ተስፋሕይወት ሰንበት ት/ቤት TesfaHiwot Sundayschool

ተስፋሕይወት ሰንበት ት/ቤት  TesfaHiwot Sundayschool ይህ በወልቂጤ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተስፋሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት የሚመራ የፌስቡክ ገፅ ነው

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከ10 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ የ101 ዓመት እድሜ ያለው የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።  የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም...
02/06/2026

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከ10 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ የ101 ዓመት እድሜ ያለው የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።

የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል።

ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

እንደ ወትሮው ሁሉ ዛሬም በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ምድር ላይ ታላቅ ሃዘን ላይ ይገኛል። ማቅ የለበሱ እናቶች፣ እንባቸው ያላለቀ ሕፃናት እና ማደሪያ ያጡ አረጋውያን ጩኸት ሰሚ አጥቷል።

ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት፣ አሰኮ ወረዳ፣ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ እና ካራ ኩፍቴና በሚባሉ አካባቢዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠረ አሰቃቂ ግድያ ተፈጽሟል።

ለደኅንነታቸው ሲባል ስማቸውን የማንጠቅሰው የአይን እማኝ እና መረጃ ሰጭያችን እንደገለጹልን ከሆነ፣ ጥቃቱ እጅግ አሳዛኝና አረመኔያዊ እንደነበር ይናገራሉ።

በአሰኮ ወረዳ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ ብቻ በታጣቂ ኃይሎች በተፈጸመ ሰብአዊነት በጎደለው ጥቃት ከ10 በላይ ንጹሃን ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል።

ይህ አሰቃቂ ጥቃት በሰዎች ሕይወት ላይ ብቻ አላበቃም የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የሚፈተትበትን መቅደስም ጭምር ኢላማ ያደረገ ነበር። በአካባቢው 101 ዓመታትን ዕድሜ ያስቆጠረው፣ ታላቁ የዕድሜ ባለጸጋ የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወውደሙን መረጃ ሰጭያችን ገልጸውናል።

በተመሳሳይ ጥቃት በካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ጥቃት የተሰነዘረ ሲሆን፣ የቤተክርስቲያኑ ንብረት የሆኑ ቤቶች በመቃጠላቸው ምእመናን የመድኃኔዓለምን ቅዱስ ጽላት ይዘው በእግራቸው ወደሌላ አካባቢ መሸሻቸው ታውቋል።

ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በሃይማኖታቸው ብቻ ቤታቸው እየተለየ ተቃጥሏል፤ ንብረታቸውና ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል። ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎችም ይዘውት የሸሹት እምነታቸውንና ማንነታቸውን ብቻ በመሆኑ አሁን ላይ ሜዳ ላይ ወድቀው ይገኛሉ ሲሉ ነበር በሃዘን ተውጠው የነገሩን።

በተያያዘ ዜና

በዚሁ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሺርካ ወረዳ በሁለት ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ግድያ መፈጸሙ ተሰምቷል።

ድርጊቱ የተፈጸመው ሚታና ዋጂ ቀበሌ ሲሆን፣ ታጣቂዎች ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ወጣቶቹ መኖሪያ ቤት በመግባት በቁጥጥር ስር እንዳዋሏቸውና በመቀጠልም ወጣቶቹን ወደ ሚታና ጋዶ ቀበሌ በመውሰድ፣ አንደኛውን በስለት አርደው፣ ሁለተኛውን ደግሞ በጥይት በመምታት በጭካኔ ሕይወታቸውን እንዳጠፉት ተገልጿል።

ሕይወታቸውን ያጡት የእነዚህ ወጣቶች ሥርዓተ ቀብር ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በጋዶ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን፣ ምዕመናንና በቤተሰብ በተገኘበት በአንድ መቃብር ተፈጽሟል።

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በአገልጋዮችና ምእመናን ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት እንደሚፈጸምበት ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ለዓመታት መረጃ እያደረሰ ቢሆንም ዛሬም ድረስ ዘላቂ መፍትሔ አልተገኘም።

ምንጭ :- EOTCMK TV


ተስፋሕይወት ሚድያ
(ስለእርሱ የምንናገረው ብዙ ነገር አለን)

በሁሉም ሶሻል ሚድያ ያግኙን :-
https://linktr.ee/Tesfahiwot

ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ ፦
https://tesfahiwot.com

በዓለ ጰራቅሊጦስ በወልቂጤ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከበረብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የቅዱስ ዜና...
01/06/2026

በዓለ ጰራቅሊጦስ በወልቂጤ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከበረ

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ መሥራችና የበላይ ሓላፊ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢ በተገኙበት ግንቦት 23 2018 ዓ.ም በዓለ ጰራቅሊጦስ በወልቂጤ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።

📷 ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚድያ


ተስፋሕይወት ሚድያ
(ስለእርሱ የምንናገረው ብዙ ነገር አለን)

በሁሉም ሶሻል ሚድያ ያግኙን :-
https://linktr.ee/Tesfahiwot

ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ ፦
https://tesfahiwot.com

"የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች...
31/05/2026

"የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫

እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!

የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በጋራ ጉባኤ በአንድነት ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚመክሩበት፣ የትውልዱን መጻኢ ጉዞ የሚተልሙበት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለነገው ትውልድ ሊያሻግሩ የሚችሉ ዐውደ ሐሳቦች ለውይይት የሚቀርቡበት ታላቅ በዓል ነው። ይህ በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ተሰጥቶት በየዓመቱ እየተከናወነ የሚገኘው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ዘንድሮ በሀገራዊ ጉዳይ ምክንያት በመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ደረጃ ጠቅላላ ጉባኤውን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማከናወን ባይችልም በሁሉም አህጉረ ስብከት፣ በየወረዳው እና በየአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ዕለቱ በደማቅ ሁኔታ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ይውላል።

ቅዱስ ጳውሎስ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ብቻ አይደለም ያለን ይህንንም የመንፈስ አንድነት እንዴት መጠበቅ እንዳለብን በመንገርም ጭምር ነው እንጂ። ይኸውም በፍጹም የዋሕነት፤ ራሳችሁን ዝቅ አድርጋችሁ፣ እየታገሣችሁ፣ ለወንድሞቻችሁም እሺ እያላችሁ፣ በፍቅር እየተጋችሁና እየተባበራችሁ በማለት ነው። የአንድነታችንንም ዓላማ እንዳንዘነጋ ሲገልጽልን “ለአንዱ ተስፋችሁ እንደመጠራታችሁ” ይለናል። እኛም የ15ኛ ዓመት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ቀንን ስናከብር ከወትሮ በላቀ የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ መትጋት እንዲገባን ይህን የቅዱስ ጳውሎስን ምክር መርሐችን አድርገናል። ከሁል ጊዜው በላይ ዓለምም ሆነ ሀገራችን እየተጓዘችበት ካለው አስፈሪ የጥፋት ጉዞ ትውልዱን መጠበቅ፣ ማዳንና ማሰማራት የሚቻለው የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ ስንተጋ ብቻ ነው።

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትውልዱን በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ለመጠብቅ የመንፈስን አንድነት መርሕ ይዞ የሚጓዝ መዋቅር ነው። ታዲያ ይህንን አንድነታችንን ከውስጥም ከውጭም ፈተናዎች ለመጠበቅ እየታየ ያለውን በጎ ፍሬ ለማስቀጠል ትጋትን ገንዘብ ልናደርግ ይገባናል እንላለን። ምንም እንኳን በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘንድሮውን ዓለም አቀፋዊ ጠቅላላ ጉባኤያችንን ማከናወን ባንችልም በያለንበት መዋቅር ዕለቱን ልንዘክረው ይገባናል።

እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ

©️ ከመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተወሰደ


ተስፋሕይወት ሚድያ
(ስለእርሱ የምንናገረው ብዙ ነገር አለን)

በሁሉም ሶሻል ሚድያ ያግኙን :-
https://linktr.ee/Tesfahiwot

ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ ፦
https://tesfahiwot.com

እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ በሰላም አደረሳችሁ!​በወልቂጤ ከተማ የምትገኙና በየአቅጣጫው የምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን በሙሉ፤ የቤተክርስቲያናችን የልደት ቀን የሆነውና መንፈስ ቅዱስ ለሐዋ...
30/05/2026

እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ በሰላም አደረሳችሁ!

​በወልቂጤ ከተማ የምትገኙና በየአቅጣጫው የምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን በሙሉ፤ የቤተክርስቲያናችን የልደት ቀን የሆነውና መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደበትን ታላቁን የጴንጤቆስጤ (የጰራቅሊጦስ) በዓል በወልቂጤ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን እሁድ ግንቦት 23 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀትና መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ይከበራል።

ቤተሰቦቻችንንና ወዳጆቻችንን በመያዝ የዚህ ታላቅ በረከት ተካፋይ እንድንሆን ቤተ ክርስቲያን ትጣራለች።

​"ኑና የበረከት ተካፋይ ሁኑ!"

ተስፋሕይወት ሚድያ
(ስለእርሱ የምንናገረው ብዙ ነገር አለን)

በሁሉም ሶሻል ሚድያ ያግኙን :-
https://linktr.ee/Tesfahiwot

ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ ፦
https://tesfahiwot.com

28/05/2026

✨ "ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚያንጽ አይደለም።" (1ኛ ቆሮ. 10፥23) ✨

ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞችየሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት ጉዳይ ክፍል ከማህበረ ቅዱሳን ወልቂጤ ወረዳ ማዕከል ጋር በመተባበር ለ12ኛ ክፍሎች ተፈታኞች  የፀሎት እና የስነ ልቦና ዝግጅት የስል...
25/05/2026

ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች

የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት ጉዳይ ክፍል ከማህበረ ቅዱሳን ወልቂጤ ወረዳ ማዕከል ጋር በመተባበር ለ12ኛ ክፍሎች ተፈታኞች የፀሎት እና የስነ ልቦና ዝግጅት የስልጠና መርሀ ግብር ረቡዕ ግንቦት 19 ከቀኑ 10:00 ሰዓት አዘጋጅቷል ።

