Abershyerufaellij

Abershyerufaellij official.Abershyerufaellij

🔵 ቁልቢ ገብርኤል ገዳም አመሠራረት🔵 ♦♦ቁልቢ ገብርኤል ከአዲስ አበባ በስተም ሥራቅ 461 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጋራ ሙለታ የሚገኝ ከተመሰረተ ጀምሮ ብዙዎቹን እን...
16/07/2025

🔵 ቁልቢ ገብርኤል ገዳም አመሠራረት🔵

♦♦ቁልቢ ገብርኤል ከአዲስ አበባ በስተም ሥራቅ 461 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጋራ ሙለታ የሚገኝ ከተመሰረተ ጀምሮ ብዙዎቹን እንቆቅልሸ የፈተ ቤተ ክርስ ቲያን ነው፡፡

♦♦በዘጠነኛው ክፍለ ዘመነ ዮዲት ጉዲት ተነሥታ አብያተ ክርስቲያናትን ስትመዘብር፣ ክርስቲያኖችን ስትገድልና መጻሕፍትን ስትቆ ነጻጽል ንጉሥ አንበሣ ውድም በአኩስም እና በአከባቢዋ የነበሩ ታቦታትንና ንዋያተ ቅዱሳትን በመያዝ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ወደ ዝዋይ መጣ፡፡

♦♦ከ40 ዓመታት ስደት በኋላ አንበሣ ውድም ወደ አኵሱም ሲመለስና ንዋያ ቅዱሳት ቆጠራ ሲደረግ ታቦተ ቅዱስ ገብርኤል በዝዋይ መቅረቱ ታወቀ፡፡

♦♦ከኤርትራ ደብረ ሲና ማርያም የመጡና አባ ሌዊ የተባሉ አባት ታቦቱን ለማምጣት ከን ጉሡ አስፈቅደው ወደ ዝዋይ መጡ፡፡

♦♦አባ ሌዊ ከሰባት ቀን ሱባኤ በኋላ ታቦተ ቅዱስ ገብርኤልን ይዘው ወደ አኵሱም ሲጓዙ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጦ “እኔ ወደ ማሳይህ ቦታ ታቦቱን ይዘህ ሂድ” አላቸው፡፡ አባ ሌዊም ታቦቱን ይዘው ተከተሉት፡፡ በመጨረሻም ቁልቢ ደረሱ፡፡

♦♦ለአባ ሌዊም የተፈቀደላቸው ቦታ ይሄ መሆኑን ታቦቱም በኋላ ዘመን ለሕዝቡ ድንቅ ሥራ እንደሚሠራ ቅዱስ ገብርኤል ነግሯቸው ተሰወረ፡፡

♦♦እሳቸውም ስለታቦቱ ታሪክ ታቦቱ በፍታ ላይ ጽፈው አባ ሌዊ በቦታው ለ130 ዓመታት ያህል አገልግለው በንጉሥ ግርማ ሥዩም ዘመነ መንግሥተ ታኅሳስ 14 ቀን ዐርፈዋል፡፡

♦♦ቱርካዊው ግራኝ አሕመድ ወረራ ዘመን ካህናት ንዋያተ ቅዱሳትን ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ለመጋዝ ተነሱ።ሸዋ ሲደርሱ ታቦተ ገብርኤል አልንቀሳቀስም አለ።

♦♦ካህናቱም ስለገብርኤል ታቦት በበፍታ ላይ የተጻውን እና ሸዋ መቀመጡን ይዘውት በነበረው መጽሐፈ ቀሌ ሜንጦስ ሕዳግ ላይ ጻፉት፡፡መጽሐፉን ዝዋይ ደሴት አስቀምጠውት ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡...........................................................

♦♦ይህ እንዲህ እንዳለ በዝዋይ ደሴት በመጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ያለውን የገብርኤልን ታቦት ታሪክ ያነበበ ሰዎች ለሐረር ገዥ ለነበሩት ለራስ መኰነን ነገሯቸው።

♦♦ራስ መኮንን የሰሙት ገብርኤል ታቦት ታሪክ ልባቸውን ተካናና"ገብርኤል ሆይ! ይህን ደም አፋሳሽ የጎሳዎች ግጭት ካስወገድክልኝ፤ በዚህ ደም አፋሳሽ ቦታ በስምክ ቤተክርስትያን አሰራልሀለው!"ብለው ተሳሉ።

