Generation for the Lord's Day Reformational Church

Generation for the Lord's  Day Reformational Church **ራዕይ**
ትውልድን ለክርስቶስ ቀን /ለጌታ ኢየሱስ ዳግመኛ መም?

የጌታ እንግዶችን በመጋበዝ ይምጡ! በእውነት አስደናቂ  ጊዜ  ይሆናል!!!!!
06/06/2022

የጌታ እንግዶችን በመጋበዝ ይምጡ! በእውነት አስደናቂ ጊዜ ይሆናል!!!!!

ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።      የሐዋ፡2፦47 10ኛ ዙር ሥርዓተ ጥምቀት 35 ሰዎች ወደ ቤተክርስቲያን ተጨምረዋል።የረዳን ጌታ ይባረክ!!!
16/05/2022

ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር። የሐዋ፡2፦47 10ኛ ዙር ሥርዓተ ጥምቀት 35 ሰዎች ወደ ቤተክርስቲያን ተጨምረዋል።የረዳን ጌታ ይባረክ!!!

29/01/2022

በዚህ ኮንፍራንስ ላይ በመገኘት ጌታን አብረን እናክብር!!

የ8ኛው ዙር ተጠማቂዎች እግዚአብሔር 40 የሚያህሉ ሰዎች እንድናጠምቅ አደረገን  ክብር ሁሉ ለጌታ ይሁን!!
13/06/2021

የ8ኛው ዙር ተጠማቂዎች እግዚአብሔር 40 የሚያህሉ ሰዎች እንድናጠምቅ አደረገን ክብር ሁሉ ለጌታ ይሁን!!

እግዚአብሔር ረድቶን ከወንድማችን ጳውሎስ ግርማ ለቤተክርስቲያን መስሪያ ቦታ በመንግስት ህጋዊነቱ ተረጋግጦ በቤተክርስቲያኒቱ ስም ተረክበናል ።እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ።መዝሙረ ዳ...
25/05/2021

እግዚአብሔር ረድቶን ከወንድማችን ጳውሎስ ግርማ ለቤተክርስቲያን መስሪያ ቦታ በመንግስት ህጋዊነቱ ተረጋግጦ በቤተክርስቲያኒቱ ስም ተረክበናል ።እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ።መዝሙረ ዳዊት 126:2-3
[2]በዚያን ጊዜ አፋችን ደስታን፥ አንደበታችንም ሐሴትን ሞላ፤ በዚያን ጊዜ በአሕዛብ ዘንድ። እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገላቸው ተባለ።
[3]እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።ወንድማችን ፖልን ባርኩልን? ግንቦት 17/2013 ዓ.ም

