Harbu Chulule Full Gospel Believer's Church

Harbu Chulule Full Gospel Believer's Church Harbu Chulule Full Gospel Believer's Church

On Harbu Chulule Full Gospel Believer's Church page we post & share new events or information in that church and we proclaim the word of God.

22/03/2021

KOONFIRAANSII HAFUURAA
"Ilmi namaa isa bade barbaaduudhaaf fayyisuudhaafis dhufeera". (Luq 19:10)
Waldaa Amantoota Guutuu Wangeela Harbuu Cululleetti
Koonfiraansiin Hafuuraa Bitootessa, 24-26/2013 turu qophaa'ee waan jiruuf
☞ Jimaata Sa'aatii 9:00 irraa eegaltanii,
☞Sanbata Xiqqaa fi Dilbata guyyaa guutuu
argamuun eebba Waaqayyoo akka hirmaattan hundi keessan affeeramtanii jirtu.

17/05/2020

ይህ በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ዋና ጽ/ቤት በየሳምንቱ እየተዘጋጀ የሚቀርብላችሁ መልእክት ነው፡፡

ነፍስን የሚዋጋውን ማሸነፍ
1ኛ ጴጥ 2፡11
በህይወት ጉዞአችን በእኛ ውስጥ ያሉ ብዙ የሚዋጉን ነገሮች እንዳሉ አስተውለን ይሆን? እነዚህ ነገሮችም በተለይ ህይወትን ሊያጠፉ ከጌታ የተቀበልነውን ማንነትና አገልግሎት አቅጣጫና መስመር ሲያዛቡ የሚችሉ ነገሮች መሆናቸውንስ እንገነዘባለን? ለምሳሌ፡-
1. ሀፍረት
2. ፍርሀት
3. ተስፋ ቢስነት
4. ምሬት/ መራርነት
5. ዋስትና/ጥበቃ ማጣት
እነዚህ ነገሮች ተስፋ እንድንቆርጥ የሚያደርጉን ናቸው፡፡ ሮሜ 7፡10-25 እኔ ላደርገው የሚገባኝን እንዳላደርግ እንዲሁም ማድረግ የሌለብኝን ሳደርግ እገኛለሁ ታድያ ከዚህ ማን ሊያወጣኝ ይችላል? እነዚህን ነገሮችን አሸንፈን ለመውጣትና እንደሚገባ ለመመላለስ ማድረግ የሚገቡንን ነገሮችን ልብ ብለን መመልከትና መፍትሔ መፈለግ አለብን፡፡
በሮሜ 8 መሰረት ከላይ የተዘረዘሩትን ድል ለማድረግ ፡-
1. ጌታ ለኔ የደረገውን በየእለቱ ማሰብ፡- ሮሜ8፡ 1-4
2. አስተሳሰብችንን መቀየር፡ ሮሜ8፡5 -8፣ ሰው የሚኖረውና የሚወሰነው ባለው አስተሳሰብ ነው በመሆኑም አስተሳሰባችን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድና እንደ መንፈስ ቅዱስ ሀሳብ ሊሆን ይገባል ይህንን ካልሆነ ግን በስጋዊ ሀሳብ እንጠቃለን፡፡
i. ዘኁ13፡33
ii. ፊል 2፡5፣ 4፡8
3. ነገሮችን አይሆንም ለማለት የሚያስችል ብቃት እንዳለን መረዳት፡- ሮሜ 8፡9-12 የመጀመሪያው መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ስላለ ኃጢአትን አላደርግም እምቢ የማለት ብቃት ይሰጠናል፡፡ ከዚያም ባሻገር መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ ስለሚኖር ክፉን ለማሸነፍ አቅም ይስጠናል፡፡
4. ፍርሀት ሲሰማኝ ሁሉን ለጌታ መስጠት አለብኝ፡- ሮሜ 8፡14-አባ አባት ብለን የምንጠራበት የልጅነት መንፈስ ተሰጥቶናልና፡፡ ሁሉን የሚችል አባት ስላለን ሁሉንም ለእርሱ አሳልፈን እንሰጠዋለሰን፡፡
5. አርቀን ማሰብ አለብን፡- ሮሜ 8፡17-18 ይበልጥ በጠንቀቅ ያለብን አሁን ስሚሆነው ጉዳይ ሳይሆን ዘለዓለማዊ የሆነው ርስታችንን መረዳት ለዚያ ራሳችንን ለማዘጋጀት መሆን አለበት፡፡
6. እግዚአብሔር ሁሉም ነገር በቁጥጥሩ ስር ነው፡- ሮሜ 8፡19-25 በዙሪያችን ያለው ሁሉ መልካም ባይሆንም እግዚአብሔር ግን ሁሉንም ለበጎ ይቀይረዋል፡፡
7. የእግዚአብሔር ፍቅር መቼም ጊዜ ቢሆን አይለወጥም፡- ሮሜ 8፡38-39

