Zake Insights / Mesfin

Zake Insights / Mesfin Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Zake Insights / Mesfin, Sodo.

ሰላም ቤተሰቦች! ዘኬ (መስፍን) ነኝ። 🇪🇹
​እንኳን ወደ Zake Insights official page በሰላም መጣችሁ።

ህይወት የምንደርስበት ግብ ሳይሆን፣ በየቀኑ የምንኖረው ጉዞ ነው።" 👣
ዓለምን በራሴ መነጽር 🔍 በምስልና በቃላት። 📸✍️

አለምን በኔ መነጽር አብረን እንቃኝ። 🔍✨

📍 ኢትዮጵያ | 🇪🇹 ዛኬ/መስፍን ነኝ follow አድረጉ ወዳቹዋለው

የAI መጨረሻ እና ሊከሰቱ የሚችሉ ስጋቶችየሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) ከጥቂት አመታት በፊት በልብ ወለድ ፊልሞች ላይ ብቻ የምናየው ክስተት ነበር  ዛሬ ግ...
29/04/2026

የAI መጨረሻ እና ሊከሰቱ የሚችሉ ስጋቶች

የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) ከጥቂት አመታት በፊት በልብ ወለድ ፊልሞች ላይ ብቻ የምናየው ክስተት ነበር ዛሬ ግን የእለት ተእለት ህይወታችን አካል ሆኗል። እንደ አንድ የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪ ይህ ቴክኖሎጂ ያለውን ግዙፍ አቅም ያህል ሊያስከትል የሚችለውን ጥልቅ ስጋት መገንዘብ ግድ ይላል። AI መጨረሻው ወዴት ነው? የሚለው ጥያቄ ለብዙዎቻችን ስጋት ሲሆን በተለይም የቴክኖሎጂው አቅም ከሰው ልጅ ቁጥጥር ውጭ የሚሆንበት (Singularity) ደረጃ ላይ ከደረሰ ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮች ቀላል አይደሉም።

● በመጀመሪያ ደረጃ የሰው ልጅን የማሰብ እና የመወሰን አቅም የሚተኩ የራስ-ገዝ መሣሪያዎች (Autonomous Systems) መስፋፋት የሞራል እና የሥነ-ምግባር (Ethical) ጥያቄዎችን ያስነሳሉ።
---AI መረጃዎችን ሰብስቦ የራሱን ውሳኔ መስጠት ሲጀምር ውሳኔዎቹ የሰውን ልጅ ደህንነት ታሳቢ ማድረጋቸውን ማን ያረጋግጣል? ከዚህ በተጨማሪ የሥራ ዕድል መጥበብ ሌላኛው ትልቅ ስጋት ነው። አውቶሜሽን ብዙ አምራች ዘርፎችን ሲረከብ ለሰው ልጅ የሚቀረው የሥራ ድርሻ ምን ሊሆን ይችላል? የሚለው ጉዳይ ለታዳጊ ሀገራት እንደ እኛ አይነቱ ትልቅ የቤት ስራ ነው።

●በሌላ በኩል የሳይበር ደህንነት ስጋቶች ሌላው ሊታሰብበት የሚገባ ነጥብ ነው። AI ለበጎ ተግባር እንደሚውለው ሁሉ ለከፋ የሳይበር ጥቃት ለሀሰተኛ መረጃዎች ስርጭት (Deepfakes) እና ለግላዊነት (Privacy) መጣስ እንደ ትልቅ መሣሪያ ሊያገለግል ይችላል። ይህ የቴክኖሎጂው ጨለማ ገጽታ የሰው ልጅን ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መስተጋብር ሊያናጋው የሚችል አቅም አለው።

●ይህንን የምላችሁ እንድንፈራ ሳይሆን እንድንዘጋጅ ነው እኛ ኮድ ስንጽፍ እንዴት ይሰራል?How it works? ብለን ብቻ ሳይሆን ምን ተጽዕኖ ያመጣል? What is the impact? ብለን መጠየቅ አለብን። ቴክኖሎጂ ያለ ሰብአዊነት አደገኛ ነው።

