Apostolic generation

Apostolic generation Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Apostolic generation, Religious organisation, Areka, Sodo.

ማርቆስ 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁹ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፥
³⁰ አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።

የዓለም አቀፍ ጉባኤ            #ዋራበኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን 35ኛው ዙር በስዳማ ክልል ዋራ በሚባል ቦታ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ከ ሐሙስ ጀምራ እያ...
15/03/2026

የዓለም አቀፍ ጉባኤ
#ዋራ
በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን 35ኛው ዙር በስዳማ ክልል ዋራ በሚባል ቦታ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ከ ሐሙስ ጀምራ እያካሄደች ትገኛለች።

በጉባኤ ከተለያዩ ሀገራት ኢትዮጽያዊ ያልሆኑ ነገር ግን ሰማያዊ ዜጋ የሆኑት ኢትዮጵያን እግዚአብሔር እንደባረካት እና ይህ ድንቅ ሥራ ወደ እኛም ይደርስ እያሉ እየመሰከሩ ይገኛሉ።

ይህ ጉባኤ ነገ እሁድ ማለትም 6/07/2018 ዓ.ም የመጨረሻ ስለሆነ ሁላችሁም የበረከት ተካፋይ እንድትሆኑ በክርስቶስ ፍቅር ተጋብዛችኋል።

በሌላ በኩል በኮንፈረንሱ እየተከናወነ ያለው ተአምራት ይህን ያህል ነው ለማለት እና ለመገለፅ የሚከብድ ቢሆንም በእኛ ቤት አድራጊ ራሱ ኢየሱስ ነው የ ተአምራት ባለቤት ስሙ ይመስገን።

ስለሆነም አንዳንድ ትምህርት የያዙት ነገሮችን ለውስጥ የሚናገር እና ለውጭ የሚናገሩትን ታሳብ በማደረግ ያሉትን ትምህርትና ፕሮግራሙን መጨረሻ ወደ እናንተ እናደርሳለን።
በዚህ ቦታ በመኖሬ ዕድለኛ ነኝ🙏
International conference



In the 35th round of the Ethiopian Apostolic Church, the Apostolic Church is holding a great spiritual conference starting from Thursday at a place called Wara in Sadama region.

In the conference, non-Ethiopians from different countries, but who are heavenly citizens, are testifying saying that God has blessed Ethiopia and that this wonderful work will reach us.

This conference will end tomorrow, Sunday, 6/07/2018, so all of you are invited by the love of Christ to be part of the blessing.

On the other hand, the miracles that are happening at the conference are so much that it is difficult to say and explain, but it is Jesus himself, the maker of our house, praise be to the owner of miracles.

Therefore, we bring to you the end of the lesson and the program, which contains some things that speak inwardly and those that speak outwardly.

I am lucky to live in this place

ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

ይህማ  ውርደት ነው ሁለተኛው አዳም ከመጀመሪያ ጋር ተቀላቀለ ማለቱ‼️እግዚአብሔር ሰውን በመፈጠሩ የተጸጸተው ሰው ልጅ የራሱ የሆነው ስሜትና ፍቃድ  ያለው ስሆን የፍርድ ቀን እስከ ምደርሰው ...
10/03/2026

ይህማ ውርደት ነው ሁለተኛው አዳም ከመጀመሪያ ጋር ተቀላቀለ ማለቱ‼️

እግዚአብሔር ሰውን በመፈጠሩ የተጸጸተው ሰው ልጅ የራሱ የሆነው ስሜትና ፍቃድ ያለው ስሆን የፍርድ ቀን እስከ ምደርሰው ድረስ አምላክ የለም ማለትም ይችላል እግዚአብሔርም ዝም ብሎ ያያል።

