የጉኑኖ ከተማ እናት አጥቢያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የወጣቶች አገልግሎት ዘርፍ

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • የጉኑኖ ከተማ እናት አጥቢያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የወጣቶች አገልግሎት ዘርፍ

የጉኑኖ ከተማ እናት አጥቢያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የወጣቶች አገልግሎት ዘርፍ ወልድ(ኢየሱስ) ያለው ሕይወት አለው።

📖   📖🔔 አዲስ ኪዳንና ትምህርቱ — የ4 ሳምንት ተከታታይ ትምህርትለ9 ሳምንታት በ“መጽሐፍ ቅዱስና ትምህርቱ” ዋና ርዕስ ሥር፣ክፍል 1 - መግቢያ፣ክፍል 2 - ብሉይ ኪዳንና ትምህርቱ፣እንዲ...
18/08/2026

📖 📖

🔔 አዲስ ኪዳንና ትምህርቱ — የ4 ሳምንት ተከታታይ ትምህርት

ለ9 ሳምንታት በ“መጽሐፍ ቅዱስና ትምህርቱ” ዋና ርዕስ ሥር፣
ክፍል 1 - መግቢያ፣
ክፍል 2 - ብሉይ ኪዳንና ትምህርቱ፣
እንዲሁም Sola Scriptura ላይ ያደረግነውን ጥናት አጠናቀን፣ አሁን ደግሞ ወደ ቀጣዩ ክፍል እንሻገራለን።

📖

"ነገር ግን እግዚአብሔር በሕዝቡ ላይ ጕድለት በማግኘቱ እንዲህ ይላቸዋል፤
“ከእስራኤል ቤት ጋር፣
ከይሁዳም ቤት ጋር፣
አዲስ ኪዳን የምገባበት፣
ጊዜ ይመጣል፤ ይላል ጌታ።”
ዕብራውያን 8፥8

ከፊታችን ሐሙስ፣ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ሐሙሳት የአዲስ ኪዳንን ትምህርት በጥልቀት እንማራለን።
🙏 ጉኑኖና አካባቢው የምትገኙ ቅዱሳን ሁላችሁ፣
ይህ ታላቅ የቃሉ በረከት እንዳያመልጣችሁ በጌታ ፍቅር እንጋብዛችኋለን።

📌 መጽሐፍ ቅዱሳችሁንና ማስታወሻችሁን አትርሱ!
መጽሐፍ ቅዱስን በእጃችን፣
ቃሉን በልባችን! ❤️📖
✨ ኑ፤ አብረን እንማር፣ እንወቅ፣ እንኑር!

🎉 እንኳን ለ11ኛው ዙር ሳምንታዊ የልጆች ፌስቲቫል በሰላም አደረሳችሁ! 🎊"እናንተ ግን ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃኑ የጠራችሁን የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ እንድታውጁ የተመረጠ ትውልድ፣ የን...
16/08/2026

🎉 እንኳን ለ11ኛው ዙር ሳምንታዊ የልጆች ፌስቲቫል በሰላም አደረሳችሁ! 🎊

"እናንተ ግን ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃኑ የጠራችሁን የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ እንድታውጁ የተመረጠ ትውልድ፣ የንጉሥ ካህናት፣ ቅዱስ ሕዝብ፣ እግዚአብሔር ለራሱ የለያችሁ ሕዝብ ናችሁ።"
1 ጴጥሮስ 2፥9

🌟 🌟

በጉኑኖ ከተማ እናት አጥቢያ ቃ/ህ/ቤ/ያን በየዓመቱ የሚካሄደው የልጆች ፌስቲቫል ለ11ኛ ዙር በልዩ መልኩ ተዘጋጅቶ በይፋ ተጀምሯል! 🎉

