምት ሠለፎች የተረዱት በዚህ መልክ እና ልክ ነው፦
ተፍሢፉ ኢብኑ ከሲር 4፥171
ኢብኑ አቢ ሐቲም እንደዘገበው፦ “አሕመድ ኢብኑ ሢናነል ዋሢጢይ እንደተናገረው፦ “ሻዝ ኢብኑ የሕያ”ረ.ዐ.” እንዲህ አለ፦ ”ወደ መርየም የጣላት የሁን ቃሉም ነው” የሚለው “ቃሊቷ እራሷ ዒሣ አልሆነችም፥ ነገር ግን በቃሊቱ ዒሣ ተገኘ እንጂ”። وقال ابن أبي حاتم : حدثنا أحمد بن سنان الواسطي قال : سمعت ش*ذ بن يحيى يقول : في قول الله : ( وكلمته ألقاها إلى مريم وروح منه ) قال : ليس الكلمة صارت عيسى ، ولكن بالكلمة صار عيسى

፨ሦስተኛው ዓረፍተ-ነገርን ላይ "ወ" وَ የሚል አርፉል አጥፍ ከሁለተኛው ዓረፍተ-ነገርን ለመለየት የመጣ ነው፥ "ወ-ሩሑን ሚን-ሁ" وَرُوحٌ مِّنْهُ ማለትም "ከእርሱ የኾነ መንፈስ ነው" ይላል፥ “ሁ” هُ ማለትም “እርሱ” የተባለው አሏህ ሲሆን “ሁ” هُ በሚለው ተውላጠ-ስም መነሻ ላይ “ሚን” مِنْ የሚል መስተዋድድ የዒሣ ሩሕ ከአሏህ ዘንድ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ይህንን የሚያስረዳ አንድ ተመሳሳይ የሰዋስው ሙግት እንይ፦
45፥13 ለእናንተም በሰማያት ያለውንና በምድርም ያለውን ሁሉ በመላ “ከ-እርሱ” ሲኾን የገራላችሁ ነው፡፡ وَسَخَّرَ لَكُم مَّا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا مِّنْهُ

“በሰማያት ያለውንና በምድርም ያለውን ሁሉ በመላ ከእርሱ ነው” የሚለው ይሰመርበት! “ሚን-ሁ” مِنْهُ ማለትም “ከ-እርሱ” የሚለው ፍጥረት ከአሏህ መሆኑን እንደሚያሳይ ሁሉ የዒሣም ሩሕ ከአሏህ መሆኑን ያሳያል፦
21፥91 ያችንም ብልቷን የጠበቀቺውን ”በእርሷም ውስጥ ከመንፈሳችን የነፋንባትን” እርሷንም ልጅዋንም ለዓለማት ተዓምር ያደረግናትን መርየምን አስታውስ፡፡ وَالَّتِي أَحْصَنَتْ فَرْجَهَا فَنَفَخْنَا فِيهَا مِن رُّوحِنَا وَجَعَلْنَاهَا وَابْنَهَا آيَةً لِّلْعَالَمِينَ

“ፊ-ሃ” فِيهَا ማለት “በ-እርሷ ውስጥ” ማለት ነው፥ “እርሷ” የተባለችው የዒሣ እናት መርየም ናት። በመርየም ማኅፀን ውስጥ ሩሕ ሲነፋ ይህ የተነፋው ሩሕ ከአሏህ ነው፥ አምላካችን አሏህ ወደ መርየም የነፋውን ሩሕ ወደራሱ በማስጠጋት “ሩሒ-ና” رُّوحِنَا ማለትም “መንፈሳችን” እንደሚል ሁሉ ወደ አደም አካል የነፋውንም ሩሕ ወደራሱ በማስጠጋት “ሩሒ-ሂ” رُّوحِهِ ይላል፦
32፥9 “ከዚያም ቅርጹን አስተካከለው፥ “በ-እርሱ ውስጥም” ከመንፈሱ ነፋበት”። ثُمَّ سَوَّاهُ وَنَفَخَ فِيهِ مِن رُّوحِهِ

ለአደም ሩሕ ስለተሰጠው “አደም የአሏህ መንፈስ ነው” እንደማንል ሁሉም ለዒሣም ሩሕ ስለተሰጠው “ዒሣ የአሏህ መንፈስ ነው” አይባልም። የዒሣም ሆነ የአደም አሊያም የሁላችንም ሩሕ ከአሏህ ነው፦
17፥85 ስለ ሩሕ ይጠይቁሃል፥ «ሩሕ ከጌታዬ ነገር ነው፥ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም» በላቸው፡፡ وَيَسْأَلُونَكَ عَنِ الرُّوحِ ۖ قُلِ الرُّوحُ مِنْ أَمْرِ رَبِّي وَمَا أُوتِيتُم مِّنَ الْعِلْمِ إِلَّا قَلِيلًا

“ሩሕ ከጌታዬ ነገር ነው” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! በዚህ አንቀጽ መሠረት የሁላችንም ሩሕ ከአፈር ሳይሆን ከጌታችን ከአላህ ነገር ነው፥ ያ ማለት “እኛ የአሏህ መንፈስ ነን” ማለት አይደለም። የሰው ሩሕ ደግሞ “ነገር” ነው፥ አሏህ የሁሉ “ነገር” ፈጣሪ ስለሆነ የማንም ሰው ሩሕ ፍጡር ነው፦
39፥62 አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ

ቁርኣን ላይ፦"ዒሣ የአሏህ ቃል ነው ወይም ዒሣ የአሏህ መንፈስ ነው" የሚል ፍንጭ ይቅርና ሽታው የለም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

✍ ኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

የበለጠ ለማወቅ
ጥሪያችን Tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም

https://youtube.com/?si=jsB5JEny9sdzgj07
13/09/2023

https://youtube.com/?si=jsB5JEny9sdzgj07

16፥125 ወደ ጌታህ መንገድ በጥበብ እና በመልካም ግሳጼ ጥራ፡፡ ادْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِالْحِكْمَةِ وَالْمَوْعِظَةِ الْحَسَنَةِ

✅እግዚአብሄር :– እኔ ሰው አይደለሁም።( ሆሴዕ 11:9 )                           Vs✅ኢየሱስ :– እኔ ሰው ነኝ። (ዮሐንስ ወንጌል 8:40 )( ትንቢተ ሆሴዕ 11:9 ) ...
24/07/2023

✅እግዚአብሄር :– እኔ ሰው አይደለሁም።( ሆሴዕ 11:9 )
Vs
✅ኢየሱስ :– እኔ ሰው ነኝ። (ዮሐንስ ወንጌል 8:40 )

( ትንቢተ ሆሴዕ 11:9 ) እኔ እግዚአብሔር አምላክ ነኝ
እንጂ ፥

ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ነኝ ብሏል በራሱ አንደበት‼

(የዮሐንስ ወንጌል 8:40 ) ነገር ግን አሁን ከእግዚአብሔር
የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን #ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ::

ግን ግን........‼

ኢየሱስ በተደጋጋሚ ሰው ነኝ እንጂ እኔ አምላክ አይደለሁም እያለ እየተማፀናቹ እናንተ አይ ኢየሱስ አምላክ ነህ፣ አንተኮ ጌታችን ነህ፣ ፈጣሪ ነህ ብላችሁ የምታመልኩት ከሆነ ይህን መልዕክት አስቀምጦላቹሃል፣

21 በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ፥ ጌታ ሆይ፥ ።

22 በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል።

23 የዚያን ጊዜም። ፤ ፥ ።

ልብ አድርጉ‼
ይህን የሚመለከተው ኢየሱስ ጌታ ነው፣ አምላክ ነው ለሚሉት #ለክርስቲያን ነን ባዮች ያስተላለፈው ጠንካራ መልዕክት ነው።

ስለዚህ ኢየሱስን ስሙ ❗️ከፊቴ ጥፉ አላውቃችሁም እላቹሃለው እያላቹ ነውኮ።

በሚልኪያስ 3:6 ላይ "እኔ እግዚአብሄር አልለዋወጥም"። ይላል
ታድያ ሰው የሆነ እየሱስ ክርስቶስ እንዴት አምላክ ሊሆን ይችላል❓

ትንቢተ ኢሳያስ 40:28 "የሚደክመዉን ሰው አምላክ አትበለው፤ አምላክ አይደክመውምና።"

ዩሀንስ 4:6 ላይ ደግሞ "እየሱስ ክርስቶስ ደክሞት ጉድጎድ አጠገብ ተቀመጠ።" ይለል

ታድያ አምላክ የሚደክም ካልሆነ የደከመው እየሱስ እንዴት አምላክ ይሆናል❓

☞ተው ግን አምላክ ሰው ነው እያላቹህ ሃጢያት አትኮናነቡ አምላክን እየተሳደባቹህ ‼ok‼
ህፃን ሆነ ማህፀን የሃይድ ደም ሲጎነጭ ከወጣም እንጣየ ሲበላ ጡጦውን ሲጠጣ ከዚያም ሲፈሳ ሲፍሳ ካካ እያደረገ እየሸና እየፈነጠዘ እየፏለል የሚያድገው የሰው ልጂ ብቻ እና ብቻ ነው።

የጳውሎስ ኩረጃበአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡3፥71 «የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በሐሰት ለምን ትቀላቅላላችሁ? እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ...
24/07/2023

የጳውሎስ ኩረጃ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥71 «የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በሐሰት ለምን ትቀላቅላላችሁ? እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ትደብቃላችሁ?» يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لِمَ تَلْبِسُونَ الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُونَ الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ

ጥንት የነበሩት የፈጣሪ ነቢያት በአምላክ ተልከው ትንቢት ሲመጣላቸው የሚናገሩት በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ነበር፦
2ኛ ጴጥሮስ 1፥21ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በአምላክ ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ።

"በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ" እንጂ "በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ጻፉ" አይልም፥ ብዙ ሰዎች ጳውሎስ የጻፋቸውን አሥራ አራት ደብዳቤዎች"letters" "በመንፈስ ቅዱስ ተነድቶ ነው" ይላሉ። ቅሉ ግን በመንፈስ ቅዱስ ተነድቶ የተጻፈ ጽሑፍ የለም፥ ባይሆን በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው የተናገሩት ንግግር አለ። ይህም ከአምላክ ተልከው ትንቢት እንጂ ታሪክ አይደለም፥ ከመነሻው ይህ ጥቅስ ስለ ነቢያት እንጂ ስለ እነ ጳውሎስ ሽታው የለውም።
ጳውሎስ ብዙ ጊዜ ከጥንት ነቢያት ሲጠቅስ ስለሚሳሳት የሚጽፈው በመንፈስ ቅዱስ በጭራሽ አይደለም፦
1ኛ ቆሮንቶስ 2፥9 ነገር ግን፦ "ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው አምላክ ለሚወዱት ያዘጋጀው" ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።

በብሉይ ኪዳን "ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው" ተብሎ የተጻፈ በባትሪ ብትፈልጉ አታገኙም፥ ጥቅሱን የወሰደበት ቦታ አምላክ ስላዘጋጀው ነገር ሳይሆን አሐዳውያን ባዕድ አምላክን መስማት፣ መቀበል እና ማየት እንዳልፈለጉ የሚያስጨብጥ ነው፦
ኢሳይያስ 64፥4 ሰዎች ከጥንት ጀምሮ ለሚጠብቁህ ከምትሠራላቸው ከአንተ በቀር ሌላ አምላክን አልሰሙም በጆሮአቸውም አልተቀበሉም ዓይንም አላየችም።

ጳውሎስ ሲኮርጅ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ቢሆን ኖሮ በትክክል ማስቀመጥ ያቅተዋልን? እንቀጥል! ጳውሎስ ከኢሳይያስ ጠቅሶ እንዲህ ይሳሳታል፦
ሮሜ 11፥26 እንደዚሁም እስራኤል ሁሉ ይድናል፤ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፦ "መድኃኒት ከጽዮን ይወጣል፥ ከያዕቆብም ኃጢአተኛነትን ያስወግዳል።
ኢሳይያስ 59፥20 ለጽዮን ታዳጊ ይመጣል፥ በያዕቆብም ዘንድ ከኃጢአት ለሚርቁ፥ ይላል ያህዌህ። וּבָ֤א לְצִיֹּון֙ גֹּואֵ֔ל וּלְשָׁבֵ֥י פֶ֖שַׁע בְּיַֽעֲקֹ֑ב נְאֻ֖ם יְהוָֽה

"ለጽዮን ታዳጊ ይመጣል" ማለት እና "መድኃኒት ከጽዮን ይወጣል" ማለት ሁለት የተለያየ ቃላት ነው፥ "በያዕቆብም ዘንድ ከኃጢአት ለሚርቁ" ማለት እና "ከያዕቆብም ኃጢአተኛነትን ያስወግዳል" ማለት ሁለት የተለያየ ቃላት ነው። መንፈስ ቅዱስ ይህ ጠፍቶት ነው? ጳውሎስ የኮረጀው ከዕብራይስጡ ሳይሆን ከግሪክ ሰፕቱጀንት ነው፦
καὶ ἥξει ἕνεκεν Σιὼν ὁ ῥυόμενος καὶ ἀποστρέψει ἀσεβείας ἀπὸ ᾿Ιακώβ.

ግሪክ ሰፕቱጀንት የዕብራይስጥ ቅጂ ሳይሆን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ የትርጉም ሥራ ነው፥ ጳውሎስ ከትርጉም ሥራ ላይ እየኮረጀ "የአምላክ መገለጥ ነው" ብሎ መቅጠፉ ጥሩ አይደለም። ጳውሎስ እንዲህ ዓይነት የኩረጃ ስህተቶችን የተሳሳተባቸው በቁና ማቅረብ ይቻል ነበር፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን አንባቢያንን ማሰልቸት ነው።
የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! ከአምላክ የመጣውን እውነት ከኩረጃ ንግግር ጋር ለምን ትቀላቅላላችሁ? ይህ ሥራ ዋጋ ያስከፍላል፦
3፥71 «የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በሐሰት ለምን ትቀላቅላላችሁ? እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ትደብቃላችሁ?» يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لِمَ تَلْبِسُونَ الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُونَ الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ

አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

★ቅዱስ ቁርአን ከመፅሀፍ ቅድስ ገልብጧል ለሚለው ትችት የማያዳግም ኢስላማዊ መልስ ★ክፍል ~1~          ‼ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic ¶ለመጀመሪያ ጊዜ ብሉይ ኪዳን...
22/07/2023

★ቅዱስ ቁርአን ከመፅሀፍ ቅድስ ገልብጧል ለሚለው ትችት የማያዳግም ኢስላማዊ መልስ ★
ክፍል ~1~ ‼
ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic
¶ለመጀመሪያ ጊዜ ብሉይ ኪዳን (መፅሀፍ ቅዱስ) #በአረብኛ ቋንቋ የተተረጎመው ነቢዩ ከሙሀመድ (ሰአወ) ህልፈት ወይም ከሞቱ ከ200 አመታት በኋላ ነው ።¶

በመፅሀፈ ኢሳያስ 29:12 "ማንበብና መፃፍ የማይችለውን ነቢይ ይከተላሉ ይላል

ቅዱስ ቁርአን ከመፅሀፍ ቅዱስ ነው የኮረጀው ብለው ሂስ የሚያቀርቡ ሰዎች ያለተረዱት ነገር ቢኖር.......