22/05/2021

የማርቆስ ወንጌል 10:46-52
[46]ወደ ኢያሪኮም መጡ። ከደቀ መዛሙርቱና ከብዙ ሕዝብ ጋር ከኢያሪኮ ሲወጣ የጤሜዎስ ልጅ ዕውሩ በርጤሜዎስ እየለመነ በመንገድ ዳር ተቀምጦ ነበር።
[47]የናዝሬቱ ኢየሱስም እንደ ሆነ በሰማ ጊዜ። የዳዊት ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ማረኝ እያለ ይጮኽ ጀመር።
[48]ብዙዎችም ዝም እንዲል ገሠጹት፤ እርሱ ግን። የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረኝ እያለ አብዝቶ ጮኸ።
[49]ኢየሱስም ቆመና። ጥሩት አለ። ዕውሩንም። አይዞህ፥ ተነሣ፥ ይጠራሃል ብለው ጠሩት።
[50]እርሱም እየዘለለ ተነሣና ልብሱን ጥሎ ወደ ኢየሱስ መጣ።
[51]ኢየሱስም መልሶ። ምን ላደርግልህ ትወዳለህ? አለው። ዕውሩም። መምህር ሆይ፥ አይ ዘንድ አለው።
[52]ኢየሱስም። ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው። ወዲያውም አየ በመንገድም ተከተለው።የበርጤሚዎስ ሁለት ችግሮች 1/ኛ አካለ ጎደሎነቱ (ዓይነስውርነበር)ከዚህ የተነሳ በሰው እርዳታ የሚኖር ሰው ነበር ራሱን የማይችል ሸክም ነበር 2ኛ/መጠቀሚያ ነበር ይህ ማለት የሚረዱት ቤተሰቦቹ ይሁኑ ወይም ሌሎች ሰዎች በሱ አካለጎዶሎነት(ችግር) ይጠቀሙ ነበር። ለምኖ ካመጣው ገንዘብ ይካፈሉ ነበር ምናልባትም አብላጫውን ይወሰዱ ነበር ። አንድ መልዕክት አለኝ ዛሬ በዬትኛውም መንገድ በእናንተ ለሚጠቀሙ ሁሉ ኢየሱስ ከተያዛችሁበት ችግር መከራ ውስንነት አለመቻል ወዘተ ነፃ አውጥቶ መሉ ሰው ያደርጋችኋል ። ከዚህ በኋላ በእናንተ ድህነት ችግር በእርዳታ ስም ቢዝነስ አይሠራም። የሐዋርያት ሥራ 16:16,19
[16]ወደ ጸሎት ስፍራም ስንሄድ፥ የምዋርተኝነት መንፈስ የነበረባት ለጌቶችዋም እየጠነቈለች ብዙ ትርፍ ታመጣ የነበረች አንዲት ገረድ አገኘችን።
[19]ጌቶችዋም የትርፋቸው ተስፋ እንደ ወጣ ባዩ ጊዜ ጳውሎስንና ሲላስን ይዘው ወደ ገበያ በሹማምት ፊት ጐተቱአቸው፤ ከላይ ያየነው በሰዎች የተፈጥሮ ችግር ሊጠቀሙ ስለሚችሉ ሰዎች ነው ያየነው በዘመናችን በስፋት እያየን ስላለ ይህ ምንም ምስክር የሚያሻው ጉዳይ አይደለም። እርግጥ ነው ህይወታቸውን ኑሮአቸውን መስዋዕት ያደረጉም አሉ። በሐዋ 16 16 እና 19 ላይ ያለው ደግሞ በመንፈስ አስሮ መጠቀሚያ ስለማድረግ ነው። በተለይ ይህ በአገራችን የተለመደ ነው በተለያየ ድግምት አስሮ በሰዎች መነገድ ማትረፍ መበልጸግ የብዙዎች የዕብደት ምክንያት ከጥንቆላ ጋር የተያያዘ ነው።ሰው ጨካኝ ነው አይደለም በሩቅ ሰው በቅርብ ቤተሰቡ ሳይቀር ይህን ትብታብ በማድረግ አንዱን አስሮ አድህይቶ ሌላው ሲበለጽግ ይታያል። አሁን ቅዱሳን በዚህ ነገር ነቅተን ተግተን እንፀልይ በቃ እንበል የታሰሩ ይፈቱ ነፃ ይውጡ። በአንድም በሌላም በስውርም በግልፅ መንፈሳዊ ተፅዕኖ ውስጥ ያሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነፃ ውጡ!!!! እስራታችሁ ይፈታ ።የተብታቢዎች የትርፋቸው ተሰፋ ይመታ!!! ፀልዩ የማንም መጠቀሚያ ላለመሆን ወደ ጌታ አብዝታችሁ ጩሁ! ምናልባት ጥቅማቸውን አንዳያጡ ዝም ሊያሰኙዋችሁ ይሞክሩ ይሆኑ ይሆናል፤ እናንተ ግን ኖ! አይሆንም አንደበርጤሚዎስ እምቢ በሉ። ዛሬ የእናንተ ቀን ነው! ነፃ ሰው ሙሉ ሰው የምትሆኑበት፤ ታውቃላችሁ፦ ከመናፍስት አሠራር ነው ነፃ የወጣሁት( ምስክርነቴን በመዳን ቀን ቲቪ አሌክሳንደር ለታ ብላችሁ በዩ ቲዩብ ብትገቡ ማየት ትችላላችሁ) ። አና ነፃ ከወጣሁ በኋላ ጠላት በግልፅም በስውርም ተፅዕኖ ያደርግብኝ ነበር። ።የመናፍስቱ ዓለም አገልጋይ እንድሆን ከቤተሰቦቼ አካባቢ ተሰርቶብኝ ነበር፦ ሆኖም የጌታ ከሆንሁ አገልጋይም ከሆንሁ ከሃያ ዓመት በኋላ ነው ከብርቱ ፀሎት የተነሳ ይህ ሰውር እጅ የተሰበረው። ዛሬ ለኔ የጠቀመኝን አንድ ምክር ልምከራችሁ በኑሮአቸሁ በቢዝነሳችሁ በአገልግሎታችሁ በባህሪያችሁ ወዘተ ነፃነት የማይሰማችሁ አሜን አትበሉ! የአርባ ቀን ዕድሌ ነው አትበሉ! እምቢ በሉ! ወደ እግዚአብሔር ጩሁ!!! እግዚአብሔር ሊያድናችሁ ሊታደጋችሁ ይወርዳል። ለማንም መጠቀሚያ አትሁኑ ጉልበታችሁንም በከንቱ አታስበሉ፥ እባካችሁ አብዝታችሁ ጩሁና ነፃ ውጡ ። በሌላ መልዕክት እስክንገናኝ ደህና ሁኑ። ከጠቀማችሁ እናንተ ጋር ብቻ አታስቀሩ ሼር አድርጉ።