👑 በዚህ ዓመት #“የመንግሥቱ_ካህናት” በሚል መሪ ርዕስ፣ ልጆቻችን ማንነታቸውን እንዲያውቁ፣ በእግዚአብሔር ቃል እንዲጸኑ፣ ክርስቶስን እንዲወዱና ለመንግሥቱም ታማኝ እንዲሆኑ የሚያግዙ ትምህርቶች፣ ጸሎት፣ ዝማሬ፣ ጨዋታና የተለያዩ መንፈሳዊ ፕሮግራሞች ይቀርባሉ።

🙏 የዛሬ ልጆች የነገ ቤተክርስቲያን መሪዎች ናቸው!
🔥 እነሱን በቃሉ እናሳድጋቸው!
👑 ለመንግሥቱ እናዘጋጃቸው!




" ይህን በመጀመሪያ እወቁ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈ...
12/08/2026

" ይህን በመጀመሪያ እወቁ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ።"
2ጴጥ1:20-21






ባለፈው ሳምንት የጀመርነውን Sola Scriptura ትምህርት በዚህ ሳምንትም በተጨማሪ ጥልቀት እንቀጥላለን።
📅 ቀን፦ ሐሙስ ነሐሴ 7/12/2018
⏰ ሰዓት፦ 11:00
📍 ቦታ፦ ጉኑኖ_ እናት_ቃለ_ሕይወት

&


👉ሁላችሁም በመገኘት በእግዚአብሔር ቃል ተባረኩ፤ ሌሎችንም በመጋበዝ የበረከቱ ተካፋይ ያድርጓቸው።

   📷Epha Pictures
08/08/2026




📷Epha Pictures

   #2📷Epha Pictures
08/08/2026



#2
📷Epha Pictures

" ይህን በመጀመሪያ እወቁ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈ...
07/08/2026

" ይህን በመጀመሪያ እወቁ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ።"
2ጴጥ1:20-21







ማለት የሕይወታችን መሪና መመሪያ ማለት ነው።
ማለት የ66 መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን ብቻ ማለት ነው።
"መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ (Sola Scriptura) የእምነታችንና የሕይወታችን የመጨረሻ ባለሥልጣን ነው።"
አንዲት ፊደል ወይም ቃል መካድ ማለት መንፈስ ቅዱስን መካድ ማለት ስለሆነ መጽሐፍ ቅዱስ (66) ላይ ሊጨመርበትም ሊቀነስበትም አይችልም።
(ራዕይ 22:18-19)
👉 "... ማንም በዚህ ላይ አንዳች ቢጨምር ማለት " እኔ ከእግዚአብሔር በላይ ስለማውቅ እጨምለሁ ፤ እሱ ረስቶታል" ማለት ነው።
👉 የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ነው።

ትናንት ሐሙስ ማታ በ"Sola Scriptura" ርዕስ የተዘጋጀው የቃልና የመዝሙር ጊዜ በእግዚአብሔር ጸጋ እጅግ የተባረከ ጊዜ ነበር።

ወ/ዊ ሳሙኤል ሳህሌ በእግዚአብሔር ቃል በብርቱ መልእክት አገልግሎናል፤

ዘማሪ ጥበቡ ደግሞ በመዝሙር አገልግሎናል። ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ ብለናል።

እግዚአብሔርም የተዘራብን ቃል በሕይወታችን እንዲያፈራ ያድርገው።
ይህ ትምህርት በሚቀጥለው ሐሙስ ማታም ይቀጥላል።

ሁላችሁም በመገኘት በእግዚአብሔር ቃል ተባረኩ፤ ሌሎችንም በመጋበዝ የበረከቱ ተካፋይ ያድርጓቸው።

 #አስታውሱ  የጉኑኖ ከተማ እናት አጥቢያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የወጣቶች አገልግሎት ዘርፍ
06/08/2026

#አስታውሱ


የጉኑኖ ከተማ እናት አጥቢያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የወጣቶች አገልግሎት ዘርፍ

"...ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ።"  ዮሐ 15:16   እና  ! በጉኑኖ ከተማ እናት ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ባለፈው እሑድ   አዲስ የቤተክርስቲያን መሪዎች ምርጫ በ...
05/08/2026

"...ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ።" ዮሐ 15:16

እና !