​የእኔ ራዕይ ኢትዮጵያ ውስጥ እነዚህን ቴክኖሎጂዎች ስንጠቀም ከባህልና ከእሴቶቻችን ጋር የተጣጣመ፣ ሰውን የማይተካ ነገር ግን ሰውን የሚያግዝ (Human-Centric AI) መገንባት ነው። ለዚህ ደግሞ የሁላችንም ንቁ ተሳትፎና ጥንቃቄ ያስፈልጋል።

እናንተስ የ AI እድገት ያስፈራችኋል ወይስ ያስደስታችኋል? ከላይ ከተጠቀሱት ስጋቶች የትኛው ይበልጥ ያሳስባችኋል?ሀሳባችሁን ኮሜንት ላይ አጋሩኝ! 👇

Follow ማድረግ አይረሳ

Abiy Ahmed Ali

ነዳጅ ቀድቶ መደበቅ ያበቃለታል— መቅደስ በዛብህ (ወላይታ ሶዶ  ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የመምሪያው ኃላፊ)በወላይታ ሶዶ ከተማ በየማዕዘኑ የሚታየው ረጅም ሰልፍና የእንግልት ምንጭ የተሽከርካ...
17/04/2026

ነዳጅ ቀድቶ መደበቅ ያበቃለታል— መቅደስ በዛብህ (ወላይታ ሶዶ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የመምሪያው ኃላፊ)

በወላይታ ሶዶ ከተማ በየማዕዘኑ የሚታየው ረጅም ሰልፍና የእንግልት ምንጭ የተሽከርካሪ ማጣት ሳይሆን የስነ-ምግባር መጥፋት ነው በሚል መምሪያው ዛሬ ከባድ እርምጃ መጀመሩን አውጇል።

የመምሪያው ኃላፊ መቅደስ በዛብህ እንደገለጹት አንዳንድ የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ከማደያ ነዳጅ ቀድተው ከወጡ በኋላ የሚያደርጉት ነገር እጅግ አስገራሚ ነው።

አገልግሎት መስጠት ሲገባቸው፦
⛔️ወደ መናኸሪያ ሳይገቡ ጠፋ ይላሉ።
⛔️መኪናቸውን መናኸሪያ ግቢ ውስጥ ደብቀው ሹፌርና ረዳት የውኃ ሽታ ይሆናሉ

​ይህ ድርጊት ሆን ተብሎ ሕዝብን ለማንገላታት የሚደረግ የጥቁር ገበያ(black Market )ሴራ አካል መሆኑ ተጠቁሟል።

መምሪያው ለወደፊቱ እንዲህ ዓይነት ድርጊት በሚፈጽሙ አካላት ላይ የማያዳግም ቅጣት መጣሉን እንደሚቀጥል ተገልጿል

ቅጣቱም፦

●​ለተከታታይ ሁለት (2) ወራት ከስምሪት ማገድ
●​የ50,000 (ሃምሳ ሺህ) ብር የገንዘብ መቀጮ

"​አገልግሎት የመስጠት ግዴታ እያለባቸው ሆን ብለው ሕዝብን የሚያንገላቱ አካላትን በዝምታ አንመለከትም" — መቅደስ በዛብህ

ይህ እርምጃ ለከተማዋ ነዋሪ ትልቅ እፎይታ ነው ነገር ግን ጥያቄው፦ ይህ ዘመቻ ለዛሬ ብቻ ነው ወይስ ዘላቂ?" የሚለው ነው። ነዳጅ በቅናሽ ዋጋ እየቀዱ ሕዝብን የሚያንገላቱ ትርፍ አሳዳጆችን ስርዓት ለማስያዝ የሕዝብ ጥቆማ ወሳኝ ነው።

Zake Insights — የእውነት ድምፅ የመረጃ ምንጭ!
ተጨማሪ ወቅታዊና አስተማሪ መረጃዎችን ለማግኘት Zake Insights ገጻችንን ይከተሉ (Follow) Zake Insights / Mesfin

​👇 Like | Comment | Share
​ **o **oAlert **oCity

15/04/2026

ከቀኑ ድካም አርፋችሁ በሰላም አድራችሁ ለነገው አዲስ ተስፋ እንዲያደርሳችሁ ምኞቴ ነው። መልካም አዳር!

