20/02/2026
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ለአንድ ወር የሚቆይ ሀገር አቀፍ የጾም እና ጸሎት አወጀች
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ መሪዎች ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በመላው ዓለም የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አማኞች የሚሳተፉበት ለአንድ ወር የሚቆይ የጾም እና ጸሎት አዋጅ ይፋ አድርገዋል።
መግለጫውን የሰጡት አመራሮች፦
የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ላኮ በዳሶ
ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ለወየው ስንሻው
የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ መጋቢ ተመስገን አዋኖ
የሥራ አመራር ቦርድ ጸሐፊ መጋቢ የኋላሸት ቡኩሉ
የጸሎቱ ዝርዝር መረጃ፦
1. መርሐ-ግብሩ ከየካቲት 30 እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ አንድ ወር ይቆያል።
2. ዓላማው ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ እና ስለ ሀገር ሰላም የሚጸለይበት ሲሆን፤
*የንስሐ፣
* የምስጋና እና
* የምልጃ ጸሎቶችን ያካተተ ነው።
3. በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሚገኙ መሪዎች፣ አገልጋዮችና ምዕመናን በሙሉ በጋራ በጸሎት እንዲተጉ ጥሪ ቀርቧል።
የሥራ አመራር ቦርድ ጸሐፊ ፓስተር የኋላሸት ቡኩሉ እንደገለጹት፣ ለጸሎቱ አጋዥ የሚሆኑ ሳምንታዊ የጸሎት ርዕሶች በቤተ ክርስቲያኒቱ ይፋዊ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ በየጊዜው የሚለቀቁ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን The Ethiopian Full Gospel Believers' Church