ታርጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን Tarcha Full Gospel Local Church

  • Home
  • Ethiopia
  • Tarch'a Sodo
  • ታርጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን Tarcha Full Gospel Local Church

ታርጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን  Tarcha Full Gospel Local Church Tarcha Full Gospel Believers' Local Church is a religious Organisation in Ethiopian Full Gospel Believers' Church.

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ለአንድ ወር የሚቆይ ሀገር አቀፍ የጾም እና ጸሎት አወጀችየኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ መሪዎች ዛሬ የካቲት 12 ቀን ...
20/02/2026

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ለአንድ ወር የሚቆይ ሀገር አቀፍ የጾም እና ጸሎት አወጀች

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ መሪዎች ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በመላው ዓለም የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አማኞች የሚሳተፉበት ለአንድ ወር የሚቆይ የጾም እና ጸሎት አዋጅ ይፋ አድርገዋል።

መግለጫውን የሰጡት አመራሮች፦

የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ላኮ በዳሶ
ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ለወየው ስንሻው
የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ መጋቢ ተመስገን አዋኖ
የሥራ አመራር ቦርድ ጸሐፊ መጋቢ የኋላሸት ቡኩሉ

የጸሎቱ ዝርዝር መረጃ፦

1. መርሐ-ግብሩ ከየካቲት 30 እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ አንድ ወር ይቆያል።

2. ዓላማው ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ እና ስለ ሀገር ሰላም የሚጸለይበት ሲሆን፤

*የንስሐ፣
* የምስጋና እና
* የምልጃ ጸሎቶችን ያካተተ ነው።

3. በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሚገኙ መሪዎች፣ አገልጋዮችና ምዕመናን በሙሉ በጋራ በጸሎት እንዲተጉ ጥሪ ቀርቧል።

የሥራ አመራር ቦርድ ጸሐፊ ፓስተር የኋላሸት ቡኩሉ እንደገለጹት፣ ለጸሎቱ አጋዥ የሚሆኑ ሳምንታዊ የጸሎት ርዕሶች በቤተ ክርስቲያኒቱ ይፋዊ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ በየጊዜው የሚለቀቁ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን The Ethiopian Full Gospel Believers' Church

 ! እሁድ ጥር 24/2018 የጥዋት ክፍል  መነሻ ጥቅስ (ዘፍጥረት 50:22-26)3, ጌታን ሰምተው በሰሙት አቅጣጫ መንቀሳቀስ እና መስራት ለጀመሩት #(ትንቢተ ዘካሪያስ 4:1-10)¹ ከእኔ...
01/02/2026

! እሁድ ጥር 24/2018 የጥዋት ክፍል


መነሻ ጥቅስ (ዘፍጥረት 50:22-26)
3, ጌታን ሰምተው በሰሙት አቅጣጫ መንቀሳቀስ እና መስራት ለጀመሩት
#(ትንቢተ ዘካሪያስ 4:1-10)
¹ ከእኔም ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክ ተመልሶ ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው አነቃኝ።
² እርሱም፦ የምታየው ምንድር ነው? አለኝ። እኔም፦ እነሆ፥ ሁለንተናው ወርቅ የሆነውን መቅረዝ አየሁ፤ የዘይትም ማሰሮ በራሱ ላይ ነበረ፥ ሰባትም መብራቶች ነበሩበት፤ በራሱም ላይ ለነበሩት መብራቶች ሰባት ቧንቧዎች ነበሩአቸው።
³ ሁለት የወይራ ዛፎች፥ አንዱ በማሰሮው በስተ ቀኝ አንዱም በስተ ግራው ሆነው፥ በአጠገቡ ነበሩ አልሁ።
⁴ ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረውም መልአክ መልሼ፦ ጌታዬ ሆይ፥ እነዚህ ምንድር ናቸው? አልሁት።
⁵ ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረውም መልአክ መልሶ፦ እነዚህ ምን እንደ ሆኑ አታውቅምን? አለኝ። እኔም፦ ጌታዬ ሆይ፥ አላውቅም አልሁ።
⁶ መልሶም፦ ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው። በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
⁷ ታላቅ ተራራ ሆይ፥ አንተ ምንድር ነህ? በዘሩባቤል ፊት ደልዳላ ሜዳ ትሆናለህ፤ ሰዎችም፦ ሞገስ፥ ሞገስ ይሁንለት ብለው እየጮኹ እርሱ መደምደሚያውን ድንጋይ ያወጣል ብሎ ተናገረኝ።
⁸ የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፦
⁹ የዘሩባቤል እጆች ይህን ቤት መሠረቱ፥ የእርሱም እጆች ይፈጽሙታል፤ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔርም ወደ እናንተ እንደ ላከኝ ታውቃላችሁ።
¹⁰ የጥቂቱን ነገር ቀን የናቀ ማን ነው? እነዚህ ሰባቱ ደስ ብሎአቸው በዘሩባቤል እጅ ቱንቢውን ያያሉ፤ እነዚህም በምድር ሁሉ የሚዘዋወሩ የእግዚአብሔር ዓይኖች ናቸው።

