23/05/2026
የአስተዳደር ጉባኤ አባላቱ በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ጎበኙ።
ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ)
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የአስተዳደር ጉባኤ አባላት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ዛሬ ጎብኝተዋል።
በዋና ሥራ አስኪያጁ ክቡር መልአከ ብርሃን ፍሥሐ ጌታነህ መሪነት በተካሄደው የመስክ ጉብኝት ሀገረ ስብከቱ በከፍተኛ በጀት እያስገነባቸው የሚገኙ ፕሮጀክቶች ተጎብኝተዋል።
በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ አባታዊ መሪነት እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት እየተከናወኑ ስለመሆኑና በግንባታ ሒደት ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለይቶ የመፍትሒ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ታስቦ የጉብኝት መርሐ ግብሩ መዘጋጀቱን ዋና ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
የጉባኤ አባላቱ 300 ወንዶችና 100 ሴቶች ደቀመዛሙርትን ተቀብሎ ለማስተማር ታስቦ እየተገነባ የሚገኘውን አዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት፣ ባለ ሰባት ወለል ሁለገብ የገበያ ማእከል፣ የዘመናዊ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ፣ የመንበረ ጵጵስና ግንባታዎችና እድሳት አፈጻጸም እንዲሁም የኢንቨስትመንት ቦታ ጎብኝተዋል።
ፕሮጀክቶቹ በተቀመጠላቸው ጊዜ በውጤታማነት እንዲፈጸሙ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎችና ኮሚቴዎች በትኩረት እንዲሠሩ ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቷል፤ የአፈጻጸም አቅጣጫም ተቀምጧል።
_______________________________
~ “ ” ~
~ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ~
________________________________
የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ፦
ቴሌግራም~ https://t.me/NWDnews
ዩቲዩብ~ https://youtube.com/c/NorthWolloDioceseMedia
ድረገጽ~ https://eotc-nw.org
ፌስቡክ~ https://www.facebook.com/EOTCNWD
Tiktok~ https://www.tiktok.com/.north?_t=ZM-8ukkHRXMOYg&_r=1