በዘፍጥረት ምዕራፍ 3 ላይ የመጣውን ወድቀት እግዚአብሔር ራሱ ለማክሸፍ እና ለመበቀል የዘመናት ዕቅድና ሃሳብ ነበረው።

በመሆኑ ሁሉንም በግዜው የምሰራ አምላክ ይህን ወድቀት በአዳም የመጣውን ወድቀት በ ሁለተኛው አዳም ለመበቀል ሁለተኛው አዳምን አዘጋጀ።
👉በራሱም ላይ የበቀል ልብስ [ ሥጋ] ለበሰ
ትንቢት ኢሰያስ 59:17
የበቀል ልብስ ለብሶ በዘፍጥረት 3 ላይ በመጀመሪያ ሰው ሆኖ የጣለውን ዲያብሎስ ተበቀለ እንደ መጀመሪያ ሰው ነው በማለት ለፈተና ስመጣ መልሱ ይህ ነው:-
👉 ጌታ አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ተጽፏል ነው።
የመጀመሪያ ሰው ሰው ነው እንጂ አምላክ አይደለም

ይህ ሁለተኛው አዳም ቃል ሥጋ የሆነው ሰው ስሆን ከመጀመሪያ አዳም ከምድር ከተፈጠረው አዳም ጋር ምንም አልተቀላቀለም
የመጀመሪያ አዳም ከመረታዊ ነው ሁለተኛው አዳም ግን ከሰማይ ነው ይላል የእግዚአብሔር ቃል።

ሰዎች ደግሞ የራሳቸው ስሜትና ፍቃድ ከመኖሩ የተነሳ በመጀመሪያ አዳምም የእግዚአብሔርን ትዕዛዝና ትምህርት በመተው ወድቀት እንዳመጣ አሁን ደግሞ ከመጀመሪያ አዳም የተቀላቀለ ነው በማለት በ ውሳኔ አጸደቁ።

እኛም በዚህ ዘመን ይህ ወንጌል አደራ የደረሰብን ትውልድ በ እግዚአብሔር ቃል መፈተሽን ዘውትር ሥራ አደረገን አንድም ቦታ ከመጀመሪያ አዳም ሥጋ ተቀላቀለ የሚል አጣን።

ከመጀመሪያ አዳም ጋር የተደበላለቀ ነው ያሉትን በጥሞና ጠይቀናቸው ምንም መልስ አልሰጡንም በቃ የተወሰነ ነው ከማለት ውጭ ።

ይህማ ውርደት ነው ሁለተኛውን አዳም ከመጀመሪያ አዳም ጋር ተቀላቀለ በማለት መወሰኑ ፤እኛም በእግዚአብሔር ቃል የሌለውን አንቀበልም አለን።

የመጀመሪያ አዳም[ የሥጋን ሰውነት] በመገፈፍ በእጅ ባልሆነ በክርስቶስ መገረዝ በጥምቀት ከእርሱ ጋር የመጀመሪያ አዳም በውኃ ቀብራችሁ ሁለተኛው አዳም በመልበስ ከእርሱ ጋር ለመነሳት ኑ እያለን ዘውትር መጥራታችን ቀጠለን ጌታም የምድኑት ነፍሳት ዕለት ዕለት እየጨመረ ከእኛ ጋር ይሠራል።
ስሙ ይመስገን ኢየሱሴ❤

👉 የሥጋንም ሰውነት በመገፈፍ፥ በክርስቶስ መገረዝ፥ በእጅ ባልተደረገ መገረዝ በእርሱ ሆናችሁ ደግሞ ተገረዛችሁ። በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ።
ቆላስይስ 2:10_11

ሁለተኛውን አዳም ከመጀመሪያ አዳም ጋር አታቀላቀሉ አልተጻፈም፤ ከተጻፈው አትለፈ የሚል የእግዚአብሔር ቃል በመጨረሻ ለፍርድ ይጠብቃል።

ማንም እንድፈረድ እኔ ወንድማችሁ አልፈለግም ለዚህ ነው በገዛ ፍቃዴ ዘውትር ወንጌል መናገር ሥራ ያደረኩት ከእኔ የሆነው አንድም የለም ሁሉ ከኢየሱስ ነው።

Share ማድረግ ወንጌል የዋጋ ተካፋይ ያደረጋል 🙏

ወንድማችሁ ነኝ
ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

ጥምቀት ያድናል።በእኛ ቤት ሁሉ ከእግዚአብሔር ቃል ነው🙏በመጀመሪያ ጥምቀት የኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ መሆኑን እውቁ ኢየሱስ ክርስቶስ ያዘዘውን ትዕዛዝ ወደ ጎን ትቶ ኢየሱስን እወዳለሁ ማለት ...
05/03/2026