" በአፍህ የተናገርኸውን ለአምላክህ ለእግዚአብሔር በፈቃድህ ተስለሃልና ከከንፈርህ የወጣውን ታደርግ ዘንድ ጠብቅ። "
(ኦሪት ዘዳግም 23:23)

♦♦ልዑል ራስ መኮንን ይህን ስለት ሊሳሉ የቻሉት የሐረር አውራጃ አስተዳዳሪ ሆነው ሳሉ የሐረር ጎሳዎች ዘወትር ውጊያ የሚገጥሙበት ብዙ ደም የሚፈስበት አንድ ደም አፋሳሽ ቦታ ስለነበረ ነው።......................................................

♦♦ለወዳጆቹ ፈጣን ሆነው ቅ/ስ ገብርኤል ራስ መኮንን ስለትን ሰምቶ የተለመደ ጎሳዎች ግጭትን አቁሞ በቦታው ሰላም አመጣላቸው።

♦♦ተሳሉት ተፈጸመላቸው ራስ መኮንንም የቅዱስ ገብርኤል ታቦት የት እንዳለ ሲያፈላልጉ ቡልጋ ውስጥ ከአዠጉጉ ካህናተ ሰማይ ጋር አባ ዱባለ የተባሉ ካህን ያስቀመጡት ታቦተ ቅዱስ ገብርኤል መኖሩ ተነገራቸው፡፡

♦♦ልዑል ራስ መኰንን አባ ዱባለ መልእ ክት ስለላኩባቸው ከሐረር በተላኩ ካህናት አማካኝነት የቅዱስ ገብርኤልን ታቦት ላኩ፡፡

♦♦ልዑል ራስ መኰንን ከነሠራዊቶ ቻቸው ሸንኮራ ድረስ ሄደው ታቦቱን በመቀበል የካቲት 21 ቀን 1884 ዓ.ም ታቦቱ ቁልቢ ገባ፡፡

♦♦የመቃኞው ሥራ በ1883 ዓ.ም

ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ቁልቢ ገብርኤልበስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!!!ከፊታችን በታላቅ ድምቀት የሚከበረውን የ ታላቁን መልአክ የ ቅዱስ ገብርኤልን በአል ለማክበር ...
07/07/2025

ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ቁልቢ ገብርኤል

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!!!

ከፊታችን በታላቅ ድምቀት የሚከበረውን የ ታላቁን መልአክ የ ቅዱስ ገብርኤልን በአል ለማክበር ማህበራችን ጉዞ አዘጋጅቷል

የጉዞ መነሻ ታህሳስ 17
የጉዞ መመለሻ ታህሳስ 20

ያሉን በጣም ውስን ወንበሮች ስለሆኑ ቀድመው ቦታ ያሲዙ

0910714747
0970063432
0912163200

የዐቢይ ጾም የመጨረሻ     ጉዞበዓለ ሆሳዕናን በኩክ የለሽ ማሪያም ገዳም ሁላችሁም ተጋብዛችኋል ጉዞ ለመመዝገብ 0910714747/0970063432 እየደወላችሁ ተመዝገቡ
08/04/2025

የዐቢይ ጾም የመጨረሻ
ጉዞ

በዓለ ሆሳዕናን በኩክ የለሽ ማሪያም ገዳም ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
ጉዞ ለመመዝገብ
0910714747/0970063432 እየደወላችሁ ተመዝገቡ

ምስክርነት እልል🙏🙏🙏ከ 2007ጀምሮ ይጥለኝ ነበር ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል ምግብ ስበላ አንደበቴን ይይዘኛል 2009ሸንቁሮ ሚካኤል ሄድኩ ከብዙ ህመም ድኛለው ሚጥለው ግን በመዳኒት ሀይል ሆነ 9 ...
22/03/2025

ምስክርነት እልል🙏🙏🙏

ከ 2007ጀምሮ ይጥለኝ ነበር ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል ምግብ ስበላ አንደበቴን ይይዘኛል 2009ሸንቁሮ ሚካኤል ሄድኩ ከብዙ ህመም ድኛለው ሚጥለው ግን በመዳኒት ሀይል ሆነ 9 አመት በመዳኒት እገዛ አምና 16 ሠሚነሽ ብድግ ብዬ ሄድኩ ከሞት ያዳነችኝ እናቴ ከበሽታማ ትምረኛለች።
ዶክተሮች ከዚ እንዳይከፋ ማድረግ አንጂ መዳን አትችዪም ተብዬ የነበረው
አሁን ሙሉ ምርመራ አድርጌ ምንም የለም ደና ነሽ የበፊቱ ጉዳት ጠባሳ ብቻ ነው ተባልኩ መቼም አታቆሚም የተባልኩትን መዳኒት ከወራቶች በዋላ እንደማቆም ተነገረኝ አናቴ የኪዳነምሕረት
ለኔ የደረሰች ለናንተም ትድረስላችሁ🙏🙏🙏