ጥያቄና አስተያየት ካላችሁ በአድራሻችን ላኩልን፡፡

ጌታ ይባርካችሁ፡፡

17/05/2020

ይህ በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ዋና ጽ/ቤት በየሳምንቱ እየተዘጋጀ
የሚቀርብላችሁ መልእክት ነው፡፡
በህብረት የሚገኝ በረከት
ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ መልካም ነው፡ ….… በዚያ እግዚአብሔር በረከቱን ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዝዞአልና። መዝ 133፡1-3

እግዚአብሔር ከምንም በላይ በህብረታችን ወይም በግንኙነታችን ደስ ይሰኛል፡፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት በተለይ በአዲስ ኪዳን እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ የማዳን ስራ ማለትም ወደ ዘለዓለም ህይወት ወደራሱ ያመጣቸውን ሰዎች ከእርሱ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በአራት መልኩ ይገልጸዋል፡፡
1. ሕያዋን ድንጋዮች፡-
ይህ ክፍል የሚነግረን የእግዚአብሔር ሕያዋን ቤተመቅደስ ሆነን ለመሰራት አንዳችን ለአንዳችን መያያዝ የግድ መሆኑን ነው፡፡ አንድን ቤት ለመስራት ግንኙነት ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ ሕንጻ ሆነን ለመቀጠል እርስ በርስ መያያዝ ተገቢ ነው፡፡ በተለይ በአዲስ ኪዳን እርስ በርሳችሁ የሚለውን 58 ጊዜ ተጠቅሶ እንመለከታለን፡፡
ሀ. ኤፌ 1፡23
ለ. ሮሜ 12፡5
ሁሉም ግንኙነቶች ለምሳሌ፡- የጋብቻ፣ የቤተሰብ፣ የንግድ ሽርክና…… ይቀራሉ ወይም ይቀየራሉ የእግዚአብሔር ማደርያ የመሆን ግንኙነት ግን የማይቀየርና ዘለአለማዊ ነው፡፡
1ቆሮ 3፡15/ኤፌ2፡21-22 ባለው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በግል ቤተክርስቲያን ለመሆን የሚቻል ጉዳይ አለመሆኑን እንረዳለን፡፡ ሕንጻ ሆኖ ስለመሰራት ስናስብ የተሰወኑ ነገሮችን ማንሳት ተገቢ ነው ከእነዚህ መካከልም ዋናው አንዱን ከሌላው ጋር ማያያዝ ነው
አብሮ በመኖርና በመጋባት መካከል ልዩነት እንዳለው ሁሉ አካል በመሆንና በቤት ውስጥ በመገኘት መካከልም እንዲሁ ነው፡፡ ይህን ህያዋን ዓለት ሆነን የምንጋጠምበት ቤት በተመለከተ ቃሉ እንዲህ ይለናል፡፡ 1ጢሞ 3፡15 … ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።.. ዓምድና መሰረት ጥንካሬና ጽናትን የሚያመላክቱ ናቸው፡፡ በመሆኑም የግንኙነት የመጀመርያ ጥቅሙ ጽናትና ጥንካሬን ማስገኘት ነው፡፡