☞ነቢዩ ሙሀመድ (ሰአወ) ማንበብም ሆነ መፃፍ የማይችሉ ከመሆናቸውም ባሻገር በነበሩበት ዘመን በአረብኛ ቋንቋ የተተረጎመ ብሉይ ኪዳንም አዲስ ኪዳንም መፅሀፍ ቅዱስ በፍፁም አለመኖሩን ትልቁ ማስረጃ ነው ።✔ አእምሮ ላለው ብቻ‼

ሲቀጥል

☞ለመጀመሪያ ጊዜ ብሉይ ኪዳን በአረብኛ ቋንቋ የተተረጎመው (እአአ) በ 900 ዓል #አርፋዲያ በተባለ ሰው ነው።

ይህ ማለት ነቢዩ ሙሀመድ (ሰአወ) ከሞቱ ከ200 አመት በኋላ መሆኑ ነው ።

እዚህ ጋር ልብ አድርጉ☞ ከ 200 አመታት በኋላ‼

☞ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ ኪዳን (ወንጌል) ወደ አረብኛ የተተረጎመው #አርፔኒየስ በተባለ ሰው (እአአ) 1616 ነው።

ይህ ማለት ነቢዩ ሙሀመድ (ሰአወ) ከሞቱ ከ1,000 አመታት በኋላ መሆኑ ነው ።

እዚህም ጋ በደምብ ልብ አድርጉልኝ☞ ከ 1000 አመታት በኋላ‼

☞በእርግጥ ቁርአንና ባይብል ሊያመሳስላቸው የሚችል ጥቂት መልእክቶች ይኖራሉ ...... ይህ ማለት ቅዱስ ቁርአን ቀድሞ ከመጣው ባይብል ኮርጆ ነው ለማለት አያስችልም፣ አያስደፍርምም,,,

ሁለቱም ምንጩ አንድ ከሆነ ከሌላ ከሶስተኛ አካል እንደመጡ ሊጠቁሙ ይችላል ።

☞የአላህ (ሱወ) መልእክት በአንድ አምላክ የማመን መልእክት ነው ።

ቀደም ሲል ከአላህ ለሰው ልጆች የተሰጡ መፅሀፍት በክልል ወይም በጊዜው የተገደቡ ሲሆን,, በሰው ልጅ የተበረዙና የተከለሱ በርካታ ነገሮችን ይዘዋል ።

እንደዛም ሆኖ የተወሰኑ የጋራ የሆኑ መመሳሰሎች ዛሬም ድረስ አሉ ።
ይህንን መነሻ በማድረግ ብቻ ነቢዩ መሀመድ ሰአወ ከመፅሀፍ ቅዱስ ኮረጀዋል ማለት በፍፁም አያስችልም ።

እንዲሁም ደግሞ (አዲስ ኪዳንና ብሉይ ኪዳን) በርካታ መመሳሰሎችም ስላላቸው ኢሳ (አሰ) ከብሉይ ኪዳን ኮርጆ ነው ማለትም አይቻለም ።

የሁለቱም ምንጭ አንድ ነውና ።

☞ለምሳሌ አንድ ተማሪ ከሌላ ተማሪ ፈተና ቢኮርጅ ከማን እንደኮረጀ የመልስ ወረቀቱ ላይ አይፅፍም ።

☞ ነቢዩ ሙሀመድ (ሰአወ) በቁርአን በተገለፀላቸው መሰረት ሙሳ ፣ኢሳ ፣ኢብራሂም (ዐሰ) ከአላህ የተላኩ ነቢያቶች መሆናቸውን በቁርአን (በአላህ ቃል) አስተላልፈዋል,,,,

የሚገባቸውን ክብርም ሰትተዋል ። እንግዲህ ቁርአንን ከመፅሀፍ ቅዱስ ቢኮርጁ ኖሮ ይህንን አያደርጉም ነበር ። ይህም ላለመኮረጁ ሁለተኛው ማስረጃ ነው ።

,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,

☞ታሪካዊ በሆኑ ጉዳዮች ብቻ በመመርኮዝ መፅሀፍ ቅዱስ ወይም ቁርአን ልክ ናቸው ለማለት አንችልም ። ማን ትክክል እንደሆነ ሳይንሳዊ እውነታዎችን በመመርኮዝ በሚቀጥለው ክፍል እንመለከታለን ።
https://www.facebook.com/profile.php?id=100064506050455 ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic

ክፍል ~2~ ይቀጥላል …………

#ሼር✔

ኢየሱስ ክርስቶስ "  #የሚያመልከው" እና "  #የሚፀልይለት " "የሚማፀነው" "የሚለምነው" የፈጠረው  " ነበረው።ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic ኢየሱስ ወደ አምላኩ ይጸል...
16/07/2023

ኢየሱስ ክርስቶስ " #የሚያመልከው" እና " #የሚፀልይለት " "የሚማፀነው" "የሚለምነው" የፈጠረው " ነበረው።
ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic
ኢየሱስ ወደ አምላኩ ይጸልይ [ዱዓ ያደርግ] እንደነበር በትንሹ "12" መፅሀፍ ቅዱሳዊ (የወንጌል) ማስረጃዎች እንመልከት:

1• ኢየሱስም "ሕዝቡንም አሰናብቶ ብቻውን ወደ ተራራ ወጣ። በመሸም ጊዜ ብቻውን በዚያ ነበረ።”(የማቴዎስ ወንጌል 14:23)

ኢየሱስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

2• ኢየሱስም "ነገር ግን እርሱ ወደ ምድረ በዳ ፈቀቅ ብሎ ።”(የሉቃስ ወንጌል 5:16)

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

3• ኢየሱስም "በነዚህም ወራት ወጣ፥ ሌሊቱንም ሁሉ ።” (የሉቃስ ወንጌል 6:12)

ኢየሱስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

4• "እየሱስም በአንድ ስፍራ ” (የሉቃስ ወንጌል 11:1)

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

5• ኢየሱስም "በፍርሃትም ሲጣጣር ” (የሉቃስ ወንጌል 22:44)

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

6• ኢየሱስም "አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ።”(የዮሀንስ ወንጌል 12:27)

7• "እየሱስም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት”(ወደ እብራውያን ሰዎች 5:7)

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

ተሰማለት ይላል
ማነው ፀሎቱን የሰማለት?

8• "ኢየሱስም ደግሞ ሁለተኛ ሄዶ #ጸለየና። አባቴ፥ ይህች ጽዋ ሳልጠጣት ታልፍ ዘንድ የማይቻል እንደ ሆነ፥ ፈቃድህ ትሁን አለ።” (የማቴዎስ ወንጌል 26:42)

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

9• "ደግሞም ኢየሱስ ትቶአቸው ሄደ፥ #ሦስተኛም ያንኑ ቃል ።”(የማቴዎስ ወንጌል 26:44)

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

10• "ኢየሱስም ማለዳም ተነሥቶ ገና ሌሊት ሳለ ወጣ ወደ ምድረ በዳም ።”(የማርቆስ ወንጌል 1:35)

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

11· "ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም። አባት ሆይ፥ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ ።" (የሉቃስ ወንጌል 22:41_42)

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

12• "ኢየሱስም ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በምድርም ወድቆ፥ ይቻልስ ቢሆን ሰዓቲቱ ከእርሱ ። አባት ሆይ፥ ሁሉ ይቻልሃል፤ ፤ ነገር ግን አንተ የምትወደው እንጂ እኔ የምወደው አይሁን አለ።"(የማርቆስ ወንጌል 14:35_36)

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወይም ፈጣሪ ከሆነ ታድያ
✔ለማን ነው ሚፀልያው?
✔ ወደማንስ ነው ሚፀልየው?

https://www.facebook.com/profile.php?id=100064506050455 ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic
👆 Click &👆Follow 👆Follow👆👆
ኑ ወደ ኢስላም ሰላም ታገኛላችሁ።

#ሼር ያድርጉት✔ በማድረግ የዳዕዋው አንድ አካል ይሁኑ

ሶላትና እንቅስቃሴዎች በአንድ ነገር ብቻ የተወሰነ አይደለም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።አምስት አውቃ ሶላት የቀልብና የሰውነት ተግባራት በውስጧ ይፈጠማሉ...
15/07/2023

ሶላትና እንቅስቃሴዎች በአንድ ነገር ብቻ የተወሰነ አይደለም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አምስት አውቃ ሶላት የቀልብና የሰውነት ተግባራት በውስጧ ይፈጠማሉ ። በውስጧ ቁረአን መቅራት ወይም ማንበብ ዱዓአ ማድረግ አላህን ማስተወስና ማወደስ ከአላህ እርዳታ መጠየቅ መተናነስ ን ማሳየት ከሱ ሌላ ረዳት እንደሌለን ማረጋገጫ ።

ሶላት የሙስሊሞች መገለጫ የእምነታቸውና የጌታቸውን ቃል መተግበሪያ በሰው ልጆችና በአላህ ሱበሀን አላህ ወተአላ መካከል ያለውን መንገድ ማቀራረቢያ የሕመም እና የጭንቀት መፈወሻ እጅግ ውብ እና አማኝ የሆነ የሙስሊሞች መገለጫ ሶላት ናት

በሰላቶች ተጠባበቁ ይላል ( አል -በቀራ ፣ 238 )

የተውሒድ ጠብታ (لا إله إلا الله) የተራራ ግዝፈት ያላቸውን ወንጀሎች ያጸዳቸዋል። የሽርክ ጠብታ ደግሞ የተራራ ግዝፈት ያላቸውን መልካም ተግባራት ከንቱ ያደርጋል። ولا تموتن إ...
12/07/2023

የተውሒድ ጠብታ (لا إله إلا الله) የተራራ ግዝፈት ያላቸውን ወንጀሎች ያጸዳቸዋል። የሽርክ ጠብታ ደግሞ የተራራ ግዝፈት ያላቸውን መልካም ተግባራት ከንቱ ያደርጋል።

ولا تموتن إلا وأنتم مسلمون!