ጥምቀት ያድናል።
በእኛ ቤት ሁሉ ከእግዚአብሔር ቃል ነው🙏

በመጀመሪያ ጥምቀት የኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ መሆኑን እውቁ ኢየሱስ ክርስቶስ ያዘዘውን ትዕዛዝ ወደ ጎን ትቶ ኢየሱስን እወዳለሁ ማለት አይቻልም።

የእርሱ አዳኝነት ሁላችንም የምናውቀው እና የምናምነው ሆኖ ሳለ እርሱ ራሱ በየዘመናቱ ሰው ልጆችን ለማዳን ትዕዛዝ ይሰጣል።

ለምሳሌ በ ጥፋት ውኃ ግዜ መርከብ እንድሰራ ኖኄን አዘዘ ለምን መርከቡን ሳይሠራ አላዳነም? መርከብ ሰርቶ በመርከቡም የሚያድነው ራሱ እግዚአብሔር ነው።

ኖኄም እግዚአብሔር የጥፋት ውኃ እንዲያመጣ ተናግሯል እኔም አምኛለሁ ያድናል በማለት ቁጭ አላለም ከራሱ የሚጠበቀውን እያደረገ መርከቡን እየሠራ ነው የጠበቀው እግዚአብሔርም አዳነ።

በአድስ ክዳን በጥምቀት አሮጌውን ማንነት በክርስቶስ ተቀየረ መነሳቱ ለአንተ/ች መቼ ጎዳ እና የኢየሱስን ትዕዛዝን ትንቃለህ
ይህኮ ለአሕዛብ ያልተሰጠ ዕድል ነበረ ነገር ግን የወደደን ለአድስ ልደት በሚሆን በመታጠብ ያዳነ ኢየሱስ ይመሰገን።

እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም።
ቲቶ 3:5

አብዛኞቹ ይህን ላለመቀበል ኢየሱስ ያድናል እንጂ ጥምቀት አይድንም ይላሉ ኢየሱስ አንተን በ አድስ ልደት በሚሆነው በመታጠብ ዳግመኛ ተወልድ ክርስቶስን ልበስ ይላል አለበለዚያ መዳን አታገኘውም ይላል።

የተኛው ሐዋርያ ወይም ነቢይ በመጽሐፍ ቅዱስ አድስ ኢየሱስ ክርስቶስን ያላመነ ሰው አግኝቶ እጅ አንሳ እና መዳን አገኝታል ያለው የለም።

👉 ያመነ ሁሉ ወደ ጥምቀት እንጂ እጅ አላነሳም

ጥምቀት የመዳን አሠራር እንደሆነ

👉 ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቅት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፥ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፥ ለእግዚአብሔር የበጎ ሕሊና ልመና ነው እንጂ፥ ይህም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው፤
1ኛ ጴጥሮስ 3:21

ጥምቀት ክርስቶስን ሞትና ትንሳኤ ማጋራት ነው።

👉 እንግዲህ ምን እንላለን? ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት ጸንተን እንኑርን?: አይደለም። ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት አድርገን በእርሱ እንኖራለን? ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን?
ሮሜ 6:1_3

የእግዚአብሔር ቃል መስክሮ ያመነ ሰውን ሁሉ ወደ ጥምቀት ይወስዳሉ እንጂ እጅ አንሳ አላሉም በእኛ ቤት ሁሉ ከእግዚአብሔር ቃል ነው። አሜን 🙏

ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ!የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በዘማሪት ኢየሩሳሌም መዝገቡ የተዘጋጀውንና “እንደገና ታነሳለህ” የተሰኘውን የዝማሬ ሰንዱቅ ሲያቀርብ...
01/03/2026

ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ!

