ሰሜን ወሎ ሀገረስብከት ሚዲያ - North Wollo Diocese Media

  • Home
  • Ethiopia
  • Woldia
  • ሰሜን ወሎ ሀገረስብከት ሚዲያ - North Wollo Diocese Media

ሰሜን ወሎ ሀገረስብከት ሚዲያ - North Wollo Diocese Media በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የሚከናወኑ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች እንዲሁም የቤተ ክርስቲያኗ የልማት ሥራዎችን ለእናንተ እናደርሳለን።

የአስተዳደር ጉባኤ አባላቱ በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ጎበኙ።ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ)የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የአስተዳደር...
23/05/2026

የአስተዳደር ጉባኤ አባላቱ በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ጎበኙ።

ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ)

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የአስተዳደር ጉባኤ አባላት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ዛሬ ጎብኝተዋል።

በዋና ሥራ አስኪያጁ ክቡር መልአከ ብርሃን ፍሥሐ ጌታነህ መሪነት በተካሄደው የመስክ ጉብኝት ሀገረ ስብከቱ በከፍተኛ በጀት እያስገነባቸው የሚገኙ ፕሮጀክቶች ተጎብኝተዋል።

በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ አባታዊ መሪነት እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት እየተከናወኑ ስለመሆኑና በግንባታ ሒደት ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለይቶ የመፍትሒ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ታስቦ የጉብኝት መርሐ ግብሩ መዘጋጀቱን ዋና ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

የጉባኤ አባላቱ 300 ወንዶችና 100 ሴቶች ደቀመዛሙርትን ተቀብሎ ለማስተማር ታስቦ እየተገነባ የሚገኘውን አዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት፣ ባለ ሰባት ወለል ሁለገብ የገበያ ማእከል፣ የዘመናዊ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ፣ የመንበረ ጵጵስና ግንባታዎችና እድሳት አፈጻጸም እንዲሁም የኢንቨስትመንት ቦታ ጎብኝተዋል።

ፕሮጀክቶቹ በተቀመጠላቸው ጊዜ በውጤታማነት እንዲፈጸሙ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎችና ኮሚቴዎች በትኩረት እንዲሠሩ ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቷል፤ የአፈጻጸም አቅጣጫም ተቀምጧል።

_______________________________
~ “ ” ~
~ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ~
________________________________
የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ፦
ቴሌግራም~ https://t.me/NWDnews
ዩቲዩብ~ https://youtube.com/c/NorthWolloDioceseMedia
ድረገጽ~ https://eotc-nw.org
ፌስቡክ~ https://www.facebook.com/EOTCNWD
Tiktok~ https://www.tiktok.com/.north?_t=ZM-8ukkHRXMOYg&_r=1

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት እየተገነባ ያለው ግዙፍና ዘመናዊው አዳራሽ ዝርዝር መረጃዎች ይፋ ሆኑ!የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የቤተክርስቲያንን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገ...
14/05/2026

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት እየተገነባ ያለው ግዙፍና ዘመናዊው አዳራሽ ዝርዝር መረጃዎች ይፋ ሆኑ!

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የቤተክርስቲያንን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ግዙፍና ዘመናዊ ሕንጻ እያስገነባ ይገኛል።

ይህ ታሪካዊ ፕሮጀክት በዋናነት 2300 ሰዎችን በአንድ ጊዜ መያዝ የሚችል ግዙፍ አዳራሽ ያለው ሲሆን፣ በአነስተኛ አዳራሾቹ ደግሞ ተጨማሪ 900 ሰዎችን ማስተናገድ ይችላል። ሕንጻው 120 አባላትን የሚይዝ ልዩ የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽን ጨምሮ፣ በመድረኩ ላይ ብቻ 104 መቀመጫዎች ያሉት በመሆኑ ለታላላቅ መንፈሳዊ ጉባኤዎች ምቹ ሆኖ ተዘጋጅቷል።

በተጨማሪም ዘመናዊ ማብሰያ የተገጠመለትና በአንድ ጊዜ 1000 ሰዎችን የሚያስተናግድ ሰፊ የመመገቢያ አዳራሽ እንዲሁም በቂ የመኪና ማቆሚያ ተካቶበታል።

ይህ አዳራሽ በቴክኖሎጂ ረገድ እጅግ ዘመናዊ ሲሆን፣ በአንድ ጊዜ እስከ 24 ቋንቋዎች የትርጉም አገልግሎት መስጫ ክፍሎችና የመጨረሻው የቴክኖሎጂ ውጤት የሆኑ ግዙፍ ስክሪኖች ይገጠሙለታል።

ለኪናዊና መንፈሳዊ ዝግጅቶች የሚሆኑ ዘመናዊ መጋረጃዎችና የኦዲዮ ቪዥዋል መሣሪያዎች የተሟሉለት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ24 ኮንቲነር በላይ ወንበሮችና የኤሌክትሮ ሜካኒካል መሣሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ እየገቡ ይገኛሉ። ይህ ታላቅ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ቤተክርስቲኗ ለምታከናውናቸው አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉባኤዎች ትልቅ አቅም ከመሆኑም በላይ፣ የስብከተ ወንጌልና የአስተዳደራዊ አገልግሎቷን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያዘምነው ይጠበቃል።