03/05/2021

ከመስቀል ወርደህ ራስህን አድን አሉ። እርሱ ግን እነሱን ሊያድን እንደተሰቀለ አላወቁም!!

28/04/2021
ዛሬ እጅግ ደስ የሚል የምልጃ ቀን ስለአገራችን የንስሐና የምልጃ የጾም ፀሎት አውጀን የ14ቀን የምልጃ ፀሎታችንን ሜዳ ላይ ወጥተን ይህን በመሰለ መልኩ ተፀልይዋል። በተለይ አገሪቱ በሶስት ማ...
25/04/2021

ዛሬ እጅግ ደስ የሚል የምልጃ ቀን ስለአገራችን የንስሐና የምልጃ የጾም ፀሎት አውጀን የ14ቀን የምልጃ ፀሎታችንን ሜዳ ላይ ወጥተን ይህን በመሰለ መልኩ ተፀልይዋል። በተለይ አገሪቱ በሶስት ማዕዘን ቅርፅ የተወጠረ ገመድ በብሎን የታሰረ ብሎኑ በምዕራብ አቅጣጫ በመፍቻ አንድ እጅ ሲያጠብቅ የተወጠረው የናይለን ገመድ ሲበጠስ አየሁ። ከዚያ አንድ እጅ የተቃጠለ አምፖል ወደ ማቀፊያ ውስጥ ለማስገባት እጁን ሲዘረጋ አየሁ ።እግዚአብሔር ይህ እንዳይሆን የምልጃ መንፈስ አፈሰሰልን ከፀሎታችን(ከጩኸታችን)በኋላ እንዲህ አየሁ አንዲት ትልቅ ሴት እንጦጦ እንጨት እንደሚሸከሙት ከባድ ሸክም ተሸክማ ጎብጣ ሆኖም ሽክሟን ወደ ኋላ ስትጥል ሸክሟ ሲራገፍ አየሁ። በአንድ ወ/ም ፕሬዝዳንቷ በእሳት ከወገቧ በታች ስትቃጠል አድኑኝ ስትል እንዳየ ይህም አገር የአድኑኝ ጥሪ ለልጆቿ እያሰማች አንደሆነ ተረዳን ህልሙ ረጅም ነው ጭብጡን ነው የነገርኋችሁ ስለኢትዮጵያ ፀሎታችንን እንቀጥል። እግዚአበሔር ጣልቃ ይገባል ለምስኪኑ ተስፋ አለው ክፋት ግን አፏን ትዘጋለች ። መዝሙረ ዳዊት 34:15-19
[15]የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደ ጻድቃን ጆሮቹም ወደ ጩኸታቸው ናቸውና።
[16]መታሰቢያቸውን ከምድር ያጠፋ ዘንድ የእግዚአብሔር ፊት ክፉን በሚያደርጉ ላይ ነው።
[17]ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው።
[18]እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፥ መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።
[19]የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል። መዝሙረ ዳዊት 12:5
[5]ስለ ድሆች መከራ፥ ስለ ችግረኞች ጩኸት እግዚአብሔር። አሁን እነሣለሁ ይላል፤ መድኃኒትን አደርጋለሁ፥ በላዩም እገልጣለሁ። መዝሙረ ዳዊት 20:7-8
[7]እነዚያ በሰረገላ እነዚያም በፈረስ ይታመናሉ፤ እኛ ግን በአምላካችን በእግዚአብሔር ስም ከፍ ከፍ እንላለን።
[8]እነርሱ ተሰነካክለው ወደቁ፤ እኛ ግን ተነሣን፥ ጸንተንም ቆምን።

Address

Sululta

Telephone

+251911371610

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Generation for the Lord's Day Reformational Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share