ፕሮግራሙ ከሰዓት 09:00 ጀምሮ ይቀጥላል!

 !  ቅዳሜ ከሰዓት ጥር 23/2018 ! መነሻ ጥቅስ (ዘፍጥረት 50:22-26)2, እግዚአብሔርን በመፍራት በጽድቅ ሕይወት ከሚመላለሱ ሰዎች ይጀምራል!( #ሉቃስ 1:5-25)⁵ በይሁዳ ንጉሥ ...
31/01/2026

!
ቅዳሜ ከሰዓት ጥር 23/2018

!


መነሻ ጥቅስ (ዘፍጥረት 50:22-26)
2, እግዚአብሔርን በመፍራት በጽድቅ ሕይወት ከሚመላለሱ ሰዎች ይጀምራል!
( #ሉቃስ 1:5-25)
⁵ በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ።
⁶ ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ።
⁷ ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ አልነበራቸውም፤ ሁለቱም በዕድሜያቸው አርጅተው ነበር።
⁸ እርሱም በክፍሉ ተራ በእግዚአብሔር ፊት ሲያገለግል፥

¹³ መልአኩም እንዲህ አለው፦ ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ።
¹⁴ ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።

¹⁶ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመልሳል።

¹⁹ መልአኩም መልሶ፦ እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፤

²² በወጣም ጊዜ ሊነግራቸው አልቻለም፥ በቤተ መቅደስም ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፤ እርሱም ይጠቅሳቸው ነበር፤ ድዳም ሆኖ ኖረ።
²³ የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሄደ።
²⁴-²⁵ ከዚህም ወራት በኋላ ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰችና፦ ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል ስትል ራስዋን አምስት ወር ሰወረች።

:00_ጀምሮ_ይቀጥላል!

   ጥር 23/2018 የቅዳሜ ከጥዋት ክፍልጊዜ። በታርጫ ከተማ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን።  #አገልጋይ ፓስተር አሌክስ ወ/ሰንበትርዕስ፦ ጸሎት እና የእግዚአብሔር ሉአላዊነት(...
31/01/2026


ጥር 23/2018 የቅዳሜ ከጥዋት ክፍልጊዜ።

በታርጫ ከተማ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን።

#አገልጋይ ፓስተር አሌክስ ወ/ሰንበት
ርዕስ፦ ጸሎት እና የእግዚአብሔር ሉአላዊነት
(ትንቢተ ዳንኤል 2:17-28)
፨ ጸሎት የእግዚአብሔር ፋቃድ የምንጠይቅበት እንጂ የምንጨነቅበት አይደለም!
፨ ጸሎት እግዚአብሔርን ምህረት የምንለምንበት ነው!
፨ ጸሎት የልብ አንድነት እና ስምምነት ይጠይቃል!
፨ ጸሎት ሚስጥር የሚገለጥበት ነው!
፨ ጸሎት እግዚአብሔር የሚመሰገንበት ቦታ ነው!
፨ ጸሎት የእግዚአብሔር አጀንዳ የሚገለጥበት ነው!

ፕሮግራሙ ከሰዓት ከ9:00 ጀምሮ ይቀጥላል!