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር ያለ ስምምነት ተበትኗል!​በፓኪስታን አስተናጋጅነት ለ21 ሰዓታት ያህል በዝግ በሮች ሲካሄድ የቆየው የአሜሪካ እና የኢራን ከፍተኛ ድርድር ያለ ምንም ውጤት መጠና...
12/04/2026

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር ያለ ስምምነት ተበትኗል!

​በፓኪስታን አስተናጋጅነት ለ21 ሰዓታት ያህል በዝግ በሮች ሲካሄድ የቆየው የአሜሪካ እና የኢራን ከፍተኛ ድርድር ያለ ምንም ውጤት መጠናቀቁን የአሜሪካው ም/ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ በይፋ አስታወቁ።

​📌 የውይይቱ ዋና ዋና ነጥቦች፡-

●​የዋሽንግተን ጥረት፡ ዋሽንግተን "የመጨረሻ እና ምርጥ" (Final and Best Offer) የተባለ የሰላም አማራጭ ብታቀርብም፣ የቴህራን ተወካዮች የቀረበውን ሃሳብ ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርገውታል።

●​የኒውክሌር ጉዳይ፡ በኒውክሌር ጦር መሣሪያ ዝግጅት እና ቁጥጥር ጉዳይ ላይ ኢራን ምንም ዓይነት አዎንታዊ ቁርጠኝነት ለማሳየት ፈቃደኛ አልሆነችም። ይህም ለቀጣዩ ቀጣናዊ ሰላም ትልቅ ስጋት መሆኑ ተገልጿል።

●ከባድ ማስጠንቀቂያ፡ ስምምነት ላይ አለመደረሱ "ከአሜሪካ ይልቅ ለኢራን እጅግ መጥፎ ዜና ነው" ሲሉ ም/ፕሬዝዳንት ቫንስ አስታውቀዋል። ይህም በኢራን ላይ አዳዲስ እና ጠንከር ያሉ ማዕቀቦች ሊጣሉ እንደሚችሉ አመላካች ተደርጎ ተወስዷል።

​🔍 ቀጣዩ እርምጃ ምን ይሆን?

​የአሜሪካ ልዑክ ቡድን በዛሬው ዕለት ወደ ዋሽንግተን የተመለሰ ሲሆን፣ እስካሁን ከኢራን ወገን በይፋ የተሰጠ ምላሽ የለም። ውጥረቱ ወደ ሌላ ምዕራፍ ሊሸጋገር እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።

​💬 የእናንተ አስተያየት ምንድነው?

​ኢራን የቀረበላትን አማራጭ ውድቅ ማድረጓ በቀጣናው ላይ ምን ዓይነት ተጽዕኖ ያመጣል?

​ሃሳብዎን በኮሜንት መስጫው ላይ ያካፍሉን!

​👇 ለተጨማሪ ፈጣን እና እውነተኛ መረጃዎች Zakeinightsን ይከተሉ!!

በወላይታ ሶዶ የህዝብን ብሶት የሰማው የትራፊክ ፖሊስ ጀብድዛሬ በወላይታ ሶዶ ከተማ  በሥራው ዓለም ለሚሰማሩ ሁሉ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ የሕሊና ዳኝነት የታየበት ድንቅ ትራፊክ ፖሊስ ​ዛሬ ...
11/04/2026

በወላይታ ሶዶ የህዝብን ብሶት የሰማው የትራፊክ ፖሊስ ጀብድ

ዛሬ በወላይታ ሶዶ ከተማ በሥራው ዓለም ለሚሰማሩ ሁሉ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ የሕሊና ዳኝነት የታየበት ድንቅ ትራፊክ ፖሊስ