ይህን መልክት የኪዳነምህረት ወዳጆች ሁላችሁ ሼር በማድረግ ሰሚነሽ ኪዳነምህረትን ለዓለም አሳውቁ ለተቸገሩ ሁሉ መፍትሄ ነች።
☎️0910714747
☎️0970063432

ምስክርነት!!!ሱስ እንደ ቀልድ ለሙድ ለጨዋታ ብዬ ነበር የጀመርኩት ግን በዛው በጣም ስር እየሰደደ መጥቶ ትምህርቴን እዳልቀጥል አርጎኝ ትምህርቴን ተውኩት።  ከዛ በኋላም የራሴን ስራ መስራት...
08/03/2025

ምስክርነት!!!

ሱስ እንደ ቀልድ ለሙድ ለጨዋታ ብዬ ነበር የጀመርኩት ግን በዛው በጣም ስር እየሰደደ መጥቶ ትምህርቴን እዳልቀጥል አርጎኝ ትምህርቴን ተውኩት። ከዛ በኋላም የራሴን ስራ መስራት ጀመርኩኝ ግን እየሰራውም ምንም እጄ ላይ ገንዘብ ሊቀመጥ አልቻለም። እሰራለው ለመጠጥ ነው እሰራለው ለጫት ነው በቃ ምንም ጠብ የሚል ነገር የለም ስፈልግ እሰራለው ስፈልግ እጠጣለው በቃ በአጭሩ እግዚአብሔርን እረሳው ልቤ አበጠ ማንም እነደኔ ያለም አይመስለኝ። ከእናቴ ከቤተሰቦቼ ሁሉ እራኩኝ በቃ ያ እንደ ቀልድ የጀመርኩት ሱስ ነገሰብኝ እና ምሰራውንም ስራ አጣውት ከብዙ አደጋዎችም ተርፌያለው እግዚአብሔር እንደኔ በደል ሳይሆን እነደ እርሱ ቸርነት አልተወኝም እንጂ በጣም ከመጥፎ አደጋዎች ተርፌያለው።

የምሞክረው የምሰራው ሁሉ ለሱሴ ስለነበር ምንም ነገር አልያዝ አልጨበጥ አለኝ በጣም ብዙ ብዙ ነገር አሳጥቶኛል እደዚህ በቃል ቢነገር የማያልቅ ነገሮችን አሳጥቶኛል።
ነገሮች ከአቅሜ በላይ ሲሆንብኝ ግን ያለፈውን የፍስለታ ፆም መጥቼ እዚሁ ሰሚነሽ ደጅ ሱባኤ ያስኩኝ እና መፆም መፀለይ መጠመቅ ጀመርኩኝ በሶስተኛው ቀን አንድ ወንድም አውደ ምህረት ላይ ቆሞ ምስክርነት መስጠት ጀመረ እራሴ ያሳለፍኩትን ህይወት ቃል በቃል ሰማውት ምስክርነቱም ከሱስ ህይወት መውጣቱን ኪዳነምህረትን ለምኛት ከዛ ሁሉ የጨለማ ህይወት የሱስ ህይወት አውጥታኝ አሁን ሁሉም ነገር አዲስ ሆኖ ቆሜ ለመመስከር በቅቻለው የሚል ምስክርነት ነው።

እንባዬ ኬት መጣ ሳልለው ዱብ ዱብ ማለት ጀመረ ልቤ በጣም አዘነ ጭራሽ በቃ ስቅስቅ እያልኩኝ ማልቀስ ቀጠልኩኝ ግን በልቤ እደው ኪዳነምህረት እኔንስ መቼ ነው ለዚህ ምስክርነት ምታበቂኝ ከጨለማ ህይወት ከሱስ ህይወት አውጥተሽ እንደዚህ ለምስጋና ምታበቂኝ እያልኩኝ እደነበር አስታውሳለው ለቅሶዬ ግን ሊቆም አልቻለም ነበር።

