St Aresma Ethiopian Orthodox Tewahido Church

St Aresma Ethiopian Orthodox Tewahido Church Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from St Aresma Ethiopian Orthodox Tewahido Church, Religious Center, 20 Eaglesham Place, Glasgow.

*በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን* በግላስጎ እና አካባቢዋ ለምትገኙ የእግዚያብሔር ቤተሰቦች የቅድስት አርሴማ ወዳጆች ሰላመ እግዚአብሔር  ከሁላችንም ጋራ ይሁንና  የፊታች...
31/05/2024

*በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን*
በግላስጎ እና አካባቢዋ ለምትገኙ የእግዚያብሔር ቤተሰቦች የቅድስት አርሴማ ወዳጆች ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋራ ይሁንና የፊታችን *ቅዳሜ* እንደ ኢትዮጵያ ቀን አቆጣጠር *24/09/2016* በዚህ ሀገር አቆጣጠር *01/06/2024*_* ከጠዋቱ *6::00* ሰዓት ጀምሮ ስርዓተ ቅዳሴ እንዲሁም ሰፋ ያለ ትምህርት በመምህር ያረጋል አበጋዝ ይኖረናል። ሁላችንም ተገኝተን የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።
*ከግላስጎ ወጪ ከሩቅ ለምትመጡ ምእመናን የምታድሩበት ማረፊያ ቤት የተዘጋጀ ስለሆነ ከታች ባለው የስልክ ቁጥር በመደወል ማረፊያ ቦታ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡*

*አገልግሎቱ የሚደረግበት ቤ/ክ አድራሻ*
St Enochs Hogganfield parish church
860 Cumbernauld Rd,
Glasgow
G33 2QW

የባስ ቁጥር.38,38A, 38C from city center direction to East ይህንን ባስ ቁጥር የምታገኙት ከ Hope street ከ City college ከ Gorge Square የምትወርዱት Dinart Street

ለበለጠ መረጃ በእነዚህ ስልክ ቁጥር ይደውሉ

07496724623,
075383658884

እንኳን ለአምላካችን ለእየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በሰላም አደረሳችሁ!Happy Easter!
16/04/2023

እንኳን ለአምላካችን ለእየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በሰላም አደረሳችሁ!
Happy Easter!

🌿🌿🌿"ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳዒሁ                 ለአምላከ ጽድቅ፣ ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዐቀብ                 ሀገረ እግዚአብሔር፤ ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃ...
12/04/2020

🌿🌿🌿"ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳዒሁ
ለአምላከ ጽድቅ፣ ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዐቀብ
ሀገረ እግዚአብሔር፤ ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃት
አእሩግ ወሕጻናት፣ ነሲዖሙ አዕፁቀ በቀልት፤
እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም ተጽዒኖ ዲበ
ዕዋል፣ ቦዓ ሀገረ ኢየሩሳሌም፣ በትፍስሕት
ወበሐሴት ይሁቦሙ ኃይለ ወሥልጣነ።"
🌿🌿🌿

(መዝሙር ዘሆሣዕና ሰንበት ዘደረሰ፥ "መዘምር ዘበድርሳን" "ወርእሰ ሊቃውንት" ቅዱስ ያሬድ🐦🐦🐦 )

🌿🌿🌿

❄❄❄"አርኅዉ ኆኀተ መኳንንት"❄❄❄
❄"ይባዕ ንጉሠ ስብሐት፣ ይባዕ አምላከ ምሕረት፤"❄

እንኳን ደስ አላችሁ የተዋህዶ ልጆች 💚 💛 ❤️ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ባለ ኮከቡን የፌደራል ባንዴራ አገደች ።      በምትኩ ከሰር የምታዩት የኖህ ቃልኪዳን የሆነውን ...
22/10/2019

እንኳን ደስ አላችሁ የተዋህዶ ልጆች 💚 💛 ❤️
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ባለ ኮከቡን የፌደራል ባንዴራ አገደች ።
በምትኩ ከሰር የምታዩት የኖህ ቃልኪዳን የሆነውን የመላእክትና የወንጌል ስዕል ያለበትን አርማ አስቀምጣለች ።
ከዛሬ ጀምሮ ባለ ኮኮቡ ባንዴራም ሆነ የክልሎች ባንዴራ በየትኛውም የቤተክርስቲያኒቷ በዓል ላይ እንዳይውለበለብ አውግዛለች ።