​ዛሬ ከወላይታ ሶዶ ተነስቶ ወደ በቅሎ ሰኞ በመጓዝ ላይ የነበረ አንድ የሕዝብ ማመላለሻ መኪና ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ ከተሳፋሪዎች ላይ ከልክ በላይ ታሪፍ ያስከፍላል። ይህንን የታዘቡት እኚህ የሕዝብ ወገን የሆኑ ፖሊስ መኪናውን በማስቆም ተገቢ ያልሆነ ትርፍ የተወሰደውን እያንዳንዱን ሳንቲም እስከመጨረሻው ለተሳፋሪዎቹ አስመልሰዋል።

​ይህ ተግባር ተራ የሥራ ግዴታ ሳይሆን፣ "የሕዝብን እንባ መጥረግ" የሚባል ታላቅ የጀግንነት ሥራ ነው።
​በዚህ የጀግንነት ተግባር የተስተዋሉ ዋና ዋና ነጥቦች፦
​የፍትህ ሚዛን ጠባቂ፦ በድሃው ተሳፋሪ ኪስ ላይ የተቃጣን ዝርፊያ በአይነ ቁራኛ በመከታተል፣ ፍትህን በአደባባይ አንግሰዋል።

​የማይደለል ሕሊና፦ "የኔ ምን አገባኝ" የሚለውን ደካማ አስተሳሰብ በመቃወም፣ ለሕዝብ አገልግሎት የተሰጠውን ኃላፊነት በሙሉ ግርማ ሞገስ ተወጥተዋል።

​ለሌሎች አርአያነት፦ ይህ ፖሊስ በወላይታ ሶዶ አውራ ጎዳናዎች ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በየልባችን ውስጥ የታማኝነትን ባንዲራ ከፍ አድርጎ ሰቅሏል።

​እንደነዚህ ያሉ የሀገር ባለውለታዎችና የሕዝብ ጠባቂዎች ባሉበት፣ የከተማችንና የሀገራችን ብልጽግና የተረጋገጠ ነው። እውነተኛው ጀግና ማለት በጦር ሜዳ ብቻ ሳይሆን፣ እንዲህ ባለው የሰላም ሜዳ የድሃውን እንባ የሚመልስ ጭምር መሆኑን ዛሬ በተግባር አይተናል።

​ክብርና ምስጋና ለዚህ ለሕዝብ ወገን ለሆነው የትራፊክ ፖሊስ!
በዘኪ (መስፍን) የተጻፈ ተጨማሪ ወቅታዊና አስተማሪ መረጃዎችን ለማግኘት Zake Insights ገጻችንን ይከተሉ (Follow)።
​ #ወላይታሶዶ #ታማኝነት #ኢትዮጵያ **o

በፎቶው ላይ የምታዩት በግርማውና በብዝሃነቱ የሚታወቀው ግዙፍ የከብት ገበያ በወላይታ ዞን ከሚገኙ በርካታ የንግድ ስፍራዎች አንዱ ነው።እስቲ እናንተ:-📍 ይህ ገበያ በየትኛው ወረዳ ወይም ከተ...
10/04/2026

በፎቶው ላይ የምታዩት በግርማውና በብዝሃነቱ የሚታወቀው ግዙፍ የከብት ገበያ በወላይታ ዞን ከሚገኙ በርካታ የንግድ ስፍራዎች አንዱ ነው።

እስቲ እናንተ:-
📍 ይህ ገበያ በየትኛው ወረዳ ወይም ከተማ ውስጥ ይገኛል?
📍 ስሙስ ማን/ምን ይባላል?
​የምታውቁ በኮሜንት አሳውቁን! 👇
​ **o **o

በከተማችን ከኮካቴ እስከ ግብርና ኮሌጅ እየተገነባ ያለው አዲሱ አስፋልት መንገድ  ገና ሳይጠናቀቅና የምርቃት ሪባን ሳይቆረጥለት "እየተፈረካከሰ" ይገኛል። ይህ ለከተማችን እድገት ተስፋ የተጣ...
06/04/2026

በከተማችን ከኮካቴ እስከ ግብርና ኮሌጅ እየተገነባ ያለው አዲሱ አስፋልት መንገድ ገና ሳይጠናቀቅና የምርቃት ሪባን ሳይቆረጥለት "እየተፈረካከሰ" ይገኛል። ይህ ለከተማችን እድገት ተስፋ የተጣለበት ፕሮጀክት ዛሬ ለስጋት ምንጭ እየሆነ መጥቷል።

ልማት ማለት በአይን የታየ ብቻ ሳይሆን፣ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት የሚሰጥና ጥራቱን የጠበቀ መሆን አለበት። ለስም ብቻ የሚሠራ "አስፋልት" ለማን ይጠቅማል?