2. የክርስቶስ አካል ፡- ኤፌ1፡22-23፣ 4፡25፣ ሮሜ12፡4-5
ከዚህ ክፍል የምንረዳው በአካሉ ማለትም በቤተክርስቲያን የሚታዩም ሆነ የማይታዩ የሰውነት ብልቶች አሉ፡፡ ጤነኛ የምንሆነው ግን ሁሉም ጤናማ ሆነው በመስራታቸው ነው ፡፡
• ከአካል ውጪ መሆን ከጥቅም ውጪ መሆን ብቻ ሳይሆን ከሕይወት ውጭ መሆንም ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ከአካሉ ውጪ ስለሆኑ ሰዎች የሚነግረንን እንመልከት፡፡ ቆላ 2፡19
• የአካሉ ክፍል በመሆን ሕይወትና እድገትን አገኛለሁ
• አንዳንድ ሰዎች የተለያየ ቤተክርስቲያን የፕሮግራም ተከታታዮች የአንድ አጥቢያ ቤተክርስቲያን አካል ስለማይሆኑ የአካሉን ሙሉ ጥቅም አያገኙም፡፡ በተለያየ ጤናማ ቦታ ቃሉን መስማት መልካም ቢሆንም አንድ ቦታ መሆን ከአካሉ የምናገኘውን ጥቅም በተሟላ መልኩ እንድናገኝ የሚረዳና ለአካሉም የሚፈለግብንን ጥቅም ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡
3. ግንድና ቅርንጫፍ፡- ከክርስቶስ ኃይል ጋር መያያዝ ዮሐ15፡4-5
ቅርጫፍ መሆናችንን ካመንን ሁልጊዜ ከግንዱ ጋር መጣበቅ መቻል አለብን፡፡ ስንጣበቅ ሀይል እናገኛለን ፍሬ ማፍራት እንችላለን፡፡ በህይወታችን የምንሻውን መንፈሳዊ ፍሬ ማፍራት ከባድ ከሆነብን መፍትሄ የሚገኘው ከግንዱ ጋር በመጣበቅ ብቻ ነው፡፡ ስንጣበቅ አብዝተን እንድናፈራ ያግዘናል፡፡
4. የእግዚአብሔር ቤተሰብ፡-
እንደ ዮሐ 1፡12 ስለተወለድን ቤተሰባዊ ግንኙነት መጀመር ደግሞ ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ ቤተሰባዊ ግንኙነት ማለት ከወላጃችን እና ከቤተሰቡ አባላት ጋር የሚኖረን ህብረት ማለት ነው፡፡ ደግሞም ቤተሰብ ለመሆናችን መለኮታዊ ማረጋገጫ ማግኘት ተገቢ ጉዳይ ነው፡፡ ሮሜ8፡16፣ 1ጢሞ 3፡15 ወገኖቼ እንደቤተሰብ ከጌታ ጋር ያለን ህብረት ምን ይመስላል? በአግባቡ በጸሎትና ቃሉን በማንበብ ከዚያም ባለፈ በጾምና በጸሎት የምናሳልፍበት ጊዜ አለን ወይ? ህብረታችንን ለማጠናከር ጌታ ይርዳን፡፡
ጥያቄና አስተያየት ካላችሁ በአድራሻችን ላኩልን፡፡

ጌታ ይባርካችሁ፡፡

17/05/2020

ይህ በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የቤተክርስቲያን እድገትና እረኝነት አገልግሎት በየሳምንቱ እየተዘጋጀ የሚቀርብላችሁ መልእክት ነው፡፡

በሞት ጥላ መካከል ስራመድ ምን እናድርግ?

″እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል። ” መዝ 23፡1-4

ከመቼውም ጊዜ ይልቅ አሁን ያለንበት ሁኔታ በተለይም ያለፉት ሁለት ወራት ዓለም ሁሉ በሞት ጥላ መካከል የሚመላለስበት ወቅት እንደሆነ እንረዳለን፡፡ ምክንያቱም አሁን በመላው ዓለም ያለው ወረርሽኝ ሀብታም ድሀ ወንድ ሴት፣ ነጭ ጥቁር አይልም ሁሉንም የሰው ዘር የሚገድል ከመሆኑም ባሻገር ቫይረሱ በምን ዓይነት መንገድ ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍ ያለን እውቀት አናሳ ነው፡፡ ነገር ግን በዚህ ወቅት አንድ መረዳት ያለብን ጉዳይ ቢኖር ቤተክርስቲያን የማትናወጥ የክርስቶስ አካል እንደመሆንዋ መጠን በዚህ መከራ ውስጥም ብንሆን ማለፍ ባለብን መንገድ ሁሉ ልናልፍ የሚገባን ቢሆንም ነገር ግን ማድረግ እና መረዳት ያለብን ነገርች እንዳሉ እንመለከታለን እነዚህም፡፡
1. የሚሰማው ሁሉ እውነት አይደለም፡- ምሳ 14፡15
• የሚባውን ሁሉ ማመን ሳይሆን ነገር ግን መምረጥ ነው ያለብን
• በዚህ ሰዓት አንዳንዱ የራሱን ፖለቲካ አጀንዳ፣ የራሱን ገንዘብ ለማሰባሰብ፣ አንዳንዱ ከክፉ ተልኮ ሰው እንዳይጠነቀቅ ለማድረግ የተላከ፣ አንዳንዱ በተለያየ መንገድ ገንዘብ ለማካበት የሚሄድበት መንገድ ሊሆን ስለሚችል የተባለው ሁሉ ከማመን ይልቅ በተለይ እውነተኛ ከሆነ ምንጭ መስማት ተገቢ ጉዳይ ነው፡- ምሳ 13፡16
• ድርጊቶቻችንን በእውነት ላይ መመስረት መቻል አለባቸው፡- ምሳ 18፡13.2፣ 14፡8፣ 23፡23
2. በዚህ ወቅት ችግሩ በአንዳንድ ሰዎች ላይ የከፋ ጉዳት ሊያመጣ ይችላል፡- አስከ ከአሁን በወጡ የተለያዩ መረጃዎች እንደምንሰማው በሽታን የመከላከል አቅማቸው ደካማ የሆኑ ሰዎች ከሁሉም ይልቅ ተጠቂዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም ችግሩ አስኪያልፍ በቤት ውስጥ ተቀመጡ ከተባልን መቀመጥ ግድ ነው፡፡ ኖቪል ኮሮና አዲስና እንግዳ ክትባትም መድሀኒትም ያልተገኘለት በሽታ ነው፡፡ በየት በኩል እንደሚመጣ ስለማናውቅ እንድናደርግ የተጠየቅነውን በማድረግ መራመድ መቻል አለብን፡፡
3. ይህ ወቅትና ጊዜ ያልፋል፡- 1ጴጥ 4፡12 ነገር ግን ያልፋል ብለን መዘናጋት ሳይሆን በጥንቃቄ መመላለስ መቻል አለብን፡፡ የዚህ ችግር ምክንያት ከእግዚአብሔር መንገድ ፈቀቅ ማለታችን እንደሆነ በግልጽ የምንረዳው ጉዳይ ነው ኢሳ 24፤5.19፣ 2ቆሮ4፡17-18
4. ሁሉን ለበጎ መለወጥ በሚችለው ጌታ ላይ ዓይናችንን እናድርግ፡- በዚህ በሽታ ምክንያት በዓለማችንም በምድራችንም ብዙ ለውጦችን እንመለከታለን ነገር ግን በዘመናት የማይለወጠውን እግዚአብሔርን መመልከት ተገቢ ነው፡፡
• የሚሆነውን ሁሉ ሁሉ እግዚአብሔር ያያል
• እግዚአብሔር ያያል ይጠነቀቅልኛልም
• እግዚአብሔር ነገር ሁሉ ይለውጣል
• እግዚአብሔር ከመልካምነቱ ያጠግበኛል
• በዚህ ሁሉ የክፉ ሀሳብ ሳይሆን የእግዚአብሔር እቅድ ይፈጸማል፡፡ ከፉ የቱንም ያህል ቢበረታ ከእግዚአሔር ፈቃድ ውጭ ምንም አያደርግም፡፡
5. እግዚአብሔር አብሮኝ አለ፡- ኢሳ 43፡2
6. ይህ የታሪክ ፍጻሜ አይደለም፡- 2ቆሮ 4፡8-14 ምክንያቱም በዚህ ብናልፍ እንኳን በሰማይ ሀገር አለን፡፡
7. እግዚአብሔር በዚህ ወቅት ሌሎችን ለማገዝ የሚጠቀመው እኔን ነው፡-
• የሮም መንግስት ክርስትናን የተቀበለው ጥቁር ወረርሽኝ በመጣ ጊዜ ሰው ሁሉ ከከተማ ሲወጣ ክርስቲያኖች ወደከተማ ገብተው ህዝቡን ስለረዱ ነው ፡፡