  ጥር 22/2018 የአርብ የከሰዓት ክፍልጊዜ  በታርጫ ከተማ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን። አገልጋይ ፓስተር ዋለልኝ ማርቆስርዕስ፦ እግዚአብሔር መጎብኘትን ይጎበኘናል!(ዘፍጥረ...
30/01/2026

ጥር 22/2018 የአርብ የከሰዓት ክፍልጊዜ
በታርጫ ከተማ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን።

አገልጋይ ፓስተር ዋለልኝ ማርቆስ
ርዕስ፦ እግዚአብሔር መጎብኘትን ይጎበኘናል!
(ዘፍጥረት 50:22-26)
እግዚአብሔር መጎብኘትን የሚጀምረው

1, ልባቸውን በጌታ ላይ ካበረቱት (1ሳሙኤል 2:1-10)

¹ ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች፦ ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።
² እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ የለምና፥ እንደ አምላካችንም ጻድቅ የለምና፤ ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም።
³ አትታበዩ፥ በኩራትም አትናገሩ፤ እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ እግዚአብሔርም ሥራውን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችሁ የኵራት ነገር አይውጣ።
⁴ የኃያላንን ቀስት ሰብሮአል፥ ደካሞችንም በኃይል ታጥቀዋል።
⁵ ጠግበው የነበሩ እንጀራ አጡ፤ ተርበው የነበሩ ከራብ ዐርፈዋል፤ መካኒቱ ሰባት ወልዳለችና፥ ብዙም የወለደችው ደክማለች።
⁶ እግዚአብሔር ይገድላል ያድናልም፤ ወደ ሲኦል ያወርዳል፥ ያወጣል።
⁷ እግዚአብሔር ድሀ ያደርጋል፥ ባለጠጋም ያደርጋል፤ ያዋርዳል፥ ደግሞም ከፍ ከፍ ያደርጋል።
⁸ ከሕዝቡ መኳንንት ጋር ያስቀምጣቸው ዘንድ፥ የክብርንም ዙፋን ያወርሳቸው ዘንድ፥ ችግረኛውን ከመሬት ያስነሣል፥ ምስኪኑንም ከጉድፍ ያስነሣል፤ የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና፥ በእነርሱ ላይም ዓለምን አደረገ።
⁹ እርሱ የቅዱሳኑን እግር ይጠብቃል ኃጥኣን ግን ዝም ብለው በጨለማ ይቀመጣሉ፤ ሰው በኃይሉ አይበረታምና።
¹⁰ ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቅቃሉ፤ በሰማይም ያንጐደጕድባቸዋል፤ እግዚአብሔር እስከ ምድር ዳርቻ ይፈርዳል፤ ለንጉሡም ኃይል ይሰጣል፤ የመሲሑንም ቀንድ ከፍ ከፍ ያደርጋል።

ኮንፈረንሱ ነገ ጠዋት ከ2:30 ጀምሮ ይቀጥላል! ከእግዚአብሔር ጸጋ ተካፋዮች እንድትሆኑ እንጋብዛችኋለን!

  ጥር 22/2018 የአርብ ጥዋት ክፍልጊዜ  በታርጫ ከተማ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን።አገልጋይ ፓስተር አለማየሁርዕስ፦ እምነት እና የእግዚአብሔር ሉአላዊነት!(ትንቢተ ዳንኤል...
30/01/2026

ጥር 22/2018 የአርብ ጥዋት ክፍልጊዜ
በታርጫ ከተማ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን።

አገልጋይ ፓስተር አለማየሁ

ርዕስ፦ እምነት እና የእግዚአብሔር ሉአላዊነት!

(ትንቢተ ዳንኤል 1:1-21)
ሉዓላዊ ማለት እግዚአብሔር ብቻውን ሁሉን ቻይ፣ ገዢ፣ ብቻውን አዛዥ፣ ባልስልጣን፣ ሁሉን አድራጊ እንደሆ ለመግለጽ የምንጠቀምበት ቃል ነው።

የእግዚአብሔር ሉዓላዊነት እንዲገለጥባቸው የሆነው
1, በማመናቸው!
2, የጣኦት አምልኮ ተግዳሮትን መቋቋማቸው!
3, ንጽህናቸውን መጠበቃቸው!
4, በትጋት የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ማድረጋቸው!