ጥሪያችን ለሚመለከታቸው አካላት፦

○ ​የመንገዱ የጥራት ደረጃ በአስቸኳይ በገለልተኛ አካል እንዲፈተሽ!
○​ኮንትራክተሩና ተቆጣጣሪ መሃንዲሶች ለዚህ ጉድለት ተጠያቂ እንዲሆኑ!
○​ጉድለቱ ሳይስተካከልና ጥራቱ ሳይረጋገጥ ርክክብ እንዳይፈጸም!

✍️በዘኬ (መስፍን) ካሌብ
​👉 Follow me | Like | Share
​ **o **o **oNews #ዎላይታ #ሶዶ #ልማት #ጥራት #ተጠያቂነት

በአሁኑ ወቅት የአለም አቀፍ ፖለቲካ ትኩረት በመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት ላይ አርፏል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሚስተዋሉ ሁለት ተቃራኒ እውነታዎች የሀገራትን "ሃያልነት" ትርጉም ዳግም እንድንመረ...
06/04/2026

በአሁኑ ወቅት የአለም አቀፍ ፖለቲካ ትኩረት በመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት ላይ አርፏል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሚስተዋሉ ሁለት ተቃራኒ እውነታዎች የሀገራትን "ሃያልነት" ትርጉም ዳግም እንድንመረምር ያስገድዱናል። በአንድ በኩል፣ አንዲት ነፍስን ለማዳን የቴክኖሎጂና የዲፕሎማሲ አቅሟን የምታዘምተው አሜሪካ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በገዛ ግዛቷ ውስጥ ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግላቸውን መሪዎቿንና እንግዶቿን መከላከል ያልቻለችው ኢራን።

የአንድ ሀገር ጥንካሬ የሚለካው በጦር መሣሪያ ብዛት ወይንስ ያንን መሣሪያ በሚያዘምነው የደህንነት መዋቅር? ይህ ጥያቄ የኢራንን ወቅታዊ ሁኔታ ለትችት የሚጋብዝ ያደርገዋል።

​የአሜሪካ ስትራቴጂ፦ አሜሪካ ለአንድ ወታደር የምታደርገው ርብርብ ከሰብአዊነት ባለፈ ትልቅ የፖለቲካ መልዕክት አለው። "ዜጋዬን በማንኛውም ዋጋ አስከብራለሁ" የሚለው መርህ ለውስጥ አንድነትና ለውጭ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ትልቅ መሣሪያ ነው። ይህ ጥንካሬ የሚመነጨው ከተራቀቀ የስለላ መረብና ፈጣን ምላሽ ሰጪ የልዩ ኃይል ስምሪት ነው።

​የኢራን ተጋላጭነት፦ ቴህራን "የመካከለኛው ምስራቅ የኃይል ሚዛን ነኝ" ብትልም፣ በገዛ ቤቷ ውስጥ የሚፈጸሙ ከፍተኛ ግድያዎችና የደህንነት ጥሰቶች የመዋቅሯን መበሳት ያሳያሉ። የደህንነት መዋቅር "እንደ ወንፊት" ሲበሳ፣ የሚለቀቁ የዛቻ ቪዲዮዎችና ወታደራዊ ትርኢቶች ዋጋቸው እየቀነሰ ይሄዳል።

ብዙዎች የኢራንን የአጸፋ እርምጃና የቆራጥነት ንግግሮች እንደ "ጀግንነት" ይቆጥሩታል። ሆኖም በፖለቲካ ሳይንስ እይታ፣ ጀግንነት ከስሜታዊነት ይልቅ በውጤት ይለካል።