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በዘማሪት ኢየሩሳሌም መዝገቡ የተዘጋጀውንና “እንደገና ታነሳለህ” የተሰኘውን የዝማሬ ሰንዱቅ ሲያቀርብላችሁ በታላቅ ደስታ ነው።

የበጎ ስጦታ ፍጹምም በረከት ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር በቤተክርስቲያን በኩል ለራሱ ክብር እና ለቅዱሳን መታነጽ በሚሆኑ የዝማሬ ስጦታ እየባረከ ስላለ እናመሰግነዋለን። ዝማሬዎቹንም በታላቅ መስዋእትነት የሚያዘጋጁትንም ቅዱሳን እንባርካለን።

በዚህ አድካሚ የዝማሬ አልበም መዝሙሮቹን በመቀበል በስጦታ ለቤተክርስቲያን ያበረከተችውን እህት ኢየሩሳሌምን ጨምሮ በተለያየ መንገድ የተሳተፉትን ሁሉ የቤተክርስቲያን አምላክ ኢየሱስ በማያልቀው በረከት እንዲባርክ ጸሎታችንም ምኞታችንም ነው።

አልበሙ በቅርብ ቀናት ውስጥ በApostolic Songs መተግበሪያ ላይ ዝግጁ የሚሆን ሲሆን ቅዱሳን ሁሉ ዝማሬዎቹን በተለያዩ የግዢ አማራጮች በማውረድ ጸጋውን፣ ቤተክርስቲያንን እና አገልግሎቱን ትደግፉ ዘንድ በኢየሱስ ፍቅር እናስታውሳለን።

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን
ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል
የካቲት 2018 ዓ.ም

ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

                              “እግዚአብሔር  #ሙላቱ ሁሉ  #በእርሱ እንዲኖር፥ በእርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲ...
27/02/2026





“እግዚአብሔር #ሙላቱ ሁሉ #በእርሱ እንዲኖር፥ በእርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዶአልና።”
— ቆላስይስ 1፥19-20

አንዱ እግዚአብሔር ሙልአቱን ሁሉ በእርሱ አድርጓል

ይህ እርሱ የተባለው ማነው ከተባለ ፤ በሁለተኛው ምዕራፍ ቁጥር 9 ላይ 👉ሰውነት ይለዋል

“For it pleased the that in him should all fulness dwell;”
— Colossians 1:19 (KJV)

father means 👉አብ

him የተባለው 👉ወልድ or bodily

“For in him dwelleth all the fulness of the Godhead bodily.”
— Colossians 2:9 (KJV)።

መልካም እግዚአብሔር ሙልአቱን በሰውነቱ ሲያደርግ በዚህ ሰውነቱ ምን ምን አከናውኗል?

1ኛ.....በልጁ ሆኖ ተናግሮናል ዕብ 1፥1

ለዚህም የሚመሰክርልን ራሱ ኢየሱስ ሲሆን ፤ እንዲህ ይለናል

“የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል የላከኝ #የአብ ነው እንጂ #የእኔ አይደለም።”
— ዮሐንስ 14፥24

ዮሐንስ 14
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ እኔ #በአብ እንዳለሁ አብም #በእኔ እንዳለ አታምንምን? እኔ የምነግራችሁን #ቃል #ከራሴ አልናገረውም፤ ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል።

¹¹ እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ፤ ባይሆንስ ስለ ራሱ ስለ ሥራው እመኑኝ።

እሺ የስላሴ አማኞች በእናንተ ትንተና መሰረት ከሄድን ወልድ ራሱን ችሎ በራሱ #እውቀት #ፈቃድና $ስሜት የሚኖር የተለየ ማንነት ሲሆን አብም in Christ ሳይሆን out Christ ሆኖ ይኖራል የሚል ነው

ታድያ በራሱ ስሜት ፈቃድና እውቀት የሚኖር ሌላ እግዚአብሔር ከሆነ ከራሱ መናገር አለመቻሉ እርሱን ማን ያደርግልናል?

ሰው ብቻ ስለሆነ ነው ከራሱ ማይናገረው?

አዎን ካላችሁ =>>አምላክ ነው የሚለውን የመጽሀፍ ቅዱስን ምስክርነትን የት ልንሸሽገው እንችላለን? ፤

አይ ሌላ እግዚአብሔር ነው ግን አብ ያልሆነ እግዚአብሔር ካላችሁ ፤ እግዚአብሔር ከራሱ መናገር የማይችለው እንዴት ነው?

ሲቀጥል እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ የሚለው የኢየሱስ አስተምህሮት ፤ አብ ከክርስቶስ ውጪ እንዳለ ፤ ወልድም free of God እንደሆነ እመኑ የሚለው የእናንተን አስተምህሮት በምን በኩል አልፈው ሊገናኙ ነው?