1. እግዚአብሔር በዚህ ወቅት እኛ ምን እንድናደርግ ይፈልግ ይሆን ?
2. እግዚአብሔር በትልቁ ዘለአለማዊ አጀንዳው ውስጥ ዛሬ ላይ ምን እየሰራ ይሆን?
በቤታችሁና አቅራቢያችሁ ካሉ ወገኖች ጋር ተወያዩበት፡፡ ጌታ ማስተዋሉን ይስጠን፡፡

ጥያቄና አስተያየት ካላችሁ በአድራሻችን ላኩልን፡፡

ጌታ ይባርካችሁ፡፡

17/05/2020

ይህ በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የቤተክርስቲያን እድገትና እረኝነት አገልግሎት በየሳምንቱ እየተዘጋጀ የሚቀርብላችሁ መልእክት ነው፡፡

ረዳቴ ከወዴት ይምጣ?

”ዓይኖቼ ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ? ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም። እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም። እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፥ እግዚአብሔርም በቀኝ እጅህ በኩል ይጋርድሃል። ፀሐይ በቀን አያቃጥልህም ጨረቃም በሌሊት። እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፥ ነፍስህንም ይጠብቃታል። ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔር መውጣትህና መግባትህን ይጠብቃል።″ መዝ121፡1-8

ይህ መዝሙር እግዚአብሔርን ለማምለክና ለማገልገል ወደኢየሩሳሌም መንፈሳዊ ጉዞ በሚጓዙ አማኞች የተዘመረ መዝሙር እንደሆነ ይታመናል፡፡ ዛሬም ወደ እግዚአብሔር መንግስት ለመግባት ከጌታ ጋር መንፈሳዊ ጉዞ የጀመርን መንገደኞች እግዚአብሔር እረዳታችን ሲሆን የምናገኛቸው ጥቅሞች ምን እንደሆኑ የሚሰጠንን ትምህርት እንያለን፡፡
1- “እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ ቁ.3 ” የእርሱ ቃልና የእርሱ መንገድ እርግጠኛ መሰረት ስለሆነ ልንታመነው ይገባል፡፡ ስለዚህ የተረዳንውን እውነት አጥብቀን መያዝ፡፡
2- “የሚጠብቀን አይተኛም አያንቀላፋምም።ቁ.4” እኛን የሚወስኑን ነገሮች ለምሳሌ እንቅልፍ እርሱን አይወስኑትም፡፡ እግዚአብሔር ሁል ጊዜ ፈቃዱን ለማድረግ በስራ ላይ ነው፡፡ እርሱን ስናመልክና ስንገለግል ጌታን አልፎና አሸንፎ ወይም ሳይታይ አምልጦ ወደእኛ ሊመጣ የሚችል አንዳች ክፉ ኃይል የለም፡፡
3- “እርሱ ከለላችን ነው/ ይጋርደናል ቁ.5፣6” እርሱን ስናመልክና ስንገለግል በቀንም በሌሊትም ከአደገኛ ነገሮች ሁሉ ይከልለናል፡፡
4- “ከክፉ ሁሉ ይጠብቀናል፥ ቁ.7” እግዚአብሔር ሊጠብቀን አጠገባችን ስላለ አንፈራም፡፡ በአጉል ፍርት ውስጥ መግባት የለብንም፡፡
5-“ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔር መውጣትህና መግባትህን ይጠብቃል።” ቁ.8 እግዚአብሔር መንገዳችንን ሁሉ ያውቃል፡፡ እርሱን ስናመልክና ስንገለግል የእርሱ ጥበቃ ሁልጊዜም አይለየንም፡፡