©EOTC Broadcasting Service Agency

_______________________________
~ “ ” ~
~ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ~
____________________________
የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ፦
ቴሌግራም~ https://t.me/NWDnews
ዩቲዩብ~ https://youtube.com/c/NorthWolloDioceseMedia
ድረገጽ~ https://eotc-nw.org
ፌስቡክ~ https://www.facebook.com/EOTCNWD
Tiktok~ https://www.tiktok.com/.north?_t=ZM-8ukkHRXMOYg&_r=1

ቅዱስ ሲኖዶስ ጸሎተ ምሕላ አወጀግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በተነጋገረባቸው ጉዳዮች በትኩረት የተወያየው የቤተ ክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ ዕድገትና ተቋ...
14/05/2026

ቅዱስ ሲኖዶስ ጸሎተ ምሕላ አወጀ

ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም

ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በተነጋገረባቸው ጉዳዮች በትኩረት የተወያየው የቤተ ክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ ዕድገትና ተቋማዊ ሕልውና ስለማስጠበቅ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ሀገራችንን ጨምሮ በመላው ዓለም እየታየ ያለው ግጭትና የሰላም መታጣት በእጅጉ አሳስቦታል፡፡

በመሆኑም ስለ ዓለምና ስለ ሀገራችን ሰላም፣ ስለ ሰው ልጆች ደኅንነት፣ በየቦታው በሃማኖታቸው ምክንያት መከራ የሚደርስባቸውንና ግጭት ባለባቸው ቦታዎች ያሉ ኦርቶዶክሳውያንን በማሰብ በመጪው የ2018 ዓ/ም ጾመ ሐዋርያት በመላው ዓለም ባሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ምሕላ እንዲደርስ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

©EOTC Tv

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫየእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክ...
14/05/2026

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶሳዊ በመሆኗ አበው ቅዱሳን በፍትሕ መንፈሳዊና በጉባኤ አድያም ዘአንጾኪያ “ወይኩን ሲኖዶስ ዘጳጳሳት ፪ተ ጊዜያተ በበዓመት - የጳጳሳት ጉባኤም በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን” ብለው በደነገጉት ቀኖና መሠረት፤ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤውን በኅብረተ መንፈስ ቅዱስ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ አካሄዷል፡፡

ምልዓተ ጉባኤው ስለ ሀገር ሰላም፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነት፤ ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነትና ክብር፣ በአጠቃላይ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ሰፊ ውይይቶችን በማድረግ ዘመኑን የዋጁ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ከውሳኔዎቹም መካከል፡-

የቤተ ክርስቲያናችንን አንድነት መጠበቅና ማስጠበቅ የቅዱስ ሲኖዶስ ተግባር በመሆኑ ጥንታዊትና ሐዋርያዊት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን በአንድነቷና በሉዓላዊነቷ እንደተረከብናት ለወደፊቱም ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እንድትቀጥል በምልዓተ ጉባኤው የተሠየመው በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራው “የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት” ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ በተረጋጋ መንገድ እንዲካሄድ፣ ለሀገር ሰላምና ለሕዝብ አንድነት በሚጠቅም ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምትጸልይ ሲሆን ምርጫው በሁሉም ወገን ለኢትዮጵውያን ዘላቂ ሰላምንና መረጋጋትን የሚያስገኝ ሆኖ እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፡፡

ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲ ሀገረ ስብከትን በሊቀ ጵጵስና በቋሚነት እንዲመሩ፣ ሕዝቡን እንዲያጽናኑ እየደረሰ ያለውን ችግር ከቋሚ ሲኖዶስና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ከሚመራው የሰላም ኮሚቴ ጋር በመሆን የሚመለከተውን የመንግሥት አካል በማነጋገር ዘላቂ መፍትሔ እንዲያፈላልጉ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡

ከጥንት ጀምሮ “ቅዱስ ሲኖዶስ” በሚል ርእስ እየተዘጋጀ ይታተም የነበረው ታሪካዊ መጽሔት የቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ ውሳኔዎችን በማካተት በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስፈጻሚነት ሕትመቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

የቤተ ክርስቲያናችንን ደንቦች መመሪያዎች መርምሮ ማጽደቅ የቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ሥልጣን በመሆኑ፡-

የስብከተ ወንጌል ሐዋርያዊ ተልእኮ ማስፈጸሚያ ደንብ በብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሰብሳቢነት

የአንድነት ገዳማት ኅብረት መተዳደሪያ ደንብ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስና ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ባሉበት በድጋሚ እንዲታይና ሌሎቹም ለውሳኔ የቀረቡ ደንቦች በሊቃውንትና በሕግ ባለሙያዎች ታርመው ለጥቅምት 2019 ዓ/ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል

የቀድሞው የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ “የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ”ና “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ” በሚሉ አርእስት አዘጋጅተው ያሳተሟቸው መጻሕፍትን የማሳተምና የማሰራጨት የባለቤትነት መብት ከሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