2ኛ.....እግዚአብሔር አብ በልጁ (በሰውነቱ ተተረከ ታየ ) ዮሐ 1፥18

እግዚአብሔር አብ በክርስቶስ አልተገለጠም የሚለው የእናንተ አስተምህሮት ከየት የመጣ ነው?

3ኛ....እግዚአብሔር አብ በልጁ (በሰውነቱ) እኛን ከራሱ ጋር አስታረቀ ....2ኛ ቆሮ 5፥19

እግዚአብሔር አብ በሰውነቱ ሆኑ ከራሱ ጋር አላስታረቀንም የሚለውን የእናንተን ዶክትሪንን አምነን እንቀበለው ዘንድ ፤ 2ኛ ቆሮ 5፥19 ላይ የተጠቀሰው እግዚአብሔር የትኛው እግዚአብሔር እንደሆነ አስረዱን

4ኛ....እግዚአብሔር በልጁ (በሰውነቱ ) ከእኛ ጋር ሆነ

5ኛ....እግዚአብሔር በልጁ በሰውነትቱ በአለም ሁሉ ላይ በጽድቅ ይፈርድ ዘንድ ቀን ቀጥሮ በመጠባበቅ ላይ ነው ሐዋ 17÷31

በአጠቃ ላይ እግዚአብሔር በስጋ ሲገለጥ በተገለጠበት ሰውነቱ በኩል ከላይ የተጠቀሱትን ለማድረግ ወድዷል

=>> በዮሐ 1፥18 ገለጻ መሰረት ፦ እግዚአብሔር የታየው የተተረከው በልጁ {በሰውነቱ) ነው

=>> በዕብ 1፥1 ገለጻ መሰረት ፦ እግዚአብሔር ቀጥታ የተናገረን በልጁ (በሰውነቱ ) ነው

=>> በ2ኛ ቆሮ 5፥19 ገለጻ መሰረት ፦ እግዚአብሔር አለምን ከራሱ ጋር ያስታረቀው በልጁ (በሰውነቱ) ነው

=>> በቆላ 1፥19 ገለጻ መሰረት ፦እግዚአብሔር ሙልአቱን ሁሉ በልጁ (በሰውነቱ) አድርጓል

=>> በማቲ 1፥23 ገለጻ መሰረት ፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሆነ ተጸንሶ በተወለደው በልጁ (በሰውነቱ ) ነው

=>> በቆላ 1፥9 ገለጻ መሰረት ፦ የመለኮት ሙልአት በልጁ (በሰውነቱ ) ተገልጦ ይኖራል

=>> በሐዋ 17፥31 ገለጻ መሰረት ፦ እግዚአብሔር የሚፈርደው በልጁ (በሰውነቱ) ነው

የስላሴ አማኞች ኢየሱስ ከአብ በተለየ ማንነቱ ራሱን ችሎ አምላክ በመሆኑ ምክንያት ፤ ከላይ የተዘረዘሩት ነጥቦች እንዴ ይስማሙታል?

እንግዲህ አብ ሚባል እግዚአብሔር አላችሁ ፤ ወልድ ሚባልም አግዚአብሄርም አላችሁ

መልካም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ የሚለው የማቲ 1፥23ን ጥቅስ አንብቡና የቱ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆኖ የቱ እግዚአብሔር ከእኛ እንደራቀ አስረዳን.........?

👉ዕብ 1፥1ን አንብቡና የቱ እግዚአብሔር በየቱ እግዚአብሔር እንደተናገረ ንገሩኝ

👉2ኛ ቆሮ 5፥19ን አንብቡና ፦ የቱ እግዚአብሔር ታራቂ ፦ የቱ እግዚአብሔር አስታራቂ እንደሆነ ንገሩኝ

👉ኢሳ 59፥16ንአንብቡና የቱ እግዚአብሔር አማላጅ ሰውን በማጣቱ ምክንያት እንዳዘነ እንደተከፋ አስረዱን

👉ኢሳ 9፥6ን አንብቡና የሚወለደው ህጻን ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ አለቅነቱ በዳዊት ዙፋን ላይ ይበዛል የተባለውን ማንነት ንገሩኝ

ማነው ህጻኑ?

