Catholic Eparchy of Emdeber

Catholic Eparchy of Emdeber Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Catholic Eparchy of Emdeber, Catholic Church, Wolkite.

28/04/2026
"ካህናትህ ጽድቅን ይልበሱ፥ ጻድቃንህም ደስ ይበላቸው።"(መዝሙረ ዳዊት 132 : 9)   ሚያዝያ 18/2018ዓ.ም"ካህናቲከ ይለብሱ ጽድቀ"   በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በእምድብር...
26/04/2026

"ካህናትህ ጽድቅን ይልበሱ፥ ጻድቃንህም ደስ ይበላቸው።"
(መዝሙረ ዳዊት 132 : 9)

ሚያዝያ 18/2018ዓ.ም

"ካህናቲከ ይለብሱ ጽድቀ"

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በእምድብር ሀገረስብከት ክቡር አባ ጸጋ ዘአብ የሃያ አምስተኛ (25ኛ) የክህነት ዓመት በዓል አከበሩ

እግዚአብሔር ካህናቶቻችንን ይባርክልን!! ክቡር አባ ጸጋ ዘአብ እንኳን ለ25ኛ ዓመት የክህነት ዓመት በሰላም አደረሶት፤ ቀሪ ዘመኖትም የወንጌሉ አርበኛ ሆነው ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋፋትና የስብከተ ወንጌልን አገልግሎት የሚያቀጣጥሉበት እንዲሆንልዎ እግዚአብሔር ጸጋውን ያብዛሎት

“መሪነት እና ተልእኮ” በሚል መሪ ቃል ለቁምስናዎች ለሥርዓተ አምልኮ እና ስብከተ ወንጌል ኮሚቴዎች የአንድ ቀን ሥልጠና ተሰጠ                  በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን...
25/04/2026

“መሪነት እና ተልእኮ” በሚል መሪ ቃል ለቁምስናዎች ለሥርዓተ አምልኮ እና ስብከተ ወንጌል ኮሚቴዎች የአንድ ቀን ሥልጠና ተሰጠ

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን የእምድብር ሀገረስብከት ሐዋርያዊ ጽ/ቤት የስብከተ ወንጌል እና ሥርዓተ አምልኮ ሐዋርያዊ ቢሮ አዘጋጅነት ለቁምስናዎች ለሥርዓተ አምልኮ እና ስብከተ ወንጌል ኮሚቴዎች የአንድ ቀን ሥልጠና ተሰጠ።

መርሐ ግብሩን ክቡር አባ ተስፋአምላክ ፍቅሬ በጸሎት ያስጀመሩ ሲሆን ክቡር አባ ፍቅረኢየሱስ ተስፋዬ መግቢያ ንግግር አድርገዋል።

ሥልጠናውን የእምድብር ሀገረስብከት ጠቅላይ ጽ/ቤት ፋይናንስ እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ቁምላቸው ወ/ገብርኤል “መሪነት እና ተልእኮ” በሚል መሪ ቃል ለታዳሚዎች ገለጻ አድርገዋል።

በሥልጠናውም አቶ ቁምላቸው ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶሳዊት መሆኗን አንሥተው የመሪነት መመሪያ ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ የእረኝነት ባሕርይ እና የተለመዱ የአመራር ስሕተቶችን ምንነትን በማንሣት ማስወገድ እንዳለብን ፣ ስለ ጠንካራ መሪዎች መገለጫ ባሕርያት እውነታዎች ምንነትን አንሥተዋል ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በመጨረሻም ውይይት ተደርጎ ፕሮግራሙ በጸሎት ተዘግቷል።

24/04/2026

ኢየሱስ | ዘማሪት ፀሐይ ፍቅሩ

የአባ ፓስካል መታሰቢያ የወጣቶች እግር ኳስ ውድድር ተጠናቀቀ።   ሚያዝያ 14/2018ዓምበኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የእምድብር ሀገረ ስብከት፣ የቤትን እንውደድ" (LOVING HOME...
22/04/2026

የአባ ፓስካል መታሰቢያ የወጣቶች እግር ኳስ ውድድር ተጠናቀቀ።
ሚያዝያ 14/2018ዓም

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የእምድብር ሀገረ ስብከት፣ የቤትን እንውደድ" (LOVING HOME ) ፕሮጀክት እና ከሀዋርያዊ ቢሮ የወጣቶች ክፍል ጋር በመተባበር ፣ሲካሄድ የቆየው ታላቁ የወጣቶች የእግር ኳስ ውድድር እሁድ ፍጻሜውን አግኝቷል።

ለታላቁ አባትና መሪ አባ ፓስካል መታሰቢያነት የተሰየመው ይህ ውድድር፣ ባለፉት ወራት በከፍተኛ ስፖርታዊ ፉክክር እና በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር ሲካሄድ ቆይቶ፣ እጅግ አስደሳች በሆነ የፍጻሜ ጨዋታ ክቡራን አባቶች፣ደናግላን እህቶች እንዲሁም ሌሎች የማህበረሰቡ በታላቅ ድምቀት ተቋጭቷል።

"አራት ቡድኖች - አንድ ራዕይ፤ አባ ፍራንሷ የዋንጫው ባለቤት!"