ኮንፈረንሱ ከሰዓት 09:00 ጀምሮ ይቀጥላል

ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።
ዕብራውያን 13፥8

     #ከጥር 21_24 በታርጫ ከተማ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን።ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።ዕብራውያን 13፥8
29/01/2026

#ከጥር 21_24
በታርጫ ከተማ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን።

ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።
ዕብራውያን 13፥8

 🙏''በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጀለህ ፥ምድር ስብን ይጠግባል። '' መዝ 85 ፥11የስልጠናና የማነቃቂያ ኮንፍራንስ በታርጫ ስታዲየም ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን።ከጥር 14_17
15/01/2026

🙏

''በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጀለህ ፥ምድር ስብን ይጠግባል። '' መዝ 85 ፥11

የስልጠናና የማነቃቂያ ኮንፍራንስ በታርጫ ስታዲየም ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን።

ከጥር 14_17

     ከታህሳስ 10_12''እግዚአብሔርን መፈለግ''በሚል ርዕስ በዩኒቨርስቲ በተማሪዎች የተዘጋጀ ትምህርታዊ ኮንፍራንስከአርብ ጀምሮ እስከ እሁድ ድረስ በታርጫ ሙሉወንጌል ቤ/ያን ተዘጋጅቷል ...
16/12/2025

ከታህሳስ 10_12

''እግዚአብሔርን መፈለግ''በሚል ርዕስ በዩኒቨርስቲ በተማሪዎች የተዘጋጀ ትምህርታዊ ኮንፍራንስ
ከአርብ ጀምሮ እስከ እሁድ ድረስ በታርጫ ሙሉወንጌል ቤ/ያን ተዘጋጅቷል ተገኝተው የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ።

ከነገ አርብ ማለትም ከታህሳስ 10_12 ድረስ ከተጋባዥ አገልጋዮች ጋር ይካሄዳል።

መዝሙር 73 ፥ 28
28 ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል፤ መታመኛዬም እግዚአብሔር ነው በጽዮን ልጅ በሮች ምስጋናህን ሁሉ እናገር ዘንድ።

!

  ርዕስ;- አደራ ተረካብ ትውልድ  #በፓስተር ባሳ በካሎ2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2፤1 እንግዲህ፥ ልጄ ሆይ፥ አንተ በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው ጸጋ በርታ።2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2፤1-3 እንግዲህ፥ ልጄ...
14/10/2025


ርዕስ;- አደራ ተረካብ ትውልድ
#በፓስተር ባሳ በካሎ

2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2፤1
እንግዲህ፥ ልጄ ሆይ፥ አንተ በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው ጸጋ በርታ።
2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2፤1-3 እንግዲህ፥ ልጄ ሆይ፥ አንተ በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው ጸጋ በርታ። ብዙ ሰዎች የመሰከሩለትን ከእኔም የሰማኸውን ሌሎችን ደግሞ ሊያስተምሩ ለሚችሉ ለታመኑ ሰዎች አደራ ስጥ። እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ ወታደር ሆነህ፥ አብረኸኝ መከራ ተቀበል።

፨አደራ ተረካብ ትውልድ ሀላፍነቱ ምንድነው?
፡በእግዚአብሔር ላይ ባለን እምነት መጽናት
፡ቃሉን በትክክል መስበክ እና በቃሉ እውነት መኖር። 2፡15
፡መከራን በመንፈስ ቅዱስ መቋቋም
፡ንፁ እና ታማኝ በመሆን ያስፈልጋል። 2ጤማ 2 ፡22
፡ብትጋት ማገልገል ይጠበቅበታል



" በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፡— እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።" የሐንስ ወንጌል 1:29


መሪ ጥቅስ= የሐንስ ወንጌል 1:29

" በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፡— እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።"

በጥቅም 02/2018 ዓ.ም ዕለተ ዕሁድ
የከሰዓት መርሀግብር
በታርጫ ከተማ ሙሉውንጌል ቤተክርሰተያን

°ጥቅምት 02/2017 በዳውሮ ዞን የታርጫ ሙሉወንገል አጥቢያ ቤተክርስቲያን የዕለተ ዕሁድ ፕሮግራም ።ርዕሰ :- የጥሞና ጊዜ መውሰድበወንድም ፦ መስፍን ማመጫ የጥሞና ጊዜው ማለት አንድ አማኝ...
12/10/2025