ኦርቶዶክሳውያን ተፈታኞች መተው እንዲታደሙ እንጋብዛለን።

በወልቂጤ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተስፋሕይወት ሰ/ት/ቤት


ተስፋሕይወት ሚድያ
(ስለእርሱ የምንናገረው ብዙ ነገር አለን)

በሁሉም ሶሻል ሚድያ ያግኙን :-
https://linktr.ee/Tesfahiwot

ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ ፦
https://tesfahiwot.com

24/05/2026

ሰውን የምናይበት መንገድ

23/05/2026

ነፍሳችንን በኃጢአትና በጭንቀት የጠፈረውን ገመድ እግዚአብሔር አምላክ ይፈታል

"በዚያም ቀን ሸክሙ ከጫንቃህ ቀንበሩም ከዐንገትህ ላይ ይወርዳል ቀንበሩም ከውፍረት የተነሣ ይሰበራል።"
ትንቢተ ኢሳያስ 10 : 27

በወልቂጤ ከተማ በሚገኙ አድባራት ሰንበት ት/ቤቶች የተዘጋጀው ልዩ የኪነጥበብ ምሽት በርካታ ኦርቶዶክሳውያን በተገኙበት በወልቂጤ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተካሄደ።በመርሃግብሩ...
22/05/2026

በወልቂጤ ከተማ በሚገኙ አድባራት ሰንበት ት/ቤቶች የተዘጋጀው ልዩ የኪነጥበብ ምሽት በርካታ ኦርቶዶክሳውያን በተገኙበት በወልቂጤ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተካሄደ።

በመርሃግብሩ
- መዝሙሮች
- መንፈሳዊ ድራማዎች
- ግጥሞች
- ሚያንጹ መንፈሳዊ መልዕክቶች በአራቱም አድባራት ጥምረት ቀርቧል።


ተስፋሕይወት ሚድያ
(ስለእርሱ የምንናገረው ብዙ ነገር አለን)

በሁሉም ሶሻል ሚድያ ያግኙን :-
https://linktr.ee/Tesfahiwot

ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ ፦
https://tesfahiwot.com

ክርስቶስ አምላካችን ዐረገ ማለታችን ከዚያ ከሰማይ የሌለ ሆኖ ከዚህ ከምድር  ወደ ሰማይ ወጣ ሄደ ማለታችን አይደለም።ነገር ግንዕርገቱ (መውጣቱ) አምስት ምሥጢራትን ለማስረዳት የተከናወነ መሆ...
21/05/2026

ክርስቶስ አምላካችን ዐረገ ማለታችን ከዚያ ከሰማይ የሌለ ሆኖ ከዚህ ከምድር ወደ ሰማይ ወጣ ሄደ ማለታችን አይደለም።
ነገር ግን
ዕርገቱ (መውጣቱ) አምስት ምሥጢራትን ለማስረዳት የተከናወነ መሆኑን እንናገራለን።
እነርሱም ፦

#1. ከትንሣኤ በኋላ ዳግም ሞት እንደማይሞት፣ ሕማም እንደሌለበት ለማስረዳት እና ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ፍጹም አንድነቱን ለማስረዳት ዐረገ።

(ነቢረ የማንሰ ያኤምር ኀበ ተዋሕዶቶሙ በክብር እንዲል)

#2. አዳም በበደለ ጊዜ "አፈር ነህ ወደአፈርነትም ትመለሳለህ" ያለውን የሰው ባሕርይ ከምድራዊነት ወደሰማያዊነት ለመለወጡ ትዕምርት (ምልክት) ሊሰጠን ዐፈር ነህ ያለውን ሰማያዊ ሆነሃል ለማለት ዐረገ።

(ዐርገ እግዚእነ ከመያለቡ ዕርገተ ጻድቃን ንጹሐን)

#3. ወረደ ስንል ተወለደ ሰው ሆነ ብለን ተርጉመን ሥራ ጀመረ ማለት ነው እንዳልን ዐረገ ስንልም ሥራውን ጨረሰ ማለታችን ነው።

#4. በአዳም ምድራዊ ሆነን ነበርና በእርሱ በክርስቶስ አምላካችን ሰማያዊ መሆናችንን የዘለዓለም መኖሪያችን በየት እንደሆነ ለማመላከት ዐረገ።

(የዚያንም የመሬታዊውን መልክ እንደ ለበስን የሰማያዊውን መልክ ደግሞ እንለብሳለን።» 1ቆሮ 15 : 48-49)

#5. ሰማያዊ እንደሆነ ለማስረዳት ሥራውን ሠርቶ ከጨረሰ በኋላ ወደሰማይ ሲወጣ ታየ።

(ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።»
— (ዮሐንስ 3፥13)

ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደሰማይ እንዳረገ እናምናለን ደግመኛ ለፍርድ እንደሚመጣም ተስፋ እናደርጋለን።

መልካም በዓል

በመምህር ሳሙኤል ሰሎሞን

Address

Wolkite

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ተስፋሕይወት ሰንበት ት/ቤት TesfaHiwot Sundayschool posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ተስፋሕይወት ሰንበት ት/ቤት TesfaHiwot Sundayschool:

Share