በዚህ በመታሰቢያ ውድድር ላይ በቅዱሳን አባቶች ስም የተሰየሙ አራት ቡድኖች ማለትም፦ አባባ ሩፋኤል፣ አባባ እንጦንዮስ፣ አባባ እስጢፋኖስ እና አባ ፍራንሷ ተሳታፊ የነበሩ ሲሆን፣ ትናንት በተደረገው እጅግ ተቀራራቢ እና ድንቅ ፍልሚያ የፍጻሜ ጨዋታ አባ ፍራንሷ ተጋጣሚውን አባባ እስጢፋኖስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የታሪካዊው ዋንጫ ባለቤት መሆን ችሏል።

ይህ ውድድር ከስፖርታዊ ፉክክር ባለፈ፣ ወጣቶቻችን በሀገራቸው ተስፋ እንዲሰንቁ እና አደገኛ ስደትን ተጸይፈው በሀገራቸው ሰርተው እንዲለወጡ ለማስተማር የተወጠነ የ"ቤትን እንውደድ" (LOVING HOME) ፕሮጀክት አካል ነው። ውድድሩ በወጣቶች መካከል የማይበገር አንድነትን፣ ወንድማማችነትን እና ቤተሰባዊ ፍቅርን መገንባት የቻለ ሲሆን፣ ወጣቶች በቤተክርስቲያን ጥላ ስር ተሰባስበው አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ትልቅ ድልድይ ሆኗል። የአባ ፓስካልን አርአያነት በመከተል ወጣቶቻችን እርስ በእርሳቸው ያላቸውን ትስስር ያጠናከሩበት እና ለወደፊት ተስፋቸውን ያደሱበት ልዩ አጋጣሚ ሆኗል።

በመጨረሻም አባታዊ ምክራቸውን የሰጡት ክቡራን አባቶች፥ ክቡር አባ ሀብተሥላሴ አንተዋን(የሀገረ ስብከቱ ጠቅላይ ጸሐፊ) እንዲሁም ክቡር አባ ተስፋአምላክ ፍቅሬ( የሀገረ ስብከቱ የሐዋርያዊ ዘርፍ አስተባባሪ) ወጣቶች ሀገራቸውን እንዲወዱ፤ እና ወጣቶችን በእንደዚህ አይነት ቦታ ማየት አስደሳች መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይም ከሁሉም ወንድሞቻችን ጋር መጫወት እንደሚገባንና ቀጣይ በሚደረጉ ውድድሮችም፥ ከሁሉም እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ጋር አብረን መጫወት እንዳለብን አስገንዝበዋል።

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አገና ቅዱስ ገብርኤል ካቶሊክ አጸደ ሕጻናት ትምህር ቤት G +1 (8 ) ክፍል የያዘ እንዲሁም የመምህራን እስታፍና መጸዳጃ ቤት የያዘ ህንጻ ግንባታ በብጹ...
13/04/2026

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አገና ቅዱስ ገብርኤል ካቶሊክ አጸደ ሕጻናት ትምህር ቤት G +1
(8 ) ክፍል የያዘ እንዲሁም የመምህራን እስታፍና መጸዳጃ ቤት የያዘ ህንጻ ግንባታ በብጹዕ አቡነ ሉቃስ የእምድብር ሀገረ ስብከት ጳጳስ እየተመረቀ ይገኛል ።

የ2018ዓም የትንሳዔ በዓል በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በቅዱስ አንጦንዮስ ካቶድራል ቤተክርስቲያን
12/04/2026

የ2018ዓም የትንሳዔ በዓል በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በቅዱስ አንጦንዮስ ካቶድራል ቤተክርስቲያን

11/04/2026

ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የእምድብር ሀገረስብከት ጳጳስ ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

...........ቀዳም ሥዑር ........ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሲኦል የወረደበት በሲኦል ከአዳም ጀምሮ ያሉ ነፍሳት ምሕረት ያገኙበት ነጻ የወጡበት ቀን ይታሰባል በዛሬው...
11/04/2026

...........ቀዳም ሥዑር ........

ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሲኦል የወረደበት በሲኦል ከአዳም ጀምሮ ያሉ ነፍሳት ምሕረት ያገኙበት ነጻ የወጡበት ቀን ይታሰባል

በዛሬው እለት ክርስቲያን በዝምታ በጸጥታ በጾም የምታሳልፈው ቀን ነው፡፡
ንጉሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቃብር ውስጥ ያረፈበት ፣ የተኛበት ፣ የዋለበት ቀን ነው፡፡

የጥንት አባቶች በስብከቶቻቸው ዛሬ በዓለም ላይ ትልቅ ዝምታ ታላቅ ጸጥታ ሰፍሯል ቤተክርስቲያን ጸጥ ብላለች ዓለም ጸጥ ብሏል ንጉሱ አርፏልና ብልው ይሰብኩ ነበር ፡፡

በዛሬው እለት የቄጤማ ቡራኬ ይደረጋል ቄጤማ የተስፋ ምልክት ነው የኖህ ዘመን የውሀ ጥፋት እንዳለቀ በኖህ መርከብ ውስጥ የነበሩ ሰዎችና ነፍሳት ጎርፉ እንደጎደለ ያውቁ ዘንድ ኖህ እርግብን ልኮ እርግብ ቄጤማ ይዞ እንደተመለሰ ጥፋት እንደቆመ ልምላሜ እንደመጣ የሚያሳይ ነው ፡፡

በክርስቶስ ሞት ሀጥያት ፣ ጥፋት ተሸንፏል ተስፋችን ትንሳዔ ፣ ልምላሜ ፣ ሕይወት ነውና ተስፋ አለን የሚል ምልዕክት ያለው ሲሆን በዛሬው ዕለትም ክርስትያኖች በጸጥታ በዝምታ ለዕኩለ ለሊት ቅዳሴ የሚዘጋጁበት ቀን ነው፡፡

"ስቅለተ ዓርብ" በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስትያን በእምድብር ሀገረ ስብከት በቅዱስ እንጦንዮስ ካቶድራል እምድብር፡፡
10/04/2026

"ስቅለተ ዓርብ" በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስትያን በእምድብር ሀገረ ስብከት በቅዱስ እንጦንዮስ ካቶድራል እምድብር፡፡

ጸሎተ ኀሙስ በእምድብር ሀገረ ስብከት በመንፈሳዊ ስነ ሥርዓቶች ተከበረ።ሚያዝያ 1/2018ዓ.ምበኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በእምድብር ሀገረ ስብከት የሰሙነ ሕማማት፦ጸሎተ ኀሙስ በተለ...
09/04/2026

ጸሎተ ኀሙስ በእምድብር ሀገረ ስብከት በመንፈሳዊ ስነ ሥርዓቶች ተከበረ።
ሚያዝያ 1/2018ዓ.ም

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በእምድብር ሀገረ ስብከት የሰሙነ ሕማማት፦ጸሎተ ኀሙስ በተለያዩ መንፈሳዊ ስነ ሥርዓት ተከብሮ ዋለ በዕለቱም በተደረጉት መንፈሳዊ ሥርዓቶች የሕጽበት እግር( የእግር አጠባ) እና የህሙማን፥ የሜሮን እንዲሁም የንዑሰ ክርስትያን ዘይት ቡራኬ የተደርገ ሲሆን፦ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የዕለቱን የጸሎተ ኅሙስ ቅዳሴን አሳርገዋል።

በዕለቱም ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የእምድብር ሀገረ ስብከት ጳጳስ መላው የሀገረ ስብከቱ ካህናት ገዳማውያን እና የሀገረ ስብከቱ ምእመናን የተገኙ ሲሆን፦ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የደቀ መዛሙርቱን እግር እንዳጠበና የትሕትና ምሳሌነትን እንዳሳየ ብፁዕ አባታችንም የካህናት እግር ያጠቡ ሲሆን፦ ክቡር ቆሞስ አባ ፍቅሩ የምእመናን እና የወጣቶችን እግር አጥበዋል።

ዕለቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ቁርባንን የመሠረተበት እንዲሁም ክህነትን የሠራበት ቀን መሆኑን ገልጸው የዕለቱን ቃለ ምዕዳን ያሰሙት ብፁዕ አባታችን ካህናትን እንኳን አደረሳችሁ በአገልግሎታችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ እግዚአብሔር ይስጥልን ብለው ምስጋናን አቅርበዋል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ ትሕትናን፤ ዝቅ ብሎ ማገልገልን እንዳሳየን እኛም አንዳችን ለሌላችን ዝቅ ብለን እንድናገለግል፦ ትሕትናን እንድናሳይ፦ ይሁዳ በመምህሩ ላይ ክህደትን አዳረገ፦ እኛ ደግሞ ታማኞች እንድንሆን፥ እና እምነታችንን ጠብቀን እንድንኖር አሳስበዋል።

Address

Wolkite

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Catholic Eparchy of Emdeber posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share