SCS - Soddo Catholic Secretariat

SCS - Soddo Catholic Secretariat Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from SCS - Soddo Catholic Secretariat, Catholic Church, Ethiopia, Wolaita Soddo, Sodo.

የሉርድ ማርያም ዓመታዊ ክብረ-በዓል በድምቀት ተከበረ። በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን በሶዶ አገረ ስብከት በዱቦ ሉርድ ማርያም ቁምስና የሉርድ ማርያም ዓመታዊ ክብረ-በዓል የካቲት 08/...
15/02/2026

የሉርድ ማርያም ዓመታዊ ክብረ-በዓል በድምቀት ተከበረ።

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን በሶዶ አገረ ስብከት በዱቦ ሉርድ ማርያም ቁምስና የሉርድ ማርያም ዓመታዊ ክብረ-በዓል የካቲት 08/2018 ዓ.ም. በድምቀት ተከበረ።
በዕለቱም የሶዶ አገረ ስብከት ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ደጀኔ የክብረ በዓሉን መሥዋዕተ ቅዳሴ መርተዋል።

በበዓሉ የሀዋሳ አገረ ስብከት ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መርሀክርስቶስ በመሥዋዕተ ቅዳሴው የተገኙ ሲሆን ካህናት ፣ ገዳማውያን ፣ መነኮሳት ፣ ወጣት መዘምራን እና ከተለያዩ አገረስበከት የመጡ ምዕምናን ተገኝተዋል።

ብጹዕ አቡነ ደጀኔ “የሉርድ ማርያም በዓል የእግዚአብሔር ስም ከፍ የሚልበት እና በእርሷ አማካኝነት ቸርነቱ የሚታይበት ታላቅ በዓል ነው። ይህ ስፍራም ከእግዚአብሔር ጋር በጸሎት የምንገናኝበት ስፍራ ነው። እናታችን ሉርድ ማርያም ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉንም አዲስ እንደሚያደርግ በመተማመን በመከራም ውስጥ ሆነን በጽናት እንድናገለግለው ትጋብዘናለች። የእርሷ ክብረ በዓል ያለፈውን ጊዜ ብቻ አስታውሰን የምንተወው ሳይሆን ሁሌም በልባችን የምናሰላስለው ጥሪ ነው። የእግዚአብሔር ጥሪ በሰዎች መስፈርት የሚለካ ሳይሆን በትህትና እና በመታዘዝ የሚገኝ ነው።” በማለት የዕለቱን ቃለ እግዚአብሔር አሰምተዋል።

በበዓሉም በተለያዩ ቋንቋዎች ስለቤተክርስትያናችን፣ ስለ ሰላም፣ ስለ ሕሙማን፣ ስለ ወጣቶች፣ እና ስለ ሀገር መሪዎች እንዲሁም በተለያዩ ሐሳቦች ላይ የምልጃ ጸሎት ተደርጓል።

የሉርድ ማርያም ክብረ-በዓል ከዋዜማው ጀምሮ በአስተምህሮ ፣ በጸሎት ፣ በዑደት ፣ በዝማሬ የተከበረ ሲሆን በዓሉን ለየት የሚያደርገው የእመቤታችን የሉርድ ማርያም ዋሻ ለመንፈሳዊ ነጋድያን ይሆን ዘንድ በብጹዕ አቡነ ደጀኔ መመረቁ ነው።

ክብረ-በዓሉ በጸሎት ፣ በዝማሬ ፣ በዑደት እና በቡራኬ ተጠናቋል።

ምንጭ : ሰላም ካቶሊክ ቲቪ Pax Catholic TV

የእመቤታችን የሉርድ ማርያም ዓመታዊ ክብረ-በዓል የዋዜማ ፕሮግራም።
15/02/2026

የእመቤታችን የሉርድ ማርያም ዓመታዊ ክብረ-በዓል የዋዜማ ፕሮግራም።

14/02/2026
የአባ ዋዱ ክንፈ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ። ወላይታ ሶዶ ፣ ጥር 23/ 2018“የጌታ ፍቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን ። “ የሐዋ. ሥራ 21:14
31/01/2026