ከተለያዩ አህጉረ ስብከት በቀረቡ ጥናቶችና የማጣራት ውጤቶች መሠረት፡-

የደቡብ ሱዳን ሀገረ ስብከት ከምሥራቅ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ጋር ተደርቦ በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ሊቀ ጳጳስ እንዲመራ፤
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ሊቀ ጳጳስ የጋምቤላንና የቤንሻንጉል ጉምዝ አህጉረ ስብከትን ብቻ እንዲመሩ፤
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጰስ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከትን እንደያዙ እንዲቀጥሉ፤
ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው በአባትነት እንዲመሩ፣
የኮንታ ዞን ሀገረ ስብከት እንዲሆን የቀረበው ጥያቄ የጸደቀ በመሆኑ ሀገረ ስብከቱ ራሱን ችሎ እንዲደራጅና በብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ ሊቀ ጳጳስ እንዲመራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የልማት ተግባራትን ምልዓተ ጉባኤው በከፍተኛ ደረጃ በማድነቅ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ/ ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ሲቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ በአባታዊ አመራር የፈጸሙት አስደናቂ የሥራ አፈጻጸም በጉልህ የሚታይ ለውጥ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የሚጠቅም፣ ሉዓላዊ ክብሯን የሚያስጠበቅ፣ ለሁሉም አበው ምሳሌነት ያለው በመሆኑ ምልዓተ ጉባኤው እጅግ ከፍ ባለ ክብር አመስግኗል፡፡

በዚህም መሠረት በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጁ አባታዊ መሪነት እየተከናወኑ ያሉት ተግባራት ማለትም፡-

የቤተ ክርስቲያንን ቀደምት ሠነዶች በዲጂታል ቴክኖሎጅ እንዲደራጁ የተደረገበት ሥልት ተጠናክሮ እንዲቀጥል፤

ከ1970 ዓ/ም ጀምሮ በመጋዝን ተከማችተው የቆዩ በርካታ ልዩ ልዩ መጻሕፍትን የማሠራጨት ሂደት በተጀመረው መንገድ እንዲጠናቀቅ፤

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የኢንፎርሜሽንና ኮምኒኬሽን ተጠቃሚ እንድትሆን የተጀመረው ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ በሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን መዋቅር በየደረጃው ተጠናክሮ ተግባራዊ እንዲሆን፤

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥር የተጀመሩ የሕንፃ ግንባታዎችና አጠቃላይ የልማት ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ሁሉም አህጉረ ስብከትና ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽኦና ትብብር እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፡፡

በሰሜን አሜሪካ የሰሜን ካሊፎርኒያ፣ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት ኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና ቅድስት አርሴማ ገዳም የመንፈሳዊ ኮሌጅ፣ የአብነት ት/ቤት ሥርዓተ ትምህርት የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ታሪክና ትውፊት በጠበቀ መልኩ ተጠናክሮ መዋቅራዊ ተጠሪነቱም በአግባቡ ተጠብቆ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ያቀረበውን የ2019 ዓ/ም በጀት በማጽደቅ በተገቢው መንገድ ሥራ ላይ እንዲውል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡

በመጨረሻም ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በተነጋገረባቸው ጉዳዮች በትኩረት የተወያየው የቤተ ክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ ዕድገትና ተቋማዊ ሕልውና ስለማስጠበቅ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ሀገራችንን ጨምሮ በመላው ዓለም እየታየ ያለው ግጭትና የሰላም መታጣት በእጅጉ አሳስቦታል፡፡

በመሆኑም ስለ ዓለምና ስለ ሀገራችን ሰላም፣ ስለ ሰው ልጆች ደኅንነት፣ በየቦታው በሃማኖታቸው ምክንያት መከራ የሚደርስባቸውን በየቦታው የሚገኙና ግጭት ባለባቸው ቦታዎች ያሉ ኦርቶዶክሳውያንን በማሰብ በመጪው የ2018 ዓ/ም ጾመ ሐዋርያት በመላው ዓለም ባሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ምሕላ እንዲደርስ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

በመላው ዓለም፣ በደቡብ አፍሪካና በሳውዲ ዐረቢያ የሚኖሩ ዜጎቻችን ሰብዓዊ መብት እንዲከበር፣ የርኅራኄ ምሕረትና ፍትሕ እንዲያገኙ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ክትትል እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ሐዋርያዊ ጥሪውን በማቅረብ ለሰባት ቀናት ሲያካሂድ የሰነበተውን ቀኖናዊ ጉባኤ ዛሬ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም. በጸሎት አጠናቋል፡፡

“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ”

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ/ም

ቅዱስ ሲኖዶስ ለ6 ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የርክበ ካህናት ጉባኤ አጠናቀቀ።ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ምየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ለስድስት ተከታታይ ቀናት...
13/05/2026

ቅዱስ ሲኖዶስ ለ6 ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የርክበ ካህናት ጉባኤ አጠናቀቀ።

ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ለስድስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን መደበኛ ምልዓተ ጉባኤውን በ22 አጀንዳዎች ላይ በመወያየትና ለቤተክርስቲያናችን ቀጣይ ጉዞ ወሳኝ የሆኑ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማጠናቀቁን የቅዱስ ሲኖዶስ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ቀሲስ ዳንኤል ሰይፈ-ሚካኤል በሰጡት መግለጫ አስታውዋል።

ጉባኤው በተለይም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት እየተከናወኑ ያሉትን የልማት፣ የዘመናዊ አሠራር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎች በዝርዝር ከገመገመ በኋላ ከፍተኛ አድናቆቱን መግለጹን ኀላፊው ተናግረዋል።

ጉባኤው በቀጣዮቹ ስድስት ወራት በቋሚ ሲኖዶስ ውስጥ የሚያገለግሉ ብፁዓን አባቶችን ምርጫ ማካሄዱን የኮሙኒኬሽን ኃላፊው ተናግረዋል።

ለቀናት በተለያዩ አገራዊና ሃይማኖታዊ አጀንዳዎች ላይ ሲመክር የቆየው የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ ነገ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሚሰጡት ቃለ ምዕዳንና አባታዊ ቡራኬ በይፋ ይጠናቀቃል።