❝...ሙስሊሞች ኾናችሁ እንጅ አትሙቱ..❞

(ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 102)

እነዚህ ሴቶች ወንጌል ላይ በትንሹ 6 ቦታ ላይ  የኢየሱስን ትዕዛዝ  ጥሰዋል።ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic ሸይኽ አህመድ ዲዳት ኢየሱስ እንዲህ አለ “ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠ...
10/07/2023

እነዚህ ሴቶች ወንጌል ላይ በትንሹ 6 ቦታ ላይ የኢየሱስን ትዕዛዝ ጥሰዋል።
ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic ሸይኽ አህመድ ዲዳት
ኢየሱስ እንዲህ አለ “ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ።”
— ዮሐንስ 14፥15-16

1) ✅ወንድ ልጅን በድፍረት ሰብካለች ፣ ይህም በወንጌል ስህተት/ሀጢያት/ ነው።
✔ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡34 ,
✔1ኛ ጢሞቲዎስ 2:11–12)

2)✅ ፀጉሯን በአደባባይ ከፍታለች ይህም በወንጌል ትልቅ ስህተት ነው።
✔☞ ((👇“በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ ሴት ራስዋን ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር ልትጸልይ ይገባታልን?”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥13
👇
✔1ኛ ቆሮ 11: 4_7,
✔1ኛ ጴጥሮስ 3:3–6 ፣
✔ 1ኛ ጢሞ 2:9–10)

3) ✅ሱሪና ታይት ታጥቃለች ይህም በወንጌል ሀጢያት ነው።
✔ (ዘዳግም 22፥5 ፣
✔ ትን.ሶፎ. 1፡18))

4)✅ በአደባባይና በአዳራሽ ሰው በተሰበሰበበት በድፍረት ሰብከዋል፣ ይህም ወንጀል ነው።
✔ ☞((1ኛ ቆሮንቶስ 14፡34-35 ፣ )

5)✅ እንግዳ ልብስ ለብሰዋል፣ ይህም በወንጌል ሀጢያት ነው።
✔☞ (ትን.ሶፎ. 1፡18)

6) ✅በአደባባይ ፀጉሯ ላይ ጌጣጌጥ አጥልቃለች፣ ይህም በወንጌል ክልክል ነው።
✔☞ (1ኛ ጴጥሮስ 3:3–6 ፣ )
☞(1ኛ ጢሞ 2:9–10)

እየሱ'ስ ክርስቶ'ስ አምላክ  #ላለመሆኑ 10 ወሳኝ ማስረጃዎ'ች ከወንጌል‼~~~~~~~~~~~~~~~~~~~http://goo.gl/l9WyYf https://goo.gl/6DMB831- እየ'ሱስ ክር'...
04/07/2023

እየሱ'ስ ክርስቶ'ስ አምላክ #ላለመሆኑ 10 ወሳኝ ማስረጃዎ'ች ከወንጌል‼
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
http://goo.gl/l9WyYf https://goo.gl/6DMB83

1- እየ'ሱስ ክር'ስቶስ አልነበረም፡፡ ‼

እንደሚታወቀው አምላክ ሁሉን አዋቂ ነው፡፡ ከዕውቀቱ የሚደበቅ ምንም ነገር የለም፡፡ እ'የሱስ ክርስ'ቶስ ግን እንደ መፅሀፍ "ቅዱ'ስ" ገለፃ ይህንን መስፈርት አያሟላም፡፡

" ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ #ልጅም [ኢየሱስ ክርስቶስም] ቢሆን ከአባት [ከእግዚአብሔር] በቀር ።"
(የማርቆስ ወንጌል 13:32)

2- እየሱስ ክርስቶስ አንዲትም ጊዜ ብሎ አያቅም‼

በብሉይ ኪዳን እግዚአብሄር እጅግ ብዙ ቦታዎች ላይ አምላክነቱን ሲያውጅና ሲገልፅ እንመለከታለን!
እየሱስ ክርስቶስ ግን በተቃራኒው ስለዚህ ጉዳይ ትንፍሽ አላለም፡፡
እስኪ ከብሉይ ኪዳን ለአብነት እንመልከት‼

" እግዚአብሔርም አለው። ፤ ብዛ፥ ተባዛም፤ "
(ዘፍጥረት 35:11)

" አለውም። የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤ ወደ ግብፅ መውረድ አትፍራ፥ በዚያ ትልቅ ሕዝብ አደርግሃለሁና።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 46:3)

"እግዚአብሔርም ሙሴን አለው። የእስራኤልን ልጆች ማንጐራጐር ሰማሁ። ወደ ማታ ሥጋን ትበላላችሁ፥ ማለዳም እንጀራን ትጠግባላችሁ፤ እኔም እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ በላቸው። "
(ኦሪት ዘጸአት 16:11,12)

" ከግብፅ ምድር ከባርነት ቤት ያወጣሁህ እግዚአብሔር ። "
(ኦሪት ዘጸአት 20:2)

3- እየሱስ በአዲስ ኪዳን የሰው ልጅ ተብሎ ተጠርቷል‼ እራሱ መፅሀፍ "ቅዱስ" እንደሚነግረን ደግሞ ይነግረናል‼

" ኢየሱስም። ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይም ወፎች መሳፈሪያ አላቸው፥ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም አለው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 8:20)

" ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአትን ያስተሰርይ ዘንድ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፥ በዚያን ጊዜ ሽባውን። ተነሣ፤ አልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ አለው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 9:6)

" የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነውና።" (የማቴዎስ ወንጌል 12:8)

" ለደቀ መዛሙርቱ። የሰው ልጅ በሰው እጅ ይሰጥ ዘንድ አለውና እናንተ ይህን ቃል በጆሮአችሁ አኑሩ አለ።"
(የሉቃስ ወንጌል 9:44)

ሌላ ቦታ ባይብልን ስናነብ ደግሞ የሰው ልጅ መታመን እንደሌለበት ይነግረናል፡፡

(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 146)
----------
1፤ ሃሌ ሉያ። ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን አመስግኚ።

2፤ በሕይወቴ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤ በምኖርበት ዘመን ሁሉ ለአምላኬ እዘምራለሁ።

3፤ ማዳን በማይችሉ በሰው ልጆችና በአለቆች አትታመኑ።

4ኛ) - እየሱስ ክርስቶስ የነበረው ስልጣንና ሀይል የእርሱ የራሱ የኢየሱስ አልነበረም፡፡‼

✔ " ኢየሱስ አብ ሁሉን በእጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥"
(የዮሐንስ ወንጌል 13:3)

✔ " እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 12:49)

✔" እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና።"
(የዮሐንስ ወንጌል 5:30)

✔ " ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው። ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም፤"
(የዮሐንስ ወንጌል 7:16)

5- እየሱስ ክርስቶስ የተላከው ለእስራኤላውያን ጎሳ እንጅ ለዓለም ህዝብ አልነበረም፡፡

" እየሱስም መልሶ። እኔ ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 15:24)

6- እየሱስ መልካም ተብሎ መጠራትን አልፈልገም ነበር ምክንያቱም መልካም የሚባለው አምላክ ብቻ ነውና‼

" እርሱም። ስለ መልካም ነገር ለምን ትጠይቀኛለህ? መልካም የሆነ አንድ ነው፤ ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ አለው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 19:17)

7- እየሱስ በራሱ አቅም ማንንም ማዳን አይችልም ነበር፡፡

" እርሱም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት፤"
(ወደ ዕብራውያን 5:7)

በዚህ አንቀፅ እንደምንመለከተው እየሱስ ሲጨንቀው ፊቱን ያዞረው ሊያድነው ወደሚችል አካል ነበር እንጅ እራሱ አዳኝ ቢሆን መጠየቅ ባላስፈለገው ነበር፡፡

8- በእየሱስ ጊዜ የነበሩና በእርሱ ያመኑ ሰዎች እርሱ አምላክ መሆኑን አያምኑም ነበር፡፡

(የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 16)
----------
13፤ ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ።

14፤ እነርሱም። አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት።

9- አምላክ ከሴት ማህፀን ተወልዷል ብለው ያምናሉ? ምን ይሄ ብቻ ከዚያም ጡት ጠብቶ ምግብ በልቶ ተፀዳድቶ ኑሯል ብለው ያምናሉ? እውን የአምላክ ባህሪ ይሄ ነውን?
አላህ ከዚህ ቅጥፈት ይጠብቀን፡፡

10- እየሱስ እያለቀሰ አምላኩን በልመና ይገዛ ነበር፡፡

(የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 26)
----------
36፤ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ጌቴሴማኒ ወደምትባል ስፍራ መጣ ደቀ መዛሙርቱንም። ወዲያ ሄጄ ስጸልይ ሳለ በዚህ ተቀመጡ አላቸው።

37፤ ጴጥሮስንም ሁለቱንም የዘብዴዎስን ልጆች ወስዶ ሊያዝን ሊተክዝም ጀመር።

38፤ ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ አዘነች፤ በዚህ ቆዩ ከእኔም ጋር ትጉ አላቸው።

39፤ ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በፊቱ ወደቀና ሲጸልይ። አባቴ፥ ቢቻልስ፥ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ፤ ነገር ግን አንተ እንደምትወድ ይሁን እንጂ እኔ እንደምወድ አይሁን አለ።
https://www.facebook.com/profile.php?id=100064506050455 ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic

ታዲያ እየሱስን ያመልካሉ ወይንስ እየሱስ ያመለከውን ብቸኛ አምላክ ያመልካሉ?

ፍርዱን ለርስዎ = ለህሊናዎ

እየሱስ አምላክ ላለመሆኑ ምስክር ከሚሆኑ ነገሮች ውስጥ አንዱ እና ዋነኛው እየሱስ በራሱ አንደበት " " ብሎ መናገሩ ነው፡፡ከዚህ በታች ያሉትን የወንጌል ጥቅሶች አንብቡና ለህሊናችሁ መልስ ስ...
04/07/2023

እየሱስ አምላክ ላለመሆኑ ምስክር ከሚሆኑ ነገሮች ውስጥ አንዱ እና ዋነኛው እየሱስ በራሱ አንደበት " " ብሎ መናገሩ ነው፡፡

ከዚህ በታች ያሉትን የወንጌል ጥቅሶች አንብቡና
ለህሊናችሁ መልስ ስጡት👇
👇 ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic
➊. ኢየሱስም ገና ወደኣባቴ ኣረግሁምና ኣትንኪኝ, ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ,እኔ ወደ ኣባቴና ወደ ኣባታችሀ ወደ #ኣምላኬና ወደ ኣምላካችሁ ኣርጋለሁ ብለሽ ንገሪያቸው ኣላት”
( የዬሐንስ ወንጌል 20:17)

እየሱስ አምላክ ከሆነ እንደት #ወደ አምላኬ ብሎ ይናገራል? በእርግጥም እሱ አምላክ ከሆነ ወደ ሰማይ ሲያርግም በሰማይ አምላክ እንዳለው እንደት ሊናገር ቻለ?

