01/11/2024
ኢየሱስም እንዲህ አላቸው ፦ "እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደኔ ኑ ፤ እኔም አሳርፋችኀለሁ፡፡ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ፤ ከእኔም ተማሩ፤ እኔም የዋህ ፥ በልቤም ትሑት ነኝና ለነፍሳችሁ ዕረፍትን ታገኛላችሁ፡፡ ቀንበሬ ልዝብ፣ ሸክሜም ቀሊል ነውና ፡፡"
ሄሎ ወዳጆቼ፦ እዚህ ጋር ኢየሱስ
እያለ ያለው "ማንም ሸክም የከበደ ቢኖር ወደኔ ይምጣና ይረፍ ፤ ልብ በለኝ ወገኔ ሸክም ከጫንቃህ ሳይወረድ ማረፍ የለም፡፡ ማንም የሒወትን ወይንም የነፍስን ሸክም ከኢየሱስ ውጭ በራሱ ሊያወርደው አይችልም፡፡ በራሱ የሞከረ ሲታገል ኖሮ ሳያርፍ ወደሲዖል ያመራል፡፡ ድምፁን ሰምቶ አምኖ ወደኢየሱስ የመጣ ግን እሱ ታደለ፤ ከመከራም ሥጋት ሁሉ ያርፋል፡፡ ወዳጄ ክርስትና ከማረፍ ነው እሚጀምረው፡፡ ከዚያም አርፈህ በጎልጎታ ላይ ተጨርሶ የቀለለውን ቀንበሩን ተሸክመህ የለዘበውን [የአማረውን] ሸክም ትቀዳጃለህ እንጂ አዲስን ፍልሚያ ሊያጋፍጥህ አይደለም ወደኔ ና ያለህ፡፡ ሲጠራህ እራሱን ተማምኖ መሆኑን ላፍታም አትዘንጋ! ከአመንክ ትከተለዋህ እርሱ በሰበረው ስብርባሪው፣ ባፈረሰውም ፍርስራሹ ላይ ቆመህ ድልን ትጎናፀፋለህ፡፡ አሁንም ላሹፍህ፦ እኔ የዋህ ነኝ ሲልህ አስተውል---- ይህን ዓለም ኢየሱስ የአንበረከከው ሲመቱት ባ ብሎ ሳይሆን ዝም የሚል በሸማቾቹም ፊት ሊታረድ ሲነዳ እያወቀ ዝም የሚል የእግዚአብሔር በግ ሆኖ እንጂ የሰማይ የምድር ንጉስ አንበሣው እኔ ነኝና ይታወቅልኝ ብሎ አግሥቶ አይደለም ፤ ፍቅሩን በተግባር ከውኖት እንጂ፡፡ ትሁት ነኝ ከኔም ተማር ሲልህ፦ የመናገር አባዜ ኖሮት ሳይሆን ኖሮ መናገርን ተናግሮ መኖርን ስላወቀበት ነው፡፡ እይ፦ እንደባሪያ እራሱን ዝቅ አድርጎ ጌታቸው የነበረ ኢየሱስ የደቀ መዛሙርቱን እግራቸውን ሲያጥብ፡፡ ንጉሳቸው -- እግራቸውን ፡፡ የሰማይ የምድር የሁሉ ፈጣሪ --- እግራቸውን፡፡ ወገኔ፦ ትልቅ መሆን፣ ገናና መሆን ፥ ማረፍ ፣ ዝና እንዲኖርህ ትፈልጋለህን?
እስቲ አስተውል! የቱስ ጀግና መሪ ነው እንኳ የመንግሥቱ (የግዛቱ) ሕዝብ ቀርቶ የአንድን ነፍስ ሸክም ወደኔ ና አሳርፍሃለሁ ብሎ ነፍስን የሚያሳርፍ ለዘለዓለምም የሚያድን፡፡ ኢየሱሳችን ግን ነፍሱን ለጠላቱ ቀድሶ አሳልፎ የሰጠ ፤ አልፎም ለዓለም ሁሉ ሕዝብ ሁሉ ወደኔ ኑ ነፍሳችሁ ከዘላለም ሞት ትድናለች ብሎ እየተጣራህ ነው፡፡ ሳይመሽ በቀን ወደሱ ሮጠህ አምልጥ፡፡ ዛሬም ያድናል ይታደግህማል!!! የትኛውም ሸክም የከበደህ ሁልህ ዕረፍትህን ወደሚሻ አባትህ ና!!! እሱ ከማንም በላይ ይወድሃል!!!
እንግዲያውስ፦
1) ከነ ሸክምክ ወደ ኢየሱስ ና!
2) ፈቃዱን ተሸከም
3) የውሃትነትን/ የዋህነትን ከሱ
ተለማመድ
4) ትህትናን ከእሱ ተማር፡፡
የሕይወት ጥያቄ ያለባችሁ ሁሉ
ጥያቄያችሁን በእግዚአብሔር ፊት አምጡት አባታችሁ ነውና የውስጣችሁን ይረዳችኀል ደግሞም ይረዳችኃል ፡፡
( የጣሩ ዋጋ የደሙ ፍሬ ነኝ ፦ አማኑኤል አበበ ፀሐይ)
ያሕዌ ሻሎም ሐብዚሁም!!!