ዮሐ 1፥14 በመሰከረልን የእውነት ቃል መሰረት ቃል ስጋ ሆኖ በመጸነስ፦ በሮሜ 1፥3 መሰረት በኃይል የእግዚአብሄር ልጅ ሆኖ በመወለዱ ምክንያት ፦ ስለ እናንተ ከእግዚአብሄር ዘንድ የተገለጠ #ሰው ነበር ብሎ ሐዋ 2፥22 በዘገበልን መሰረት ህጻን የተባለው ሰውነቱ ነው?

ወይንስ መጽሀፍ ቅዱሳዊ ባልሆነው በእናንተ አስተምህሮት መሰረት the 2nd personal god ነው ህጻኑ??

👉ዮሐ 16ን አንብቡና ከአብ ወጥቼ እንደመጣሁ ሲባል ፤ ስለ ምኑ እየመሰከረ እንደሆነ አስረዱኝ

ከአብ ወጥቼ ሲል ሙሉ እግዚአብሔር ከሙሉ እግዚአብሔር ውስጥ መውጣቱን ያሳያል ወይንስ ሙሉ አምላክ ከሙሉ አምላክ ውስጥ መውጣቱን ያሳያል?

👉ኢሳ 43፥10ን አንብቡና ከእኔ በፊት አምላክ የለም ፤ ከበኃላዬም አይኖርም ያለውን ማንነት ንገሩኝ

አባትየው እግዚአብሔር ነው ይህንን ቃል ተናጋሪ? ወይስ ልጅየው እግዚአብሔር ነው በተለየ አካሉ የተናገረው?

አባትየው ነው ካላችሁ ፤ ከበኃላዬ አምላክ የለም ብሎ ሲናገር እየዋሸ ነው? ወይንስ ምን ምክንያት ቢኖረው ነው?

ልጅየው ነው እንዲህ ያለው ካላችሁ ደግሞ ፤ ልጅየው የአባትየውን አምላክነት ቀምቶት ነው ከበፊቴ አምላክ አልነበረም ፤ በኃላዬም አይኖርም ያለው??

👉ዘዳ 32፥39ን አንብቡና እኔ ብቻዬን ነኝ ተመልከቱ ብሎ የተናገረውን ማንነት ለይልን

ማነው ብቻውን እንዳለ ምስክርነትን የሰጠው? አባትየው እግዚአብሔር? ወይስ ልጅዬው እግዚአብሔር?

👉1ኛ ቆሮ 8፥4 ን አንብቡና ፦ ከአንዱ በቀር አምላክ እንደሌለ እናውቃለን ሲል ፤ ይህ አንዱ አምላክ ማን እንደሆነ ለይታችሁ ንገሩኝ

አባትየው እግዚአብሔር ነው? ወይንስ ልጅየው እግዚአብሔር ነው አንዱ ተብሎ በነጠላ ቁጥር የተገለጸው?

ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

25/02/2026

በ England የነበረ ቆይታ

 ?👇👇👇👇"ቀኝ" (Right hand/side) የሚለው ቃል  መጻሕፍት ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሔርን ሉዓላዊነት (Sovereignty)፣ ጽድቅ (Justice)፣ እና የማይለወጥ ፍቅር (Unfail...
25/02/2026

?👇👇👇👇
"ቀኝ" (Right hand/side) የሚለው ቃል መጻሕፍት ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሔርን ሉዓላዊነት (Sovereignty)፣ ጽድቅ (Justice)፣ እና የማይለወጥ ፍቅር (Unfailing Love) የሚወክል ታላቅ መንፈሳዊ መግለጫ ነው።

#​1. (The Symbol of Power and Victory)
​የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ መለኮታዊ ኃይሉንና ድል አድራጊነቱን የሚገልጽበት ዋና መንገድ ነው።

👉​ዘጸአት 15፥6
"አቤቱ፥ ቀኝህ በኃይል ከበረች፤ አቤቱ፥ ቀኝህ ጠላትን ቀጠቀጠች።"
👉​መዝሙር 118፥16
"የእግዚአብሔር ቀኝ ከፍ ከፍ አደረገችኝ፤ የእግዚአብሔር ቀኝ ኃይልን አደረገች።"