እነዚህ ተስፋዎች በቃሉ ውስጥ ሳላሉን በዚህ ወቅት የእኛ ድርሻ፡-
1. እርሱን ማምለክና ማገልገል፡- ከመጨነቅ ይልቅ በፍጹም ልባችን እርሱን ማምለክና ማገልገል ፡፡ “እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ እሹ፤“ ቆላ 3፡1-2 በሚለው ቃል ልባችንን ማስተካከል፡፡
2. በትዕግስት መጠበቅ፡- እርሱን በመተማንና መስራት ያለብንን ሁሉ በንቃት እየሰራን መጠበቅ፡፡ ጠቢባን ከነገሩን በላይ አሁን ላሉብን ተግዳሮች የእግዚአብሔር ዓላማ ምን እንደሆነ ለማወቅ እና ምን ማድረግ እንዳለብን ጌታ አላማውን እንዲገልጽልን በጉጉት፤በጸሎትና በንጹህ ህሊና መጠበቅ፡፡ በብዙ ሆነን በአምልኮ ቦታዎች መሰብሰብ ባንችልም ከቤተሰባችን ጋር ጊዜውን በአግባቡ መጠቀም፡፡
3. በቃሉ ውስጥ በምናገኘው ጥበብ ዘመኑን መዋጀት፡- ጥብበ በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ አለ፡፡ እግዚአብሔር በቃሉ እንደሚናገረን በማወቅና የሚናገረንን በመስማት በተስፋ ቃሉ መታመን፡፡ ”እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ።”ኤፌ5፡15-16 ″…ጥበብ በዚህ አለ። .. አእምሮ ያለው ……ቍጥር(ሩን) ይቍጠረው፤″ ራዕ13፡17-18፡፡ አሁን ላለንበት ሁኔታ ሚዲያውና ነገስታት ከሚነግሩን ባሻገር በጥሞና እና በቃሉ ዘመኑን በመመርመር ለጌታ ምጽአት በመዘጋጀት መኖር ምክኒያቱም የጉዞአችን መዳረሻ ላይ ነንና፡፡
4. በመሰጠትና ባለን አቅም መስራትና መመስከር፡- በሁኔታዎች ግራ የተጋቡ ሰዎች መጽናናትን ይፈልጋሉ፡፡ እንደጌታ አገልጋዮች ለሌሎች ልንጠነቀቅና ሌሎችን በቃሉ ልናበረታታ ይገባል፡፡ የወንጌልን እውነት በቃልና በተግባር እየኖርን በመመስከር ሰዎች ሁሉ ወደመንግስቱ አብረውን እንዲጓዙ መጋበዝ ይጠበቅብናል፡፡

”እንግዲህ ….. አንተ በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው ጸጋ በርታ።″ 2ጢሞ2፡1

ጥያቄና አስተያየት ካላችሁ በአድራሻችን ላኩልን፡፡

ጌታ ይባርካችሁ፡፡

17/05/2020

ይህ በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የቤተክርስቲያን እድገትና እረኝነት አገልግሎት በየሳምንቱ እየተዘጋጀ የሚቀርብላችሁ መልእክት ነው፡፡
ለተቸገሩ ማካፈል
1. መግቢያ
በዚህ ወቅት ቀለም፣ዘር፣ሐይማኖት ፣ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ሁኔታ ሰይለይ ሁሉን እገደለ ያለውና በፍጥነት እየተሰራጨ ያለው ኮሮና ቫይረስ የሀገራትን ሰዋዊ እሴት /human capital/ ፣ ማህበራዊ እሴት /spcial capital/ እና ኢኮኖሚ እያደቀቀና እያወደመ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያም መሰረታዊ ጥናት እንደሚያመለክተው ከታቀደው የኢኮኖሚ እድገት ከ2.8-3.8 በመቶ ሊቀንስ እንደሚችል ተተንብዮአል፡፡ በዚህ ጊዜ በቅድሚያ የሚጠቁት ቀድሞውኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ ችግረኞችን፣ አካል ጉደተኞች፣ ባልቴቶች፣ ወላጅ የሌላቸው ልጆች፣ ጎዳና ተዳደሪዎች ወዘተ እንደሆኑ አያጠያይቅም፡፡ ምንግስትም ይህን ተገንዝቦ እግዚአብሔር የባረካቸው ሰዎች ለችግሩ ገፈት ቀማሾች የቸርነት እጃቸውን እንዲዘረጉ ጥሪ አቅርቦ የሚያስደስት ምላሾች እየተገኙ ነው፡፡
ይህ ወቅት እምነት የሚፈተንበት ነው፡፡ ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ከስራ የተለየ እምነት ከንቱ ነው የሚለው፡፡ አምላከችንን ከቃል ያለፈ በተግባር መውዳዳችንን የምንገልጥበት፣ ባልንጀራችንን እንደራሳችን መውዳዳችንን የምንገልጥበት እድል አሁን በፊታችን አለ፡፡ የእምነታችን ዘላቂነትና እውነተኛነት፣ ደግሞም መታዘዛችን የሚገለጥበት ወቅት ነው፡፡ ስለዚህ በዚህች አጭር ጽሁፍ ውስጥ ለተቸገሩ ማካፈል በሚል ርእስ እንማራለን፡፡
2. ለተቸገሩ የሚራራ ልብ
2.1. የርህራሄ ልብ ፡ ባለንጀራውን የሚንቅ ይበድላል ፣ ለችግረኛ የሚራራ ምስጉን ነው ( ምሳሌ14፡21)፡፡
2.2. ጭካኔን ማስወገድ፡ 1ኛ ዮሐንስ 3፡17 “ነገር ግን የዚህ ዓለም ገንዘብ ያለው ወንድሙንም በሚያስፈልገው ሲያጣ አይቶ ያልራራለት ማንም ቢሆን የእግዚአብሔር ፍቅር በርሱ እንዴት ይኖራል?
2.3. አለማዳላት፡ ያዕቆብ 2፡1-4
2.4. በተቸገሩ ሰዎች ላይ የሚደርስ ነገር በእኛ ላይ እንደደረሰ መቁጠር፡
2.5. የተቸገሩትን የመደገፍ መነሻው ርህራሄ መሆን አለበት፡ ዮሐን 12፡3-6