የአባ ዋዱ ክንፈ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ።

ወላይታ ሶዶ ፣ ጥር 23/ 2018

“የጌታ ፍቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን ። “
የሐዋ. ሥራ 21:14

30/01/2026
የሐዘን መግለጫበሶዶ ሀገረስብከት የኦሞራቴ መጥምቁ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ቆሞሰ የነበሩት ክቡር አባ ዋዱ  ዛሬ ጥር 21/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል። እኛም የተሰማንን ጥልቅ ሐ...
29/01/2026

የሐዘን መግለጫ

በሶዶ ሀገረስብከት የኦሞራቴ መጥምቁ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ቆሞሰ የነበሩት ክቡር አባ ዋዱ ዛሬ ጥር 21/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል።
እኛም የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለሀገረስብከታችን ካህናቶች፣ ምዕመናን እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

12/01/2026

ሰላም ካቶሊክ ቲቪ Pax Catholic TV መረጃዎችን በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉን✅ YouTube – https://youtube.com/pax_ctv✅ ...

06/01/2026

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የሶዶ ሀገረ-ስብከት ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ደጀኔ ሂዶቶ የ2018 ዓ.ም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል በማስመልከት ለመላው ምዕመናን ያስተላለፉት መልዕክት፡፡

26/12/2025

every drop of water is a story of a mother who no longer has to walk miles and a child who can now focus on school. This isn't just a project; it’s a gift of dignity and health for the people of Melo Koza. Clean water is a human right, and today, we celebrate life! 💧

💧  !በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በሶዶ ሀገረ ስብከት ማህበራዊና ልማት ኮሚሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አማካኝነት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጎፋ ዞን፣ መሎ ኮዛ ወረዳ በባንካ ጋራ ሀስ...
26/12/2025

💧 !

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በሶዶ ሀገረ ስብከት ማህበራዊና ልማት ኮሚሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አማካኝነት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጎፋ ዞን፣ መሎ ኮዛ ወረዳ በባንካ ጋራ ሀስቴ ቀበሌ የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በቀን 16/04/2018 ዓ.ም በድምቀት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

በምርቃቱ ስነ-ስርዓት ላይ፦

ክቡር አባ አለማየሁ ወ/ኢየሱስ (የሶዶ ሀገረ ስብከት ጳጳስ እንደራሴ)

አቶ ሙሉነህ ተስፋዬ (የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር)

ዶ/ር ነፃነት ደምሴ (የልማት ጽ/ቤቱ ዳይሬክተር)

የወረዳው ከፍተኛ ባለስልጣናት እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ተወካዮች

የአካባቢው ህዝብ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የጽ/ቤቱ ሰራተኞች ተገኝተዋል።

የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ስራዎች፡- 🏗 7 አዳዲስ የውሃ ቦኖዎች ግንባታ 🏗 100,000 ሜትር ኩብ ይዘት ያለው አንድ ግዙፍ የውሃ ማጠራቀሚያ ገንዳ (Reservoir) 🏗 14 ኪሎ ሜትር የውሃ ቧንቧ ዝርጋታ
🛠 6 ነባር የውሃ ቦኖዎች እና የ50,000 ሜትር ኩብ የውሃ ማጠራቀሚያ ገንዳ እድሳት

ይህ ፕሮጀክት ከካሪታስ ቼክ እና ከቼክ መንግስት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የተገነባ ሲሆን፣ በአካባቢው ለረጅም ጊዜ የነበረውን የውሃ ችግር በእጅጉ የሚቀርፍ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች በደስታ ገልፀዋል።

#ኢትዮጵያ #ካቶሊካዊትቤተክርስቲያን #የንጹህውሃ #ልማት #መሎኮዛ #ጎፋ

Address

Ethiopia, Wolaita Soddo
S**o

Opening Hours

Monday 08:00 - 18:00
Tuesday 08:00 - 18:00
Wednesday 08:00 - 18:00
Thursday 08:00 - 18:00
Friday 08:00 - 18:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SCS - Soddo Catholic Secretariat posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to SCS - Soddo Catholic Secretariat:

Share