➋. በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ,ኢሎሄ ኢሌሄ ላማሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ ትርጓሜውም ” #ኣምላኬ #ኣምላኬ ለምን
ተዉከኝ? ማለት ነው”
( ማርቆስ ወንጌል 15:34)

እየሱስ እውነት አምላክ ከሆነ እንዴት #አምላኬ ይላል? ሁለት አምላክ አለን?

➌. እየሱስም መልሶ እንዲህ ኣለው,ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ,እስራኤል ሆይ ስማ ጌታ #ኣምላካችን 1 ጌታ ነው”
( ማርቆስ 12:29)

እየሱስ አምላክ ከሆነ ለምን አምላካችሁ አላለም? ለምን እሱስ አምላክ እንዳለው ተናገረ?

➍. እውነተኛ ኣምላክ ብቻ የሆንክ አንተን የላክኸውንም እየሱስ ክርስቶስ ያውቁ ዘንድ ይህቺ የዘላለም ሂወት ናት”
( የዬሐንስ ወንጌል 17:3)

እየሱስ አንድ አምላክ #ብቻ የሆንከው አንተ ነህ ፡ አንተ ብቻ ነህ አምላክ እኔ የተላኩኝ መልክተኛህ ነኝ እያለ ለምን ክርስቲያኖች በተቃራኒው አንተ አምላክ እንጂ መልዕክተኛ አይደለህም አሉት?

➎. " ኢየሱስም ጮኸ፥ እንዲህም አለ። በእኔ የሚያምን በላከኝ ማመኑ ነው እንጂ በእኔ #አይደለም፤"
(የዮሐንስ ወንጌል 12:44)

እየሱስ ሲናገር እኔን መከተል ማለት የላከኝን አምላክ መከተል እንጂ እኔን ማምለክ አይደለም እያለ እየተናገረ ምነው ክርስቲያኖች ያለቦታው ቦታ ሰጥተው ከፍ አድርገው እሱኑ ተገዙት?

➏. " ኢየሱስም። ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።"
(የማርቆስ ወንጌል 10:18)

እየሱስ ቸር መባል እንኳ አልፈልግም እሱ የአምላክ መጠሪያ ነው ካለ፡ ምነው ታዳ ክርስቲያኖች ከእየሱስ አስተምህሮ ውጭ ሆነው ያለቦታው ቦታ ሰጥተው እየሱስን ቸር በማለት ተገዙት?

➐. “እኔ #ከራሴ ኣንዳች ላደርግ #አይቻለኝም እንደሰማሁ እፈርዳሎ ፍርዴም ቅን ነው የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን ኣልሻምና”
( የዬሐንስ ወንጌል 5:30)

የራሱ ስልጣን የሌለው ፍጡር እንደት አምላክ ነህ ተብሎ ይመለካል? ኧረ እናስብ ሰወች!!

➑. "እየሱስም አለ:- ባሪያ ከጌታዉ አይበልጥም መልክተኛም ከላከዉ #አይበልጥም፡፡
(ዩሀንስ 13:16)

እየሱስ እኔ መልዕክተኛ ነኝ ፡ መልዕክተኛ ደግሞ ከላከው ከአምላኩ አይበልጥም እያለ በይፋ እየተናገረ እንደት ክርስቲያኖች አንተ እራስህ አምላክ ነህ ካንተ በላይ ማንም የለም በማለት በተቃራኒው ተረዱት?

➒. ""ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰኣት ግን የሰማይ መላእክትም ልጅም ቢሆን ከኣብ በቀር የሚያውቅ የለም"
(ማርቆስ ወንጌል 13፡32)

እየሱስ የትንሳዔ ቀን መቼ እንደሆነ አላውቅም እያለን ነው፡፡ እሷን የሚያውቀው አንድ አምላክ ብቻ ነው እኔ አላውቅም እያለ እንደት ክርስቲያኖች እየሱስ ሁሉን አዋቂ ጌታ ነው ብለው ሊያመልኩት ቻሉ?

ሁሉን የማያውቅ አምላክ አምላክ ይሆናልን? አስቡበት!!

➓. "የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ #አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ"
(ኤፌ 1፡17)

👇👇👇👇 👇👇
ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic https://www.facebook.com/profile.php?id=100064506050455 ዶ/ር ዛኪር ናይክ - peace tv amharic
👆 Click &👆Follow 👆Follow👆👆

Address

London Colney
926

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jesus Is Muslim posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share