ከዛ ምስክርነቱም አለቀ ከዛ ጉባኤያችንም አለቀ እንዴት እደዛ እዳለቀስኩኝ እደዛ ልሆን እደቻልኩኝ ገርሞኝ ወደ ማረፋያዬ ገባው። ከዛ ሱባኤውም ፆሙም በሰላም ጨርሰን ወጣው።

ይህው አሁን ለ10 አመታት ሙሉ ልጅነቴን ወጣትነቴን እዳልሰራ እዳላድግ እዳልለወጥ አድርጎ አስቀርቶኝ የነበረውን ሱስ ከኔ ጋር ዳግም ላይመለስ ተነቅሎ ወቶልኛል አዲስ ህይወት ጀምርያለው አዲስ ብርሀን ወቶልኝ ከሱሰ የፀዳ ህይወት አያሳለፍኩኝ ነው።
ለኔ የደረሰች እመብርሃን እኔን ከስቃይ ያወጣች ኪዳነምህረት የኔን የ 2 ደቂቃ እንባ አይታ ከዛ ሁሉ ከጨለማ ህይወት ከዳቢሎስ እስራት ያወጣችኝ ልደታ ማርያም የሁላቹንም ፀሎት ትስማቹ እንባቹን ታብስላቹ።

እግዚአብሔር ይመስገን።

ይህን መልክት የኪዳነምህረት ወዳጆች ሁላችሁ ሼር በማድረግ ሰሚነሽ ኪዳነምህረትን ለዓለም አሳውቁ ለተቸገሩ ሁሉ መፍትሄ ነች።
☎️0910714747
☎️0970063432

05/03/2025
እናቴ ሰሚነሽ ያደረገቺልኝ ብዙ ነዉ።የአመቷ ኪዳነምህረት ለት 16/06/2013 ለስራ አፕላይ አድርጌ እናቴ አንቺ ባርኪዉ ብዬ ቅዳሜ ቀን ጓደኛዬ በየማር ፀበል የሚሰጥበት ቀን ቀድመን ለመሔድ...
03/03/2025

እናቴ ሰሚነሽ ያደረገቺልኝ ብዙ ነዉ።
የአመቷ ኪዳነምህረት ለት 16/06/2013 ለስራ አፕላይ አድርጌ እናቴ አንቺ ባርኪዉ ብዬ ቅዳሜ ቀን ጓደኛዬ በየማር ፀበል የሚሰጥበት ቀን ቀድመን ለመሔድ ተነጋግረን በጠፈጥሮ ጉዳይ እኔ ቀርቼ እሱ ሄደ ሲሄድ ፀልይልኝ ብዬዉ እሱ ሄደ። የእዛኑ ቀን አፕላይ ካደረኩበት መስሪያ ቤት ተደወለልኝ። መደወሉን ልነግረዉ ስደዉል ገና መግባቱ እንደሆነ ነገረኝ ገና እግሩ ደጇን ሲረግጥ መልስ ሰጠቺኝ።
ጓደኛዬም የዛሬ አመት የማር ፀበል በሚሰጥበት ቀን ሄዶ በሳምንቱ ነዉ ስራ የጀመረዉ የእኔ ፈጥኖ ደራሽ እናቴ የሰጠቺኝን ባርካልኝ ለደጇ አብቅታኝ እንዳመሰግናት ትርዳኝ በቃል ኪዳንዋ ሁላችንንም ታስበን ሀገራችንን ትጠብቅልን

ሰሚነሽ ጭንቀታችሁን ታቅልላችሁ       #ሰሚነሽኪዳነምህረት  #ኦርቶዶክስ  #ተዋህዶ  #ኢትዮጵያ2017
24/02/2025

ሰሚነሽ ጭንቀታችሁን ታቅልላችሁ
#ሰሚነሽኪዳነምህረት #ኦርቶዶክስ #ተዋህዶ #ኢትዮጵያ2017

06/09/2023

Adresse

Paris

Notifications

Soyez le premier à savoir et laissez-nous vous envoyer un courriel lorsque Abershyerufaellij publie des nouvelles et des promotions. Votre adresse e-mail ne sera pas utilisée à d'autres fins, et vous pouvez vous désabonner à tout moment.

Contacter Le Lieu De Culte

Envoyer un message à Abershyerufaellij:

Partager

Type