EOTC tv

______________________________
~ “ ” ~
~ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ~
____________________________
የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ፦
ቴሌግራም~ https://t.me/NWDnews
ዩቲዩብ~ https://youtube.com/c/NorthWolloDioceseMedia
ድረገጽ~ https://eotc-nw.org
ፌስቡክ~ https://www.facebook.com/EOTCNWD
Tiktok~ https://www.tiktok.com/.north?_t=ZM-8ukkHRXMOYg&_r=1

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ...
12/05/2026

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት እንደሚከተለው ነው፦

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

‹‹ተዘከሩ መቁሓነ ዘከመ ተሞቃሕክሙ ምስሌሆሙ ወእለ ተሣቀዩ ከመ ዘሀለውክሙ በሥጋክሙ፡-
ከእነርሱ ጋር አብራችኋቸው እንደታሰራችሁ ሆናችሁ እስረኞችን ዐስቡ፤ መከራ የጸናባቸውንም በሥጋችሁ ከእነርሱ ጋር እንዳላችሁ ሆናችሁ ዐስቡ››
(ዕብ. 13፡3)

እውነተኛ እምነትም ሆነ ጤናማ አመለካከት የሚመዘነው መከራ ስለሚቀበሉ ሰዎች ሰምቶና አይቶ በዝምታ ባለማለፍ፤ ይልቁንም በእነርሱ ሕመም ውስጥ ራስን በማስገባት በሚሰማው ጥልቅ ኀዘን እና በሚደረገው ድጋፍ ነው፡፡ ይልቁንም በዚች ዓለም የምንኖር ለችግርና ለመከራ ቅርብ እንደመሆናችን የታሰሩትን መጎብኘት፣ የተገፉትን ማጽናናት፣ በስደት ምድር ላይ ሆነው በሞት ፍርድ የሚጨነቁትን ወገኖች ስቃይም እንደራሳችን ስቃይ በመቁጠር ስለእነርሱ ድምፅ መሆንና ማዘን ስንችል በሰማያዊው መንግሥት የማይጠፋ የጽድቅ ዋጋን እናከማቻለን፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን!

እረኛ በበረት ውስጥ ያለችው አንዲት በግ ስትጠፋ ወይም ለአደጋ ስትጋለጥ ዝም ብሎ እንደማያይ ሁሉ፣ በሳዑዲ ዓረቢያ ምድር በሞት ጥላ ሥር ሆነው ‹‹የፍትሕ ያለህ›› እያሉ የሚጮኹ፤ በጭንቀት ቀናትን የሚቆጥሩና ድምፅ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን የተሻለ ኑሮ እናገኛለን ብለው በተሰደዱበት ሀገር ሕይወታቸው በጅምላ ሊቀጠፍ እንደሆነ መረጃውን ከልዩ ልዩ መገናኛ ብዙኃን የተገነዘብን በመሆኑ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ጠቀሜታው የሰው ልጆችን ሕይወት ለመጠበቅ ነውና የኢትዮጵያ መንግሥት በከፍተኛ ደረጃ ከሚገኙ ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በመነጋገር በግፍ የተፈረደባቸው ልጆቻችን የሞት ፍርድ እንዲነሳላቸውና ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበት መንገድ ይመቻች ዘንድ የተጀመሩ ሥራዎች ልዩ ትኩረት እንዲሰጥባቸው፤ ወገኖቻችንም በቋንቋ እጥረትና በሕግ አማካሪ እጦት ለሞት እንዳይዳረጉ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን ፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ለሰው ልጅ የሰጠው ታላቅ ስጦታ ሕይወት ነው፤ "አትግደል" የሚለው ሕግም በማንኛውም ምድርና ቋንቋ የሚሠራ ሲሆን ፍርድ ያለ ምሕረት ከሆነ አምላካዊ ቁጣን ይጋብዛልና የሳዑዲ ባለሥልጣናት የሁለቱን ሀገራት የቆየ ታሪክና ወዳጅነት አስበው፣ በሞት ፍርድ ጥላ ሥር ላሉት ወገኖቻችን ምሕረትን እንዲያደርጉ፣ ቅጣቱንም ወደ እስራት እንዲቀይሩ በአባታዊ ርኅራኄ እንጠይቃለን ፡፡

ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችም በማያውቁት ቋንቋ እንዲሁም ባልተረዱት የሕግ ሂደት ሞት የተፈረደባቸውን ወገኖች ስቃይ ተመልክተው የፍትሕ መዛባትን እንዲቃወሙና የንጹሐንን ነፍስ እንዲታደጉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በመጨረሻም፣ ማንኛውም በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ ሰው ሕይወቱ ሊጠፋ አይገባምና ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን የክርስትናችን አንዱ መገለጫ የአንደኛው ወገን ሕመምን በጋራ መካፈል እንደሆነ ተረድታችሁ ወደ ፈጣሪያችን በጸሎት እንድትማጸኑ፤ መላው ኢትዮጵያውያንም ለመፍትሔው የበኩላችሁን ጥረት እንድታደርጉ ስንል አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሦሰተኛ ቀን ውሎ ሦስት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳለፈ፡ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ)ዓመታዊ የርክበ ካህናት ...
08/05/2026

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሦሰተኛ ቀን ውሎ ሦስት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳለፈ፡

ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ)

