Brightness of Christ

Brightness of Christ It is all about reflecting the true light to the world-that is, Jesus the Christ, the son of God!!

09/10/2020

በብሉይ ኪዳን የተሰጡ የተስፋ ቃሎች ፍጻሜን ያገኙት ነው።

ቀን ሁለት በሶዶ ባፕቲስት ቤተክርስትያን በተዘጋጀው የአምስቱ ብቻዎች [Five solas] ኮንፈራንስጠዋትመዝሙር :- እግዚአብሔር በክርስቶስ ስለዋለንን አመሰግንነውየመጀመሪያ ክፍለ ጊዜ - ሳ...
09/10/2020

ቀን ሁለት በሶዶ ባፕቲስት ቤተክርስትያን በተዘጋጀው የአምስቱ ብቻዎች [Five solas] ኮንፈራንስ

ጠዋት

መዝሙር :- እግዚአብሔር በክርስቶስ ስለዋለንን አመሰግንነው

የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜ - ሳይመን ዶይለ

በእምነት ብቻ [sola fide]

ሮሜ 3:18-4:12

መግቢያ

- በእምነት ብቻ የሚለው አስተምህሮ ተደላድሎ ያለ አይደለም። አሁንም በጥቃት ላይ ነው።

- እምነት ብቻ ማለት ለደኅንነት በክርስቶስ ብቻ ማመንና መደገፍ ነው።

- ኃጢአተኛ የሚጸድቀው በእምነት ብቻ ነው።
መዝ 36:9, 119:96

- ከእምነት ተከትሎ የሚመጣው 'ብቻ' የሚለው ቃል ሌላ ተጨማሪ ነገር እንደሌለ የሚያሳይ ቁልፍ ቃል ነው።

- እምነት በራሱ ጽድቅ ማስገኛ ሥራ አይደለም።

- እምነት ሕግን የመጠበቅ ታማኝነት አይደለም።
ገላ 2:15-15, 2ቆሮ 5:20-21

- ከእምነት ብቻ ጋር ተያይዞ ሳይነሳ የማይቀረው : የክርስቶስ ጽድቅ ለእኛ መቆጠሩ [imputation]
ሮሜ 3:23-26, 2ቆሮ 5:20-21

ሁለተኛ ክፍለጊዜ :- ሳይመን ዶይለ

መዝሙር :- ስለ እግዚአብሔር ቃል አዜምን : ለቃሉ ፍቅራችንን ገለጥን

ትግበራ

- ወንጌሉ ያለ መስፈርት ለሁሉም የቀረበ ነው።
ማቴ 11:28-30, ኢሳ 55:1
- የድነት እርግጠኝነት በእምነት ብቻ የሚሆን ነው።
ዮሐ 3:36, 2ጴጥ 1:3-11
- በአጠቃላይ ሕይወታችን ጥንካሬ የሚሆነው በእምነት ብቻ ነው።
መሳ 16:15-22,ዕባ 2:4, 1ቆሮ 1:30-31

ከሰዓት

መዝሙር :- በእግዚአብሔር ተመርጠን : በክርስቶስ ስለተደረገልን አዜምን

የመጀመሪያ ክፍለጊዜ :- ጌዲዮን አግዘው

በክርስቶስ ብቻ :- ከአዲሱ ኪዳን ተስፋ አንጻር

ዕብ 10:19-25

- በእግዚአብሔር ፊት የምቆምበት መሠረት ምንድር ነው ? ከቆሞኩስ የምፀናው በምንድርነው ?

- በክርስቶስ ብቻ ነው!!!

ኤር 31:31 , 31:14
* እውነተኛ ካህን, ንጉሥ የአዲሱ ኪዳን ተስፋ ነው።

- ይህ የተሟላው በክርስቶስ ብቻ ነው!!

* ዕብ 10:22

- የአዲሱ ኪዳን ተስፋ ፍጻሜ በኃይልና በሥልጣን በክርስቶስ ተፈጽሟል። ስለዚህ ክርስቶስ ብቻ በቂ ነው።

መዝሙር :- እግዚአብሔር ስለገለጠልን ፍቅር አመሰገንን ደስ ተሰኘን

ሁለተኛው ክፍለጊዜ :- ጌዲዮን አግዘው

በክርስቶስ ብቻ :- ከሰው ልጅ የመፈጠር ዓላማ አንጻር
መዝ 8
* ኃጢአት የሰው ልጅን ከሰውነት አጉድሏል
መዝ 106:20
* ክርስቶስ ወደ ቀደመው ማንነት መልሷል። ስለዚህ ክርስቶስ ብቻውን በቂ ነው።

ጌዲና ሳይመን ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ!!

መርሃ ግብሩ ነገም የሚቀጥል ይሆናል።

ቦታ :- ጦና ህንጻ, ሲቲ ሆል

ሰዓት :- 3:00

ሁላችንም በቦታው በመገኘት ይህን አስደናቂ እውነት : ከቤተክርስትያን አበው ጋር በአንድነት እናውጅ! !