የገዛ ቤቱን በር መቆለፍ ያልቻለ ኃይል፣ ክልላዊ ተጽዕኖው አጠራጣሪ ይሆናል።አሜሪካና አጋሮቿ በጠላት ቀጠና ውስጥ ገብተው ኦፕሬሽኖችን መፈጸማቸው የመረጃ የበላይነትን (Intelligence Superiority) ያሳያል።ፖለቲካ በጭብጨባና በስሜት ሳይሆን በተጨባጭ የመከላከል አቅም የሚመራ መሆኑን የኢራን ወቅታዊ ሁኔታ ማሳያ ነው።የአንበሳ ቆዳ የለበሰ ሁሉ አንበሳ አይደለም" እንዲሉ፣ የሀገር ጥንካሬ የሚለካው በጠመንጃው ርዝመት ነው ወይስ ዜጎቿንና መሪዎቿን ባለችበት የመጠበቅ ብቃት?

አሜሪካ አንድ ወታደሯን እንዴት እንዳዳነች ስታይ ..በአንጻሩ ደግሞ ኢራን የራሷን መሪዎች በራሷ ግዛት መጠበቅ የማትችል መሆኗን ስታይ ።ኢራን ጀግና ናት ሚሉ ሰዎች ምናቸውን ነው ሚያማቸው!????

የእናንተስ እይታ ምንድነው? የሀገር ክብር የሚለካው በንግግር ነው ወይስ በተግባር?

Follow like share Zake Insights / Mesfin
​✍️ Zake/Mesfin - Insights

የማይረሳ መሪ! 🕰️           ​የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን በአንድ ቃል ግለጹ ቢባሉ ምን ይላሉ?     ​መልሳችሁን በኮሜንት አስቀምጡልን! 🇪🇹 Follow Zake Insi...
05/04/2026

የማይረሳ መሪ! 🕰️
​የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን በአንድ ቃል ግለጹ ቢባሉ ምን ይላሉ?

መልሳችሁን በኮሜንት አስቀምጡልን! 🇪🇹
Follow Zake Insights / Mesfin

04/04/2026

ልቡ በአምላኩ የታመነ

በዲ/ን ዳንኤል ክብረት

📌ላለፉት ስምንት ዓመታት የማውቃቸው የዐቢይ ስምንት ገንዘቦች እነዚህ ናቸው

1. ቁጭት፡- የኢትዮጵያን ታሪኳን ያነበበ፤ ቅርሶቿን የጎበኘ፤ተራሮቿን የወጣ፤ ዋሻዎቿን የመረመረ፤ የመስጊዶቿንና የአብያተ ክርስቲያናቷን ውስጥ የሚያውቅ፤ በዚህ የተነሣም የኢትዮጵያ ኋላ ቀርነት፣ ድህነትና ተዋርዶ የሚቆጨው፡፡ ስለሚቆጨውም ኢትዮጵያን ወደ ትክክለኛ ቦታዋ ለማድረስ የሚለፋ፡፡

2. እልህ፡- የኢትዮጵያ ድህነትና ኋላ ቀርነት እንደሚቆጨው መሪ፤ ንጋቷን ሳያይ፣ ታሪኳን ሳይቀይር፣ ገናንነቷን ሳይመልስ “ለዓይኖቹ ዕንቅልፍ፣ ለሽፋሽፍቶቹ ዕረፍት” የሌለው፡፡ ከድህነትና ከኋላ ቀርነት ጋር እልህ የተጋባ፡፡ ቃል የገባለትን፣ ያመነበትንና ለኢትዮጵያ ይጠቅማል ያለውን - ቀን ለፍቶ፣ ሌት ተንከራትቶ ሳያሳካ በቃኝ የማይል፡፡ የትም፣ መቼም፣ በምንም ሁኔታ ከዓላማው የማይዛነፍ፡፡ ከኋላው ያለውን እየተወ ከፊቱ ያለውን ለመያዝ ያለ ማቋረጥ የሚዘረጋ፡፡