በጉኑኖ ከተማ እናት ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ባለፈው እሑድ አዲስ የቤተክርስቲያን መሪዎች ምርጫ በእግዚአብሔር ቃልና በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የምርጫ ሥርዓት መሠረት ተካሂዷል።

ላለፉት ሦስትና ስድስት ዓመታትን በትጋት፣ በታማኝነትና በፍቅር እግዚአብሔርንና ቤተክርስቲያኑን ያገለገሉትን መሪዎች በአክብሮት ሸኝተን፣ ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት አገልግሎቱን የሚመሩትን አዲስ መሪዎች በደስታ ተቀብለናል።

ይህን የአገልግሎት ቅብብሎሽ ለማስታወስና የወደፊት ተስፋን ለመግለጽ፣ ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

የተተከለው ችግኝ ዛሬን ብቻ ሳይሆን የነገን ትውልድ የሚጠቅም አረንጓዴ ቅርስ ነው። እንዲሁም በቤተክርስቲያናችን የተጀመረው አዲስ የአገልግሎት ዘመን በፍሬ፣ በበረከትና በመንፈሳዊ እድገት እንዲሞላ የምንጸልይበት ምልክት ነው።

የቀድሞ መሪዎቻችንን ስለ ታማኝ አገልግሎታቸው ከልብ እያመሰገንን ለአዲስ መሪዎቻችንም እግዚአብሔር ጥበብን፣ ጸጋን፣ ጥንካሬንና የታማኝነት መንፈስን እንዲሰጣቸው እንጸልያለን።

"እግዚአብሔር በእናንተ የጀመረውን መልካም ሥራ ይፈጽመው፤ የተተከለው ችግኝ እንደሚያድግ ሁሉ፣ የቤተክርስቲያናችን አገልግሎትም ከክብር ወደ ክብር ይደግ!"

!

" የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።...
03/08/2026

" የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።"
2ጢሞ 3:16-17

📖 #"SOLA_SCRIPTURA"

#"መጽሐፍ_ቅዱስ_ብቻ"

የተወደዳችሁ ባላችሁበት ቦታ ሁሉ ይኼን መልዕክት የምትመለከቱት በሙሉ ሰላምና ጸጋ ይብዛላችሁ፤

በ"Sola Scriptura (መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ)" በሚል ርዕስ የትምህርትና የአምልኮ ፕሮግራም ጀምሮ ተዘጋጅቷል ።
በፍቅር እንጋብዛለን።
#አገልጋዮች

🎤 ወ/ዊ
🎙ዘማሪ ጥበቡ ዳንኤል

ኦሪት ዘዳግም 17:19 አምላኩን እግዚአብሔርን መፍራት ይማር ዘንድ፥ የዚህን ሕግ ቃል ሁሉ ይህችንም ሥርዓት ጠብቆ ያደርግ ዘንድ፥ ልቡ በወንድሞቹ ላይ እንዳይኰራ ከትእዛዙም ቀኝና ግራ እንዳ...
30/07/2026

ኦሪት ዘዳግም 17:19

አምላኩን እግዚአብሔርን መፍራት ይማር ዘንድ፥ የዚህን ሕግ ቃል ሁሉ ይህችንም ሥርዓት ጠብቆ ያደርግ ዘንድ፥ ልቡ በወንድሞቹ ላይ እንዳይኰራ ከትእዛዙም ቀኝና ግራ እንዳይል፥ እርሱም ልጆቹም በእስራኤል ልጆች መካከል ረጅም ዘመን ይነግሡ ዘንድ መጽሐፉ ከእርሱ ጋር ይኑር፥ ዕድሜውንም ሁሉ ያንብበው።




እና

Address

S**o-tericha
S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጉኑኖ ከተማ እናት አጥቢያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የወጣቶች አገልግሎት ዘርፍ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share