ዓመታዊ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሦስተኛ ቀን ውሎ አስመልክቶ የቅዱስ ሲኖዶስ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ቀሲስ ዳንኤል ሰይፈሚካኤል (ረ/ፕ) በሰጡት ማብራሪያ ምልዓተ ጉባኤው በሦስት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡

ቀዳሚው አጀንዳ የበዓላት አካባበርን የተመለከተ ሲሆን

1. በቤተክርስቲያናችን የሥርዓተ አምልኮ አፈጻጸም፣ በረከት እና ጸጋ የሚገኝባቸው በዓላት አካባበር ላይ አንዳንድ አላስፈላጊ ከመንፈሳዊነት የወጡ እንቅስቃሴዎችን፣ በዝማሬ፣ በዓወደ ምሕረት ሥርዓት በመሳሰሉት በጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም ቀርቦ ማስተማሪያ የሚሆን ሰነድ በሊቃውንትና በምሁራን ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ በተወሰነው መሠረት ሰነዱ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን ነገር ግን ሰነዱ የሚቀሩት ጉዳዮች ስላሉ ቀኖናዊ ጉዳዮቹ በሊቃውንት ጉባኤ ታይተው ለቀጣይ ለጥቅምት ምልዓተ ጉበኤ እንዲቀርቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል ።

2. ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ገዳማት በተመለከተ ሰፊ ወይይት ከተደረገ በኃላ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የገዳሙ ተወካዮች በአካል ቀርበው እንዲስረዱና ለችግሮቹ መፍትሔ እንዲሰጥባቸው ምላዓተ ጉባኤው ወስኗል።

3.የደቡብ ሱዳን ጁባን በሚመለከተ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አጣሪ ኮሚቴ የቀረበውን የማጣራት ሥራ ሪፖርት በአግባቡ ከተሰማ በኃላ የደቡብ ሱዳን አብያተ ክርስቲያናት በምሥራቅ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ሥር እንዲተዳደር ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል።

የቅዱስ ሲኖዶስ 75ኛ ዓመት ዝክር በዓልን የተመለከተ አጀንዳ ላይ ተወያይቷል። በተጨማሪም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት መሠረት የሆነው "የመንፈስዊ ጉባኤ " የተመሰረተበት 100ኛ ዓመት ተዘክሯል።

ለመታሰቢያ እንዲሆን በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተዘጋጀው መጽሔት በቅዱስነታቸው ተባርኮ ተመርቋል፤ ለዝግጅቱ የተባበሩትን አካላት ሁሉ በማመስግን የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች በሰነድ መልክ ተዘጋጅተው ለህትመት እንዲበቁ ተወስኗል ።

EOTC TV

ቅዱስ ሲኖዶስ የተመሠረተበትን ፸፭ኛ ዓመት ፤የቤተክህነት  አስተዳደርና ለሊቃውንት ጉባኤ አደረጃጀት መሠረት የሆነው  "መንፈሳዊ ጉባኤ ዘመንግሥተ ኢትዮጵያ" የተቋቋመበት ፻ኛ ዓመት የመታሰቢያ...
08/05/2026

ቅዱስ ሲኖዶስ የተመሠረተበትን ፸፭ኛ ዓመት ፤የቤተክህነት አስተዳደርና ለሊቃውንት ጉባኤ አደረጃጀት መሠረት የሆነው "መንፈሳዊ ጉባኤ ዘመንግሥተ ኢትዮጵያ" የተቋቋመበት ፻ኛ ዓመት የመታሰቢያ በዓል ተከበረ። በዚሁ ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስን ታሪክ የሚዘክር መጽሔትም ተመርቋል።

ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የቅዱስ ሲኖዶስ ታሪክ የሚዘክር መጽሔት መርቀዋል።

ቅዱስነታቸው በመጽሔቷ ላይ ባስተላለፉት መልእክት
"በኢትዮጵያዊ ሊቀ ጳጳሳት የሚመራው የቅድስት ቤተክርስቲያናችን ቅዱስ ሲኖዶስ ፸፭ኛ ዓመት ለቤተክህነታችን አስተዳደርና ለሊቃውንት ጉባኤ አደረጃጀት መሠረት የሆነው "መንፈሳዊ ጉባኤ ዘመንግሥተ ኢትዮጵያ" ለተቋቋመበት ፻ኛ ዓመት የመታሰቢያ በዓል እንኳን በሰላም አደረሰን፣ አደረሳችሁ ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የቅዱሳን ሁሉ ጉባኤ የሆነችው ቅድስት ቤተክርስቲያናችን አሠራርዋ የዘመነ፣ ታሪኳ የተመዘገበ፣ ቅርሶቿ የተጠበቁ፣ አገልግሎቷ የሠመረ ሆኖ መንፈሳዊ ተልዕኮዋ ለሁሉ ተደራሽ እንዲሆን የምናደርገውን ጥረት በአንድነትና በመከባበር ከሠራነው በእግዚአብሔርም በሰውም ዘንድ ሞገስንና ክብርን የሚያስገኝ መሆኑን የቅዱስነታቸው መልእክት ያስረዳል።

ቅዱስነታቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ቤተክርስቲያናችን በራስዋ ሊቀ ጳጳሳት ለመመራት መሠረት የጣለችበትን ፸፭ኛ ዓመትና "መንፈሳዊ ጉባኤ ዘመንግሥተ ኢትዮጵያ" የተቋቋመበትን ፻ኛ ዓመት የመታሰቢያ በዓል ምክንያት በማድረግ ተዘንግቶ የኖረውን የታሪካዊ መጽሔት ኅትመት እንዲቀጥል በቋሚ ሲኖዶስ አስወስኖ ለንባብ በማብቃቱ እናመሠግናለን ብለዋል ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው። በመጨረሻ አገልግሎቱ የሚሠምረው፣ ቅድስት ቤተክርስቲያንም የምትከብረው እግዚአብሔር የወሰነውን ሥራ በሲኖዶሳዊ አንድነት ስንሠራው ብቻ በመሆኑ፣ የሐዋርያት ተከታዮች ሆነን የተቀበልነውን አደራ መጠበቅ እንችል ዘንድ ዘመን ተሻጋሪ የልዕልና ሥራ ላይ ልናተኩር ይገባል ሲሉ መልእክታቸውን በመጽሔቷ ላይ አስተላልፈዋል።

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመጽተ ላይ ባሠፈሩት መልዕክት ሐዋርያዊ ትውፊትን መሠረት በማድረግ እውነትንና አማናዊ ሥርዐትን በአንድነትና በፍቅር ጠብቀው ያቆዩት የቀደሙት አባቶቻችን የቤተክርስቲያንን አንድነትና የፀናውን ሥርዐት ስላስተላለፉልን ዛሬ የተዋበ ሥርዐት እንዲሁ የተገኘ ሳይሆን አባቶቻችን የሕይወት ዋጋ የከፈሉበት የመንፈሳዊ ተጋድሎ ውጤት ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ሲኖዶስ ያገኘውን ሉዓላዊነትና መዋቅራዊ ጥንካሬ ተጠቅሞ በአሁን ዘመን ካለው ፈጣን ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ለውጥ ጋር ለመራመድ ሊሠራቸው የሚገቡ በርካታ መሠረታዊ ሥራዎች አሉ ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክበስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን!ብፁዕ ኣቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ ኣስኪያጅ፤ ብፁዕ ኣቡነ ዲዮስቆ...
06/05/2026

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን!
ብፁዕ ኣቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ ኣስኪያጅ፤
ብፁዕ ኣቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፤
ብፁዕ ኣቡነ ሕርያቆስ
የኣዲስ ኣበባ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት፣
በኣጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፦
ማሕየዊት በምትሆን ሞቱ ሰማያውያንና ምድራውያንን ያስታረቀ፣ በቅድስት ትንሣኤውም የሙታንን ሕይወት በተስፋ ያለመለመ ጌታችን፣ ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ እንኳን ለዓመታዊው የረክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
“እስመ ተዋለጠ እግዚአብሔር ዓለመ በክርስቶስ ኣናኅስዮ ኃጢኣቶሙ ወኢነጺሮ ጌጋዮሙ፤ ወረሰየ ላዕሌነ ቃለ ሥምረቱ፤ ወወሃበነ መልእክተ ሣህሉ፡- እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና በደላቸውን ኣይቈጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል ኣኖረ” (2ቆሮ. 5፥19)።
የእግዚአብሔርም ልጅ፣ የሰውም ልጅ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም በሰብእነት ሲገለጽ ግልጽ የሆነ ዓላማና ግብ እንደነበረው ቅዱስ መጽሓፍ ይነግረናል፤ እሱም በሰማይም፣ በምድርም ያሉትን በሙሉ ማስታረቅ፣ ማገናኘትና ኣንድ ማድረግ ነበረ፤
ጌታችን ይህንን ሲያደርግ ሰማያውያኑንና ምድራውያኑን የለያየው ምክንያት በማስወገድ ነው፤ የመለያየቱ ምክንያት ክፉ ኅሊና ኣምጦ የወለደው በደልና እሱን ተከትሎ የተከሠተው ኃጢኣት ነበረ፤ በኃጢኣት ምክንያት የገባው ሞት ደግሞ የቅጣቱ ማሳያ ፍርድ ነበረ።
የመጀመሪያዎቹ ሰዎች በፈጸሙት ስሕተት መነሻነት ምድርንና ምድራውያንን ለከባድ ቅጣትና መርገም የዳረገው ይህ መለያየት ለሰማያውያኑም ተርፎኣል፤
ምክንያቱም መለያየቱ በእግዚአብሔርና በሰው፣ በመላእክትና በሰው፣ በሰውና በሰው፣ በነፍስና በሥጋ ጭምር የጥል ግድግዳን ገንብቶ እስከ ክርስቶስ ዕለተ ስቅለት መዝለቁን በቅዱስ መጽሓፍ የምናውቀው ስለሆነ ማለት ነው።
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!