† በኢትዮጵያ ውስጥ በየትኛውም ክልል እንዲሁም ከኢትዮጵያ ውጭ ባሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ከእንግዲህ መደቡ አረንጓዴ፣ቢጫ፣ቀይ ሆኖ በመሃሉ በትረ ሙሴና ቅዱስ ወንጌል በቅዱሳን መላዕክት ተይዞ የሚታይበት ዓርማ ያለበት ሰንደቅ ዓላማ ብቻ ከፍ ብሎ እንዲታይ ቤተክርስቲያኒቱ በጽኑ አቋም ውሳኔዋን አስተላልፋለች።†

† የአርማው ትርጉም ኢትዮጵያ ጥንት በሕገ ኦሪት ኋላም በሕገ ወንጌል እግዚአብሔርን ስታመልክ የኖረች ሀገር መሆኗንና ብሉይን ከአዲስ አጣምራ ይዛ ትውልድን በመንፈሳዊ በረከት ያቆየች ሀገረ እግዚአብሔር መሆኗን የሚገልጽ ነው።†

† ከእንግዲህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሚከበሩ መንፈሳዊና ብሔራዊ በዓላት በሙሉ ይህ ሰንድቅ ዓላማ ብቻ ከፍ ብሎ እንዲታይ ቤተክርስቲያኒቱ ደንግጋለች።ስለሆነም በጥምቀት፣በመስቀልና በሌሎችም መንፈሳዊ በዓላት የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋይ ካህናት፣ሰንበት ተማሪዎችና፣ምዕመናን ይህንን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርገው በነጻነት እንዲያገለግሉ በየትኛውም ክልል ቤተክርስቲያኒቱ ላይ የመንግስት አካላት ጥያቄ እንዳያነሱ ጠንካራ ውሳኔዋን ለመንግሥት አካላት ሁሉ አስተላልፋለች።†

ይህ ሰንደቅ ዓላማ የየትኛውም ብሔር መገለጫ ሳይሆን የአንዲት ኢትዮጵያ ብቸኛው ዓርማ ነው። እነ አቡነ ጴጥሮስ መስዋዕት የሆኑት ለዚህ ሰንደቅ ዓላማ ክብር ነው፣እነ አቡነ ሚካኤል ደማቸው በግፍ የፈሰሰው ስለዚህ ሰንደቅ ዓላማ ክብር ነው።ኢትዮጵያውያን አርበኞች ወራሪ ጠላትን በዱር በገደል እየተፋለሙ ሀገርን ከነድንበሩ፣ ነጻነትን ከነክብሩ ለትውልድ ያወረሱት ይህንን ሰንደቅ ዓላማ ከፊት አስቀድመው በከፈሉት የደም መስዋዕትነት ነው።ሰንደቅ ዓላማው የሚወክለው ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ነው።ስለሆነም በኢትዮጵያ ውስጥ ፓለቲካ በተለዋወጠ ቁጥር ማንም እንዳሻው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ይለዋወጥ እያለ ታሪካዊ ስህተት በመፈጸም ትውልድን ሲያስት መኖር ስለሌለበት የሀገር ባለ አደራ የሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከእንግዲህ በጽኑ አቋም ባንዲራዋ እንዳይለወጥ ውሳኔዋን አስተላልፋለች።በዚህም መሠረት ለጊዜው አስር ሺ ሰንደቅ ዓላማዎችን አዘጋጅታ አዲስ አበባ ባሉ አብያተ ክርስቲያናትና በሌሎችም ቦታዎች እንዲውለበለብ አሰራጭታለች።በቀጣይም በየክልሉ ያሉ አኅጉረ ስብከቶች እያዘጋጁ በመላው አጥቢያ ቤተክርስቲያን በገዳማትና በአድባራት ሁሉ እንዲያስተላልፉ ጥብቅ መመሪያ ቤተክርስቲያኒቱ አስተላልፋለች።

የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር የኢትዮጵያን ትንሣኤ ያሳየን።



✝ ✝

❇️፩.

፩. መደቡ ነጭ
፪. ዙሪያው የስንዴ ዛላና የወይን ዘለላ
፫. ከላይ ከአናቱ አክሊል፤ ከታች ከግርጌው መሐል
ለመሐል ወጥቶ አናቱ ከአክሊሉ ሥር የደረሰና መስቀል
ያለበት አርዌ ብርት
፬. በግራ ኹኖ በቀኝ እጁ አርዌ ብርት፤ በግራ እጁ
ዘንባባ የያዘ መልአክ፤ በቀኝ ኹኖ በግራ እጁ አርዌ ብርት
በቀኝ እጁ ዘንባባ የያዘ መልአክ
፭. ከአርዌ ብርቱ ሥር “ነዋ ወንጌለ መንግሥት”
ተብሎ የተጻፈበት ቅዱስ መጽሐፍ
፮. ከቅዱስ መጽሐፍ ሥር መስቀለኛ የ”ጸ” ፊደል
ቅርፅን የሚመስል፤ ኹለቱ ጫፎቹ ከመደቡ ወደ ውጭ
የወጣ ሰበን፤
፯. የስንዴ ዛላና የወይን ዘለላ በተገናኙበት የዓለም
ምስል፤ ያለበት ይኾናል፡፡

❇️፪.