3. ልቡ በአምላኩ የታመነ፡- የአንበሳ ግሣት፣ የሌት ወፍ ጩኸት፣ የእባቡ ፉጨት፣ የዕንቁራሪቱ ማሽካካት ምንም የማይመስለው፡፡ ሁሉም ከአምላኩ በታች መሆኑን የሚያምን፡፡ በባሕሩ ላይ ሲራመድ፣ ማዕበሉን እንዳይፈራ ዓይኑን ከፈጣሪው ላይ ያልነቀለ፡፡ ሁሉን የያዘውን የያዘ፤ ማንም የማያሸንፈውን የተጠጋ፤ የማይለወጠውን የተማመነ፤ ዋጋን ለሠሪ፣ ድልን ለፈጣሪ የሚሰጥ፡፡

4. ትጋት፡- ከድህነትና ከኋላ ቀርነት ጋር በገባው እልህ የተነሣ ትጋት እግሩ፣ ልፋት ባቡሩ የሆነ፡፡ ቀን እንደ ሠራዊት፣ ሌሊት እንደ መላእክት ሲለፋ የምታየው፡፡ ፕሮጀክትን እንደ ልጁ፣ ሥራን እንደ ወዳጁ የሚያይ፡፡ ሕዝበ አዳም እንደ ቤተልሔም ሰዎች ሲተኛ፣ እሱ እንደ እረኞቹ ወደ ፕሮጀክቶቹ ሌት የሚገሠግሥ፡፡

5. ፍቅር፡- በትጋት የሚያገለግላትን፣ ከድህነቷና ከኋላ ቀርነቷ ጋር እልህ የተጋባባትን፣ የስሟንና የታሪኳን ያህል ባለመሠልጠኗ የሚቆጭላትን ኢትዮጵያን ከልቡ የሚወዳት፡፡ ፍቅሩን በዜማ፣ መንሰፍሰፉን በቁዘማ የማይግልጥ፡፡ ከዚያ ይልቅ - ፍቅሩን በመሥዋዕትነት፣ መንሰፍሰፉን በትጋት የሚገልጥላት፡፡ ልጅ ሆኖ የተዋጋላት፤ መሪ ሆኖ ግንባር የወረደላት፤ የኢትዮጵያ ፍቅር እንደ ሞት የበተረታበት፡፡

6. ሁሌ አዲስ፡- የሚወዳትን ሀገር ዕለት ዕለት አዲስ የሚያደርጋት፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትርነቱን በዓመት ሳይሆን በዕለት የሚለካ፡፡ ለኢትዮጵያ - ትናንት ምን አለፈ? ዛሬ ምን ተሰለፈ? ነገ ምን ተነጠፈዠ፣ የሚል፡፡ የመቶ ዓመታትን ዝግመት በወራት ፍጥነት የሚያካክስ፡፡ ኢትዮጵያን እንደ እናቱ የሚያይ፤ በዚህ የተነሣ የፈሰሰ ሊያቀና፣ የተሰበረ ሊያጸና፣ ትናንትን ሊያድስ፣ ነገን ሊቀይስ የሚተጋ፡፡

7. ፈጠራ፡- ፍጥነት ቁርሱ፣ ፈጠራ ትራሱ፡፡ በፍቅር እንደመር፣ በይቅርታ እንሻገር፤ ከቢሮ እስከ ሀገር፤ አረንጓዴ ዐሻራ፤ ገበታ ለሸገር፤ ገበታ ለሀገር፤ ገበታ ለትውልድ፤ የሌማት ትሩፋት፤ ጽዱና አረንጓዴ ሀገር፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ 5 ሚልዮን ኮደርስ፣ የኮሪደር ልማት፣ ኢትዮጵያ ታምርት፣ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ ወዘተ.፤ ስምንት ዓመትን እንደ ስምንት መቶ ዓመት የሠራበት፡፡