ቀዳማዊና ዘላለማዊ የሆነው ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ሰብእናችንን ተዋሕዶ በዚህ ዓለም የተገለጸው ሰማያውያንንና ምድራውያንን የለያየው የጥል ግድግዳን ለማፈራረስ ነው፤
ለመለያየት ምክንያት የሆነችውን ኃጢኣት በሰውነቱ በመቅጣት የሕግን ትእዛዝ ከፈጸመ በኋላ የዕርቁን ተግባር በወሳኝ መልኩ ኣከናውኖታል፤
በክርስቶስ ቤዛነት የሆነው ይህ ዕርቅ በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተወደደ ነበረና እሱ ራሱ በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ኣስታረቀ፤
ለዚህም ነው ተበዳይ እሱ፣ ቤዛዊ መሥዋዕት ሆኖ የቀረበው እሱ፣ ኣስታራቂ እሱ፣ ታራቂ እሱ ሆኖ የምናገኘው፤ ለሱ የሚሳነው ነገር የለምና ለኛ ግር የሚል ቢመስልም ለሱ ቀላል ነበረ።
በዚህ የዕርቅ ተግባር ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሰውና ሰው፣ ነፍስና ሥጋ ታርቀው በይፋ ተገናኙ፤ በኅብረትና በኣንድነትም መኖር ቻሉ፤ በቀኙ ለተሰቀለው ሽፍታ “ዛሬውኑ ከኔ ጋር በገነት ትኖራለህ” የሚለው ቃለ ምሕረትና “ኣባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ ኣደራ እሰጣለሁ” የሚለው ቃለ ኣማሕፅኖ የዕርቁ፣ የግንኙነቱና የኣንድነቱ ማሳያ ኣስረጅ ናቸው።
ስቅለተ ክርስቶስ ነፍሶቻችን ወደ ግዞት ቤት ሳይሆን ወደ ገነት እንዲገቡ፣ የሚቀበላቸውም ራሱ እግዚአብሔር እንዲሆን ያስቻለ ታላቅ መለኮታዊ ፍጻሜ ነው፤
እኛ “ክርስቶስ መድኃኒታችን ነው፤ ኣድኖናል” ብለን በልበ ሙሉነት የምንመሰክረው፣ እሱም “ሰላሜን ሰጠኋችሁ” ብሎ የሚያረጋጋን በመሰቀሉ ይህንን ውጤት ስላስገኘልን ነው።
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!
የድኅነታችንና የሰላማችን መሠረት የሆኑትን የክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ለዓለም ማኅበረ ሰብ የማብሰርና የማሥረጽ ተግባር የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቍጥር ኣንድ ተልእኮ ነው፤
ነገረ ሞቱና ነገረ ትንሣኤው በኣስተውሎት፣ በጥልቀትና በተመሥጦ ስናስተምር በውስጡ የምናገኘው የዕርቅ፣ የሰላምና የኣንድነት ምስጢር ነው፤
እንደ እውነቱ ከሆነ እኛ የክርስቶስ መልእክተኞች እንደ ቃሉ ራሳችንን ክደን በሚጠበቀው መጠን ተልእኮኣችንን መወጣት ብንችል ኖሮ፣ ኣሁን በዓለማችን የተፈጠረው መለያየትና ግጭት ኣይኖርም ነበር፤
ችግሩን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ባንችልም በእጅጉ መቀነስና ዓቅሙን ማዳከም እንችል ነበር፤ ነገር ግን ተልእኮኣችንን በኣግባቡ ኣለመወጣት ኣንድ ነገር ሆኖ የዓለሙ መሳሪያ ሆነን መገኘታችን “በዕንቅርት ላይ…” ሆኖ ይስተዋላል።
ይሁንና ኣሁንም ሕዝቡን ወደ ኣንድነት፣ ወደ ፍቅር፣ ወደ ሰላም፣ ወደ ዘላቂ የጋራ ጥቅምና ወደ ፈሪሐ እግዚአብሔር ማምጣት የጉባኤያችን ዓቢይ ተግባር ሊሆን ይገባል፤ እነዚህ ካሉ የምናጣውም ሆነ የሚያመልጠን የለምና ነው፤
ሃገርን በኃላፊነት ተረክባችሁ በላዕላዊ፣ በማእከላዊና በታሕታዊ መዋቅር የምትገኙ፣ እንደዚሁም ኣማራጭ ሓሳብ ኣለን ብላችሁ የምትንቀሳቀሱ ልኂቃነ ሃገር ፣ ሁላችሁም እግዚአብሔርን ከሚያውቅ፣ ከሚያመልክና ከሚፈራ ሕዝብ የተገኛችሁ ናችሁና በልባችሁ እግዚአብሔርን ፍሩ፤ ድምፁንም ስሙ፤ የሱ ገንዘብ በሆኑ ፍጡራንም ኣትጨክኑ፤ ሰውን መያዝ የሚቻለው ኅሊናን በመርታት እንጂ በሌላ ኣይደለምና፣
የሕዝቡን ፍላጎትና የልብ ትርታ በሚገባ ኣዳምጡ፤ ሕዝቡ የሚፈልገው በኣንድነትና በእኩልነት መኖር፣ በሰላም ወጥቶ መግባት፣ ፍትሕን ማስፈን፣ ለኑሮው የሚበቃ ምጣኔ ሃብትን ማግኘት፣ የእምነት ነጻነትና እኩልነት መረጋገጥ የመሳሰሉት ናቸው።
ሕዝቡ እነዚህ ከተሟሉለት ተደመጠ ማለት ነው፤ ከተደመጠ ደግሞ እሱም በበኩሉ ያደምጣል፤ ይከተላልም፤
ስለሆነም ለሁሉም ልጆቻችንና ወገኖቻችን የምናስተላልፈው ወቅታዊ ጥሪ ሁሉንም ችግሮቻችን በሰላምና በሰላም ብቻ ለመፍታት ተባበሩ የሚል ነው፤ ከዚህ ውጭ የሚደረገው ኣማራጭ ሁሉ ለዘላቂ ሰላማችን ኣይበጅም እንላለን።
በመጨረሻም፦
በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ከበዓለ ትንሣኤ በኋላ በሃያ ኣምስተኛው ቀን የሚካሄደው ዓመታዊው የረክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑና ለመላው ኢትዮጵያውያን እናበስራለን!!!
እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሓት ለእግዚአብሔር፤
አሜን!!!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤
ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም
ኣዲስ ኣበባ - ኢትዮጵያ

https://youtu.be/fKzcu7PAwXU
05/05/2026

https://youtu.be/fKzcu7PAwXU

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

ከ485 ዓመታት በፊት የተመሠረተው ቤተክርስቲያን በፍሳሽ ምክንያት የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበታል፡፡ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ)በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ላ...
04/05/2026