29/01/2013 ዓ.ም

ወላይታ ሶዶ

ቀን አንድ በሶዶ ባፕቲስት ቤተክርስትያን በተዘጋጀው የአምስቱ ብቻዎች [Five solas] ኮንፈራንስጠዋትየመጀመሪያ ክፍለ ጊዜ - ሳይመን ዶይልመዝሙር :- እግዚአብሔርን ከጨለማ ስላወጣን አመ...
08/10/2020

ቀን አንድ በሶዶ ባፕቲስት ቤተክርስትያን በተዘጋጀው የአምስቱ ብቻዎች [Five solas] ኮንፈራንስ
ጠዋት
የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜ - ሳይመን ዶይል
መዝሙር :- እግዚአብሔርን ከጨለማ ስላወጣን አመሰገንነው
መግቢያ : መዝ 3:1-8
- የአምስቱን ብቻዎች ታሪካዊ አውድ በመመልከት ጀመርን
የሁለቱን ሺህ አመት ታሪክ በአራት ከፍለን ተመለከትን
- Godfrey ታሪኩን የተመለከበትን አራት ምልከታ በዚህ መልክ አየን
* 100 - 600 A.D - ቤተክርስትያን ተመሠረተች [formed]
* 700 - 1400 A.D - ቤተክርስትያን ወደቀች [deformed]
* 1500 - 1600 - ቤተክርስትያን ታደሰች [Reformed]
* 1600 - 2000 - ቤተክርስትያን ተለወጠች [Transformed]
- የተሐድሶው አበው ቃል በቃል ብቻዎች እያሉ አላስተማሩም። ይህ ማለት ግን እውነታው በእነርሱ አይታወቅም ወይም የለም ማለት አይደለም።
- አምስቱ ብቻዎች ጥቅል ናቸው። ተነጣጥለው መነሳት ቢችሉም እርስ በእርስ የሚደጋገፉ ናቸው።
- መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ [sola scriptura] መሠረታዊ : የሁሉም አስተምህሮዎች መለኪያ ነው።
- ሮማን ካቶሊኮችና የተሐድሶው አባቶች በብቻዎች በአጠቃላይ [ generally] ይስማማሉ : በአስተንትኖቱ ግን ግልጥ ልዩነት አላቸው።
መዝሙር :- ስለ ቤዝኦት : ጽናት : በአንድነት በጋሽ ተስፋዬ ጋቢሶ ዝማሬ አመሰገንን ደስ ተሰኘን
ሁለተኛ ክፍለጊዜ :- ሳይመን ዶይል
ርዕስ :- መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ [ Scripture Alone ]
ኢሳ 8:16-22
- ለምን በመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ መጀመር አስፈለገ?
* የሁሉም ነገር መሠረትና መለኪያ በመሆኑ ነው።
- መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ስንል ምን ማለታችን ነው?
* መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ለእርሱና በእርሱ በተፈጠረው ዓለም ለእውነተኛ መረዳት እና ኑሮ ብቸኛ ተዓማኒ ባልጣን መጽሐፍ ነው እያልን ነው።
- ያለ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን : እርሱ የፈጠራቸውንም ነገሮች መረዳት አንችልም። ያለ መጽሐፍ ቅዱስ ሁሉም ነገር ጨለማና ድፍን ነው።
- መጽሐፍ ቅዱስ ለየትኛውም ሥልጣን የማይገዛ : ሁሉን ከሥልጣኑ ከሥር የሚያንበረክክ ከፍተኛው ባለሥልጣን ነው። ምክንያቱም ልዩ ነውና።
- መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ምን ያካትታል?
1. መጽሐፍ ቅዱስ እስትንፈሰ እግዚአብሔር ነው።
2. መጽሐፍ ቅዱስ ፍጹም ሊሳሳት የማይችል እና ስህተት የሌለበት መጽሐፍ ነው።
3. መጽሐፍ ቅዱስ አይለወጥም።
* አዳዲስ የሚጨመሩበት [update] ነገር የለም።
4. መጽሐፍ ቅዱስ ግልጽ ነው።
5. መጽሐፍ ቅዱስ በቂ ነው።
ትግበራ - Application
- እግዚአብሔርን ለማወቅ እና በእርሱ ለመደሰት መጽሐፍ ቅዱስን መውደድና እርሱን መተንፈስ አለብን።
- በግል ሕይወታችን መጽሐፍ ቅዱስ ገዢ እንዲሆን መጽሐፍ ቅዱስን መውደድና እርሱን መተንፈስ አለብን።
- መጽሐፍ ቅዱስ መላለሙን እና በውስጡ ያለውን የምንረዳበት ንጽረት ዓለማችን እንዲሆን መጽሐፍ ቅዱስን መውደድና እርሱን መተንፈስ አለብን።
- መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ እንዲናገር እንፍቀድ አንጨምርበት።
- መጽሐፍ ቅዱስ መውደድና እርሱን መተንፈስ የእኛን እና የእግዚአብሔርን ሥልጣን እንድንረዳ ያደርገናል።
ከሰዓት
መዝሙር :- እግዚአብሔርን ስለጥበቃው አመሰገንን
ፀጋ ብቻ [ Sola Gratia ] - መጋቢ ጌዲዮን አግዘው
የመጀመሪያው ክፍለጊዜ - ፀጋ ብቻ ከአጠቃላይ ውድቀት አንጻር
ሮሜ 3:21-26
- ፀጋ ብቻ የሚለውን አስተምህሮ በግልጽ የምናገኘው በዚህ ክፍለ ምንባብ ነው።
- በፀጋ ብቻ የሚለውን አስተምህሮ መጽሐፍ ቅዱስ ቀስ በቀስ ያዳበረው ትምህርት ነው።
- በቀደመው ኪዳን የእግዚአብሔር ጽድቅ አሁን በተገለጠው መልኩ አልተገለጠም።
- ታዲያ በየትኛው ኪዳን ተገለጠ?
* ኤር 31:31 - በአዲሱ ኪዳን
- የአዲሱ ኪዳንና የአሮጌው ኪዳን ልዩነት የሕጉ በልብና በጽላት መጻፉ ላይ ነው።
- ሕጉ በልቦና መጻፉ - ዳግም ልደት
- ፀጋ ብቻ ስንል በዳግም ልደት ከሞተ ማንነት ለእግዚአብሔር ጉዳይ ሕያው መሆን ማለታችን ነው።
- የሰው ዘር [ አይሁድ ሆነ አሕዛብ ] በሙላ በአንድነት ለእግዚአብሔር ጉዳይ የሞተ ነው። ለአይሁድ የተሰጠው የቀደመው ኪዳን ከሰዎቹ አለመቻል የተነሳ ከዚህ ሊያድናቸው አልቻለም።
- ስለዚህ የቀደመው [የሙሴ] በአዲሱ ኪዳን ሊተካ ይገባል።
- ሙት የመሆናችን መገለጫ ፈቃድ አልባ መሆናችን ነው [ ኤፌ 2:3]።
- በፀጋ መዳን ሕይወትን በመቀበል የሚጀምር ነው። ስለዚህ የእኛ ድርሻ ሊኖርበት አይችልም።
- በፀጋ መዳን በተሰራው ስራ መሠረት መዳን እንጂ ያለ ስራ መዳን ማለት አይደለም።
ትግበራ :- በትህትና በሕብረት ውስጥ እንኑር።
ሁለተኛ ክፍለጊዜ - በፀጋ ብቻ መመረጥ
ሮሜ 11:1-7
- ሮሜ 11 ያለበት አውድ ከ 9ና 10 የተለየ አይደለም።
- እግዚአብሔር አይሁድን ጥሏል አልጣለም : ለዚህ ጳውሎስ ማሳያ ነው። ነገር ግን ምርጫ ግላዊና ቅድመ ሁኔታ የሌለው ነው [ቁ.1]።
- ምርጫ ሙሉ በሙሉ የእግዚአብሔር ድርጊት ነው።
- በቁ.4 ለኤልያስ የተሰጠው ምላሽ ምርጫን ሙሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር ይሰጣል።
- ያለ ቅድመ ሁኔታ መመረጥ በፀጋ ብቻ መመረጥ ነው [11:3]
ትግበራ :- ያለ ቅድመ ሁኔታ ተመርጣችኋል - በፀጋ ተመርጣችኋልና በምንም ዓይነት መከራ ታገሱ : ምክንያቱም ከፊት በማንም የማይሻር ክብር አለን።
- በፀጋ መዳን ብቻን ከአጠቃላይ ውድቀትና ከቅድመ ሁኔታ አልባ ምርጫ ነጥሎ መመልከት የማይሆን ነው።
- ከቅድመ ሁኔታ አልባ ምርጫ ውጪ በፀጋ መዳን የሚባል ነገር የለም።
- የቤተክርስቲያን ታሪክ መንግሥት በቤተክርስትያን እጁን ያስገባበት ጊዜ ያ የቤተክርስትያን ውድቀት እንሆነ ይነግረናል። ከዚህ በመነሳት አሁን መንግሥት ከተመሠረተው ካውንስል የተነሳ ፕሮቴስታንት በፕሮቴስታንት የሚያደርሰው ሊመጣ የሚችል መከራ አለና ራሳችሁን አዘጋጁ ተብለን ተመከርን። በዚህ መከራ ውስጥ ለመጽናታችን ዋስትና ያለ ቅድመ ሁኔታ መመረጣችን ነው!!
ጌዲና ሳይመን ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ!!
መርሃ ግብሩ ነገም የሚቀጥል ይሆናል።
ቦታ :- ጦና ህንጻ, ሲቲ ሆል
ሰዓት :- 3:00
ሁላችንም በቦታው በመገኘት ይህን አስደናቂ እውነት : ከቤተክርስትያን አበው ጋር በአንድነት እናውጅ! !
28/01/2013 ዓ.ም
ወላይታ ሶዶ

Coming soon...
07/09/2020

Coming soon...

This trailer is for the upcoming Amharic (Ethiopian Version) of Unpopular movie.

08/05/2020
20/03/2020

Address

S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Brightness of Christ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Brightness of Christ:

Share