3. ለችግረኞች የማካፈል አስፈላጊነት፡
ችግረኛን መርዳት ሁሉም ይፈልጋል፡፡ ሁሉም ደስ ይሰኝበታል፡፡ ባህላችንም መጽሐፍ ቅዱሳችንም ያስተምረናል፡፡ ግን በማስተዋል እናደርጋለን ወይ? ለችግረኞች ማካፈል
3.1. የወንጌል አገልግሎት አካል ነው፡ ገላ 2፡10 ድሆችን እናስብ ዘንድ ለመኑን ይህንን ደግሞ ላደርግ ተጋሁ፡፡ ሐዋ 4፡33-35
3.2. የእግዚአብሔር ትእዛዝ ነው፡ ዘዳግም 15፡11 ፣ ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ ዮሐ. 14፡15 ፡፡ “ኢየሱስም ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሂድና ያለህን ሽጠህ ለድሆች ስጥ፡፡ መዝገብም በሰማይ ታገኛለህ፡፡ መጥተህም ተከተለኝ አለው (ማቴዎስ 19፡21)
3.3. ንጹህ አምልኮ ነው፡ ያዕቆብ 1፡27
3.4. የእምነት ምላሽ ነው፡፡ ያዕቆብ 2፡14-17
3.5. የመንፈስ ፍሬ ነው፡፡ ገላ 5፡22 ቆላ 3፡12 ፣ 1ኛ ቆ 16፡3
3.6. የፍቅር ምላሽ ነው 1ኛ ዮሐ3፡17-19
3.7. የጽድቅና የልባምነት ምልክት ነው ምሳሌ 29፡7
3.8. እግዚአብሔር ለድሆች አሳቢ በመሆኑ መዝ 721-13 ፣ ኢሳ 11፡4

4. ችግረኛን የመግፋት ውጤቶች
4.1. ደሃን መግፋት ያስቀጣል ህዝቅኤል 18፡12-13 ፣ ኤር 5 ፡27-29፣ምሳ 17 ፡ 5
4.2. ፍርድን ያመጣል ምሳሌ 22፡22-23፣ምሳ 23፡10-11፣ መዝ 146፡5-6፣ ምሳ 15፡25
4.3. በክፉ ቀን ቢጮህ አይሰማም ምሳ 21፡13፣ ያዕ 5፡4፣መዝ 41፡1

5. ለተቸገሩት የማካፈል ትሩፋቶች
5.1. የበረከት ምክንያት ነው ዘዳ15፡10-11፣ 14፡29፣ ምሳ 19፡17፣ ምሳ28፡27፣ ምሳ 22፡ 9
5.2. ምስጋናን ያመጣል መዝ 41፡ 1-2፣ ኢዮብ 29 ፡11-12.
5.3. መልካም ይሆናል ኤር 22፡13-16፣ ምሳ 29 ፡14
5.4. በሞገስ ከፍ ከፍ ያደርጋል መዝ 112፡9፣
5.5. እግዚአብሄርን ያከብራል ምሳሌ 14፡31 ፣ 1ኛ ሳሙ 2፡30
5.6. የፀሎት መልስ ነው ኢሳ 58፡7-9
5.7. ደስታን ይሰጣል መክበብ 2፡ 25-26