ሀ•

ዘመነ ሥጋዌ የምሕረት የደስታና የነፃነት ዘመን መኾኑን
ያመለክታል።
(ዮሐ.፳፥፲፪፤ የሐዋ. ሥራ ፩፥፲)

ለ•

ምእመናን በቅዱስ ቊርባን አማካይነት ከእግዚአብሔር
ጋር አንድነትን፣ ስርየተ ኃጢአትን፣ የዘለዓለም ሕይወትን
የሚያገኙ መኾናቸውን ይገልጻል።
(ዮሐ. ፮፥ ፶፫-፶፰፤ ማቴ. ፳፮፥፳፮-፳፱፤ መዝ. ፬፥፯)

ሐ•



ሕዝበ እስራኤል ዓርዌ ብርቱን ባዩ ጊዜ ከእባብ መርዝ
እንደ ዳኑ ኹሉ መስቀል ላይ በተሰቀለ በጌታችን
በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑ
ኹሉ በዲያቢሎስ ምክንያት ከመጣባቸው ፍዳ ኃጢአት
የሚድኑ መኾናቸውን መስቀሉ የቤተ ክርስቲያን የድኅነት
ዓርማ መኾኑን።
(ዘኍ. ፳፩፥፰፤ ዮሐ. ፫፥፲፬)
መ• #አክሊል

ቅዱሳን በሰማያዊ መንግሥት የሚቀዳጁትን አክሊለ
ክብር እና ማኅተመ ጽድቅን ያመለከታል።
(ዘጸ. ፴፱፥፴፤ ፩ተሰ. ፪፥፲፱፤ ፪ጢሞ. ፬፥፰፤ ፩ጴጥ.
፭፥፲፬፤ ራእይ ፪፥፲፤ ፬፥፲፬)

ሠ•

በመንፈስ ቅዱስ የሚገኝ መንፈሳዊ ደስታንና ድኅነተ ነፍስን
ያመለክታል ቅዱሳን መላእክት የቤተ ክርስቲያን
ጠባቂዎችና የመልካም ዜና አብሣሪዎች መኾናቸውን
ያሳያል ዓርዌ ብርቱን ይዘው መቆማቸው ነገረ መስቀሉን
አምኖና ሃይማኖቱን አጽንቶ ይዞ የሚኖር የዘለዓለም
ድኅነትን የሚያገኝ መኾኑን ያመለክታል።
(መዝ. ፺፥፲፩፤ ሉቃ. ፲፫፥፮-፱፤ ዕብ. ፩፥፲፬)
ረ• ፥
“ ” የሚል ጽሑፍ በበላዩ አለበት የዚኽ ትርጉም

የቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖት ቀኖና እና ትውፊት በቅዱስ
መጽሐፍ ትምህርት ላይ የተመሠረተ መኾኑን ያመለክታል፡፡
(ማቴ. ፳፬፥፲፬)

ሰ• ነገር፥ ዓለምን የሚወክል ኾኖ ዓለም
በክርስቶስ መዳኑን ያመለክታል፡፡
(ዮሐ. ፫፥፲፯)

❇️፫. #የዓርማው #ክብር
ሀ• #ዓርማው

የቤተክርስቲያኒቱ ሉዓላዊ ክብር መገለጫ ስለኾነ በሀገር
ውስጥም ኾነ በውጭ ሀገር የሚገኙ ቤተክርስቲያን
መዋቅር /ቤቶች ከዚኽ ዓርማ በቀር ሊጠቀሙ
አይችሉም፡፡

ለ• የቤተ ክርስቲያኒቱ አካል ደብዳቤ ኾኖ ይህ ዓርማ
የሌለበት ማኅተምና የማዘዣ የሚጠቀም ማንኛውም
የቤተ ክርስቲያኒቱ ጽ/ቤት ተቀባይነት አይኖረውም፡፡

ውስበአት ለእግዚአብሔር !

💚💛❤️

10/10/2019

Address

20 Eaglesham Place
Glasgow
G511PS

Opening Hours

1pm - 7pm

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when St Aresma Ethiopian Orthodox Tewahido Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share