8. የማንም/ የሁሉም፡- አወላለዱ፣ አስተዳደጉ፣ የትዳር ሕይወቱ፣ የእምነት ጉዞው፣ የባህል ሥሪቱ፣ የአገልግሎት መንገዱ - የሁሉ የሆነ፡፡ በዚህም የተነሣ የማንም የግል ንብረት ያልሆነ፡፡ ከሁሉም ያለው፡፡ ለሁሉም የሚሰጠው ያለው፡፡ የኢትዮጵያ ለመሆን የተሠራ፡፡ በአንድ ሳጥን ሊቆልፉት የማይቻል፣ አማካይ ለመሆን የታደለ፡፡

"አማን አማን እብለከ፤ ከመ ዘነአምር ንነግር፤ ወበዘርኢነ ሰማዕተ ንከውን -
እውነት እውነት እልሃለሁ። የምናውቀውን እንናገራለን፤ ያየነውንም እንመሰክራለን" እንዲል መጽሐፉ።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

በነዳጅ ሰበብ የሚፈጸም የኢኮኖሚ ደባና የህዝብ እንባ!​በአሁኑ ወቅት የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ መናር በሁሉም አገራት ላይ የራሱን ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑን እንረዳለን። መንግስትም የነዳጅ ድ...
04/04/2026

በነዳጅ ሰበብ የሚፈጸም የኢኮኖሚ ደባና የህዝብ እንባ!

​በአሁኑ ወቅት የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ መናር በሁሉም አገራት ላይ የራሱን ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑን እንረዳለን። መንግስትም የነዳጅ ድጎማን በማንሳቱ የተወሰነ የታሪፍ ጭማሪ መኖሩ የማይቀር ሀቅ ነው። ነገር ግን፣ "ነዳጅ ጨመረ" የሚለው ሰበብ በወላይታ ሶዶ እና በባይራ (በቆሎ ሰኞ) መስመር ላይ ለሚታየው ዓይን ያወጣ ዘረፋ መሸፈኛ ሊሆን አይችልም!

እውነታው :-

●​የጉዞ ርቀት፦ 16 ኪሎ ሜትር ብቻ።
●ተገቢው ታሪፍ፦ 55 ብር አካባቢ።
●​አሁን የሚጠየቀው፦ 200 ብር!

​ለመሆኑ በየትኛው የኢኮኖሚ ስሌት ነው በ16 ኪሎ ሜትር ውስጥ የ300% ጭማሪ በአንድ ጀምበር የሚደረገው? ይህ የነዳጅ ዋጋ መጨመር ውጤት ሳይሆን፣ የቁጥጥር ስርአቱ መውደቅና ህዝቡን ለቀን ጅቦች አሳልፎ የመስጠት ፖለቲካዊ ቸልተኝነት ነው።
​ለሚመለከታቸው አካላት፦
የዓለም የነዳጅ ገበያ ተለዋዋጭነትን ህዝቡ ተገንዝቧል፤ ነገር ግን ይህ ግልጽ የትርፍ ማጋበሻ ደባና የድሃው ኪስ ላይ የሚደረግ ወረራ በዝምታ ሊታለፍ አይገባም። የትራንስፖርት ባለስልጣናት ሆይ! በየመንገዱ ቆማችሁ የምታዩት ይሄንኑ የህዝብ እንባ አይደለምን? ወይስ የአሽከርካሪዎችና የደላሎች ህገ-ወጥ ስምምነት ከህዝብ መብት በላይ ሆኖባችኋል?

16 ኪሎ ሜትር ለመጓዝ 200 ብር መክፈል ድሃውን ህዝብ ካለበት የኑሮ ውድነት በተጨማሪ "አትንቀሳቀስ" ብሎ እንደመቅጣት ይቆጠራል። ይህ አሰራር በአስቸኳይ ሊታረም ይገባል!
​መብታችንን እናስከብር!
ዝምታው ይብቃ!

ይህ አሰራር በአስቸኳይ ሊታረም ይገባል! የሕግ የበላይነት ይከበር! የድሃው እንባና ጩኸት የሚሰማበት የቁጥጥር ስልት ተግባራዊ ይደረግ!

✍️zake/Mesfin Kaleb
​ #ባይራ #ኢትዮጵያ

Address

Sodo

Telephone

+251975130650

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zake Insights / Mesfin posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Zake Insights / Mesfin:

Share