የፋሲካ በዓልን ስናከብር የተቸገሩትን መራዳትን አንርሳ፡፡ የወንጌልን እውነት በተግባራችን እንመስክር፡፡

ጥያቄና አስተያየት ካላችሁ በአድራሻችን ላኩልን፡፡

ጌታ ይባርካችሁ፡፡

እጅ ፡ ለእጃችን:- አዝ፦ እጅ ፡ ለእጃችን ፡ ተያይዘንኢየሩሳሌም ፡ እንገባለንበኢየሱስ ፡ ደም ፡ አንድ ፡ ሆነናልአንለያይም ፡ ተዋደናልመልክና ፡ ጐሳ ፡ ደም ፡ ግባት ፡ ዕውቀትከቶ ፡ አ...
15/05/2019

እጅ ፡ ለእጃችን:-

አዝ፦ እጅ ፡ ለእጃችን ፡ ተያይዘን
ኢየሩሳሌም ፡ እንገባለን
በኢየሱስ ፡ ደም ፡ አንድ ፡ ሆነናል
አንለያይም ፡ ተዋደናል

መልክና ፡ ጐሳ ፡ ደም ፡ ግባት ፡ ዕውቀት
ከቶ ፡ አይለየንም ፡ ከያዝነው ፡ እምነት
በቀራኒዮ ፡ በፈሰሰው ፡ ደም
ከእንግዲህ ፡ አንድ ፡ ነን ፡ ሰይጣንም ፡ ይፈር

አዝ፦ እጅ ፡ ለእጃችን ፡ ተያይዘን
ኢየሩሳሌም ፡ እንገባለን
በኢየሱስ ፡ ደም ፡ አንድ ፡ ሆነናል
አንለያይም ፡ ተዋደናል

በመሃላችን ፡ ገደብ ፡ ዐይኖርም
አጥር ፡ ግድግዳ ፡ አይሰራም ፡ ማንም
የኢየሱስ ፡ ደም ፡ አንድ ፡ አድርጐናል
እንዘምራለን ፡ ሃሌ ፡ ሉያ ፡ አያልን

አዝ፦ እጅ ፡ ለእጃችን ፡ ተያይዘን
ኢየሩሳሌም ፡ እንገባለን
በኢየሱስ ፡ ደም ፡ አንድ ፡ ሆነናል
አንለያይም ፡ ተዋደናል

ታላቅም ፡ ታናሽ ፡ ክፉ ፡ ጨዋ ፡ የለም
ሁሌ ፡ አንድ ፡ ሆኗል ፡ በክርስቶስ ፡ መስቀል
አባትና ፡ ልጅ ፡ አንድ ፡ እንደሆኑ
እኛም ፡ አንድ ፡ ሆንን ፡ ሲወርድ ፡ መንፈሱ

አዝ፦ እጅ ፡ ለእጃችን ፡ ተያይዘን
ኢየሩሳሌም ፡ እንገባለን
በኢየሱስ ፡ ደም ፡ አንድ ፡ ሆነናል
አንለያይም ፡ ተዋደናል

እንደመልካችን ፡ የሁሉ ፡ ጠባይ
ሁሌ ፡ አንድ ፡ ባይሆን ፡ ምንም ፡ ቢለያይ
ግን ፡ በውስጣችን ፡ የያዝነው ፡ ጌታ
እርሱ ፡ አንድ ፡ ነው ፡ አንድነን ፡ በቃ

አዝ፦ እጅ ፡ ለእጃችን ፡ ተያይዘን
ኢየሩሳሌም ፡ እንገባለን
በኢየሱስ ፡ ደም ፡ አንድ ፡ ሆነናል
አንለያይም ፡ ተዋደናል

የእግዚአብሔርን ፡ ስራ ፡ እንሰራለን
እርስ ፡ በእርሳችን ፡ አንድ ፡ ልብ ፡ ሆነን
በፍፁም ፡ የለም ፡ የሚያግደን
የመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ችቦን ፡ አንድደን

አዝ፦ እጅ ፡ ለእጃችን ፡ ተያይዘን
ኢየሩሳሌም ፡ እንገባለን
በኢየሱስ ፡ ደም ፡ አንድ ፡ ሆነናል
አንለያይም ፡ ተዋደናል

Address

Harbu Chulule, Shewa
Tulu Bolo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harbu Chulule Full Gospel Believer's Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share