°ጥቅምት 02/2017 በዳውሮ ዞን የታርጫ ሙሉወንገል አጥቢያ ቤተክርስቲያን የዕለተ ዕሁድ ፕሮግራም ።

ርዕሰ :- የጥሞና ጊዜ መውሰድ
በወንድም ፦ መስፍን ማመጫ

የጥሞና ጊዜው ማለት አንድ አማኝ ለብቻው በእግዚአብሔር ፍት አጭር/ረዥም ጊዜ ቃሉን በማንበብ ፣ በፆምና በፀሎት የሚናሳልፈው ጊዜ ማለት ነው።
መነሻ የመጽሐፍ ጥቅስ ኢያሱ 7፥2_26
2ሳሙኤል 21፥1_14

ለአንድ አማኝ የጥሞና ጊዜ ለምን ያስፈልጋል?
1,የተበላሸውን የመንፈሳዊ ህይወታቸውን ከእግዚአብሔር ጋር እንደገና ለማስተካከል እንዲውም ምህረት ለመቀበል።
ኢያሱ 7፥6_9
2,የእግዚአብሔርን መጣ /መቅሰፍትን ከእኛ ፣ከቤተሰብ ፣ከሀገር እና ከቤተክርስቲያን እንድነሳ
3, የእግዚአብሔርን ህልውና /አብሮነት ወደ ራሳችን ወደ በክርስቲያናችን እንድመለስ
4,ፅሞና የእግዚአብሔርን ሀሳብ በህይወታችን ምን እንደሆነ የምናውቅበትና እግዚአብሔር በህይወታችን እንድሰራ የምንፈቅድበት ቦታ ነው።
5,በዘላቂነት ፣ በወጥነት ፣ የእግዚአብሔርን ቤት ለማገልገል የፅሞና ህይወት ለአማኝ እጅግ አስፈላጊ ነው። መሳፍንት 16፥1

#የታርጫ ሙሉወንገል አጥቢያ ቤተክርስቲያን


" በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፡— እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።"

በጥቅም 02/2018 ዓ.ም ዕለተ ዕሁድ
ጧት 2:30-6:30
ከሰዓት 8:30-12:00
#የታርጫ ሙሉወንገል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ።

🔴 የቤተክርስቲያንቱ ሳምንታዊ ፕሮግራሞች ፦

🔹እሁድ = 2:00 ስዓት ጀምሮ መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራም አለን።
🔹ማክሰኞ = ምሽት ከ12:00 እስከ 2:00 ስዓት ቤትለቤት ህብረት የአምልኮ ጊዜ ፕሮግራሞች ፦
🔺ሰላም ሰፈር በአቶ ሀይሉ ገሮ ቤት ።
🔺በአረንጓዴ መንደር አዳጊ ቤተክርስቲያን እና
🔺ቤተመንግስት ሰፈር በአቶ ታይበላ ሻንቆ ቤት የሚደረጉ ቤትለቤት ህብረት የአምልኮ ፕሮግራሞች ናቸው ።
🔹ረቡዕ = ምሽት ከ12:00 እስከ 2:00 የትምህርትና የፀሎት ጊዜ በቤተክሪቲያናችን አለን ።
🔹አርብ = ከ11:30 እስከ 2:00 ደረስ የወጣቶች ፕሮግራም በቤተክሪቲያናችን ዘውትር በየሳምንቱ የሚኖረን ይሆናል ።

“ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።”
— ዕብራውያን 13፥8

Like,follows,Share በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎችም ያጋሩ።

. Full Gospel Believers Local Church.

🔴 Weekly programs of the church :_

🔹Sunday = We have a regular worship program starting at 2:00.
🔹Tuesday = evening from 12:00 to 2:00
🔴Neighborhood programs :-

🔺Selam sefer
🔺 Arenguwade Adagi Church
🔺 Betemengist akebabi

🔹Wednesday = evening from 12:00 to 2:00 we have study Word of God and prayer time.
🔹Friday = We have a youth program from 11:30 to 2:00.