ከ485 ዓመታት በፊት የተመሠረተው ቤተክርስቲያን በፍሳሽ ምክንያት የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበታል፡፡

ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ)

በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ላስታ ወረዳ ቤተክህነት የኩልመስክ ደብረ ፀሐይ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በ1530ዎቹ እንደተመሠረተ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

በዚሁ ቤተክርስቲያን ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴን ጨምሮ ነገሥታትና ገዥዎች ያበረከቷቸው ከወርቅ፣ ከብር፣ ከመዳብና ከነሐስ የተሠሩ በርካታ የከበሩ ንዋያተ ቅድሳትና የብራና መጻሕፍት ጥንታዊነቱን እያስረዱ ጥበቃና እንክብካቤ እየተደረገላቸው በሙዚየም ተቀምጠዋል፡፡

በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ የቦታው ተወላጆች በራሳቸው ተነሳሽነት የቤተክርስቲያኑን ጥንታዊነት የሚመጥን መንበር ከ650 ሽህ ብር በላይ በሆነ ወጭ አሠርተው ትናንት ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአባቶች ቡራኬ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡

በእግዚአብሔር ተአምር በ1951 ዓ.ም የፈለቁ አራት ቀዝቃዛና አንድ ሙቅ ጸበሎች ከኦርቶዶክሳዊያን ባሻገር የሌላ እምነት ተከታዮች ከተለያዬ ደዌ እየተፈወሱ ምስክርነትም እየሰጡ ሲሆን ወጣቶች ተደራጅተው ለሕሙማን ምቹ እንዲሆን እያለሙት ይገኛሉ፡፡

የደብሩ አገልጋይ ካህናት፣ ምእመናን፣ በውጭ ሀገርና በሀገር ውስጥ የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች ከአባቶቻቸው የተረከቡትን ታሪክ ለመጠበቅና አዲስ የታሪክ አሻራ ለማስቀመጥ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ የሀገረ ስብከትና የወረዳ ቤተክህነት ልዑካን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

ቀደምት አባቶቻችን ያቆዩትን ታሪክ እየጠበቀ የራሱን አዲስ አሻራ ለማስቀመጥ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የገለጸው የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ከዛሬ 485 ዓመታት በፊት የተመሠረተው ጥንታዊው የቅድስት ሥላሴ ቤተ መቅደስ በዝናብ ፍሳሽ ምክንያት የገጠመው የመፍረስ አደጋ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሮብናል ብለዋል።

በፍሳሽ ምክንያት ቤተመቅደሱና መገልገያ ንዋያተ ቅድሳቱ እየተጎዱ በመሆኑ ጣራውን በአዲስ መልክ ለመሥራት፣ አዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ለማቋቋምና የምእመናንን ቁጥር ታሳቢ ያደረገ ተጨማሪ አብያተክርስቲያን ለመገንባት ዝግጅት እያደረገ መሆኑንም ሰበካ ጉባኤው ለልዑካኑ ገልጿል፡፡

የሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ዋና ጸሓፊ ሊቀ ጠበብት አበበ ካሣው ባስተላለፉት መልእክት ሰበካ ጉባኤው የደብሩን ታሪክ በመጠበቅና የቤተክስቲያኗን አገልግሎት ለማፋጠን በእቅድ ላይ የተመሠረተ ሥራ እያከናወነ በመሆኑ አመስግነዋል፡፡

የሰበካ ጉባኤውን የቀጣይ እቅድ ለማሳካት ሀገረ ስብከቱና ወረዳ ቤተክህነቱ መዋቅራዊ ድጋፍ እንደሚያደርግ የገለጹት ዋና ጸሓፊው ካህናት፣ ምእመናን፣ ወጣቶች፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች የዕውቀት፣ የገንዘብና የጉልበት አሥራታቸውን በማውጣት ለቤተክርስቲያኑ ልማት የበኩላቸውን መንፈሳዊ ኀላፊነት እንዲወጡም አሳስበዋል፡፡

መንበሩን ለማሠራት የጊዜ፣ የእውቀት፣ የገንዘብና የሀሳብ አስተዋጽኦ ላበረከቱ በጎ አድራጊዎች በሰበካ ጉባኤው የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
_______________________________
~ “ ” ~
~ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ~
____________________________
የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ፦
ቴሌግራም~ https://t.me/NWDnews
ዩቲዩብ~ https://youtube.com/c/NorthWolloDioceseMedia
ድረገጽ~ https://eotc-nw.org
ፌስቡክ~ https://www.facebook.com/EOTCNWD
Tiktok~ https://www.tiktok.com/.north?_t=ZM-8ukkHRXMOYg&_r=1

Address

Woldia

Telephone

+251946203517

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሰሜን ወሎ ሀገረስብከት ሚዲያ - North Wollo Diocese Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ሰሜን ወሎ ሀገረስብከት ሚዲያ - North Wollo Diocese Media:

Share