"Jesus Christ is the same yesterday, today, and forever." -
Hebrews 13:8

°ጥቅምት 02/2017 በዳውሮ ዞን የታርጫ ሙሉወንገል አጥቢያ ቤተክርስቲያን የዕለተ ዕሁድ ፕሮግራም ።ርዕሰ :- የጥሞና ጊዜ መውሰድ በወንድም ፦መስፍን ማመጫ የጥሞና ጊዜው ማለት አንድ አማኝ...
12/10/2025

°ጥቅምት 02/2017 በዳውሮ ዞን የታርጫ ሙሉወንገል አጥቢያ ቤተክርስቲያን የዕለተ ዕሁድ ፕሮግራም ።

ርዕሰ :- የጥሞና ጊዜ መውሰድ በወንድም ፦መስፍን ማመጫ

የጥሞና ጊዜው ማለት አንድ አማኝ ለብቻው በእግዚአብሔር ፍት አጭር/ረዥም ጊዜ ቃሉን በማንበብ ፣ በፆምና በፀሎት የሚናሳልፈው ጊዜ ማለት ነው።
መነሻ የመጽሐፍ ጥቅስ ኢያሱ 7፥2_26
2ሳሙኤል 21፥1_14

ለአንድ አማኝ የጥሞና ጊዜ ለምን ያስፈልጋል?
1,የተበላሸውን የመንፈሳዊ ህይወታቸውን ከእግዚአብሔር ጋር እንደገና ለማስተካከል እንዲውም ምህረት ለመቀበል።
ኢያሱ 7፥6_9
2,የእግዚአብሔርን መጣ /መቅሰፍትን ከእኛ ፣ከቤተሰብ ፣ከሀገር እና ከቤተክርስቲያን እንድነሳ
3, የእግዚአብሔርን ህልውና /አብሮነት ወደ ራሳችን ወደ በክርስቲያናችን እንድመለስ
4,ፅሞና የእግዚአብሔርን ሀሳብ በህይወታችን ምን እንደሆነ የምናውቅበትና እግዚአብሔር በህይወታችን እንድሰራ የምንፈቅድበት ቦታ ነው።
5,በዘላቂነት ፣ በወጥነት ፣ የእግዚአብሔርን ቤት ለማገልገል የፅሞና ህይወት ለአማኝ እጅግ አስፈላጊ ነው። መሳፍንት 16፥1

#የታርጫ ሙሉወንገል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ።


#ከሰዓትም የመዝሙር ድግሱ የሚቀጥል ይሆናል

ዓ.ም

" በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፡— እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።" የሐንስ ወንጌል 1:29

#የታርጫ ሙሉወንገል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ።

🔴 የቤተክርስቲያንቱ ሳምንታዊ ፕሮግራሞች ፦

🔹እሁድ = 2:00 ስዓት ጀምሮ መደበኛ የአምልኮ ፕሮግራም አለን።
🔹ማክሰኞ = ምሽት ከ12:00 እስከ 2:00 ስዓት ቤትለቤት ህብረት የአምልኮ ጊዜ ፕሮግራሞች ፦
🔺ሰላም ሰፈር በአቶ ሀይሉ ገሮ ቤት ።
🔺በአረንጓዴ መንደር አዳጊ ቤተክርስቲያን እና
🔺ቤተመንግስት ሰፈር በአቶ ታይበላ ሻንቆ ቤት የሚደረጉ ቤትለቤት ህብረት የአምልኮ ፕሮግራሞች ናቸው ።
🔹ረቡዕ = ምሽት ከ12:00 እስከ 2:00 የትምህርትና የፀሎት ጊዜ በቤተክሪቲያናችን አለን ።
🔹አርብ = ከ11:30 እስከ 2:00 ደረስ የወጣቶች ፕሮግራም በቤተክሪቲያናችን ዘውትር በየሳምንቱ የሚኖረን ይሆናል ።

“ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።”
— ዕብራውያን 13፥8

Like,follows,Share በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎችም ያጋሩ።

. Full Gospel Believers Local Church.

🔴 Weekly programs of the church :_

🔹Sunday = We have a regular worship program starting at 2:00.
🔹Tuesday = evening from 12:00 to 2:00
🔴Neighborhood programs :-

🔺Selam sefer
🔺 Arenguwade Adagi Church
🔺 Betemengist akebabi

🔹Wednesday = evening from 12:00 to 2:00 we have study Word of God and prayer time.
🔹Friday = We have a youth program from 11:30 to 2:00.

"Jesus Christ is the same yesterday, today, and forever." -
Hebrews 13:8

Address

Tarch'a S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ታርጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን Tarcha Full Gospel Local Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ታርጫ ሙሉወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን Tarcha Full Gospel Local Church:

Share