#​2. (The Place of Exaltation and Authority)
​ይህ ጥቅስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ ያለውን ፍጹም መለኮታዊ ሥልጣንና ክብር ያሳያል።

👉​መዝሙር 110፥1
"እግዚአብሔር ጌታዬን፦ ጠላቶችህን ለእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው።"
👉​ዕብራውያን 10፥12
"እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ።"

#​3. (The Promise of Support and Protection)
​እግዚአብሔር ለአማኞች ያለውን ቅርበትና የማይናወጥ ረዳትነት የሚገልጥባቸው ጥቅሶች ናቸው።

👉​ኢሳይያስ 41፥10
"እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ እጅ ደግፌ እይዝሃለሁ።"
👉​መዝሙር 16፥8
"ሁልጊዜ እግዚአብሔርን በፊቴ አየዋለሁ፤ በቀኜ ነውና አልታወክም።"

​4. (The Sign of Favor and Judgment)
​በመጨረሻው ዘመን የሚሆነውን የመለያየትና የክብር ርስት መቀበልን ያመለክታል።

👉​ማቴዎስ 25፥33-34
"በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል። በዚያን ጊዜ ንጉሡ በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።"

#​5. (The Source of Eternal Joy)
​በእግዚአብሔር ቀኝ መገኘት የሚገኘውን መንፈሳዊ እርካታ ይገልጻል።

👉​መዝሙር 16፥11
"የሕይወትን መንገድ ታሳየኛለህ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን አጥግባለሁ፥ በቀኝህም የዘላለም ፍሥሐ አለ።"

ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

YouTube link=https://www.youtube.com/

✍️ ኢየሱስ ክርስቶስን በአንድ ወገን ልጅ ብቻ (እንደ ልጅነት ብቻ) መገደብ የማንነቱን ሙሉነት መረዳት እንደማይቻል ነው። ​ ✍️ የነቢያት ምስክርነት፡ ኢየሱስ የዘላለም አባት ነው​ነቢያት ...
24/02/2026

✍️ ኢየሱስ ክርስቶስን በአንድ ወገን ልጅ ብቻ (እንደ ልጅነት ብቻ) መገደብ የማንነቱን ሙሉነት መረዳት እንደማይቻል ነው።


​ ✍️ የነቢያት ምስክርነት፡ ኢየሱስ የዘላለም አባት ነው
​ነቢያት ስለ መሲሑ ሲተነብዩ የአምላክነቱን ሙሉነትና የአባትነት ማንነቱን ጭምር በግልጽ አስቀምጠዋል።

✍️​ኢሳይያስ 9:6፦ "ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና... ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።"

✍️​እዚህ ጋር ነቢዩ ኢሳይያስ የሚወለደው ሕፃን (ወንድ ልጅ) በተመሳሳይ ሰዓት "የዘላለም አባት" መሆኑን ይናገራል።

ይህም ኢየሱስ በሥጋ ሰውነት ልጅ ቢሆንም፣ በመለኮታዊ ማንነቱ ግን የፍጥረት ሁሉ ምንጭና አባት (አብ) መሆኑን ያረጋግጣል።

​📌 የሐዋርያት ምስክርነት፡ ልጅም አባትም ኢየሱስ "

​ሐዋርያት ኢየሱስን "የእግዚአብሔር ልጅ" ብለው ሲጠሩት መለኮትነቱንና በሥጋ መገለጡን ለመግለጽ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ደግሞ አምላክነቱንና አባትነቱን አጽንተውታል።

✍️​የሐዋርያው ጴጥሮስ ምስክርነት፦ ጴጥሮስ በማቴዎስ 16:16 ላይ "አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ" ብሏል። ነገር ግን በ1 ጴጥሮስ 1:17 ላይ ደግሞ ያለ ፊት አይቶ የሚፈርደውን "አባት" ብላችሁ ብትጠሩት በማለት ኢየሱስን እንደ ፈራጅና እንደ አባት ይገልጸዋል።

✍️​የሐዋርያው ቶማስ ምስክርነት፦ ቶማስ ከትንሣኤ በኋላ ኢየሱስን ሲያየው "ጌታዬና አምላኬ" (ዮሐንስ 20:28) በማለት አምላክነቱን መስክሯል።

​እኔና አብ አንድ ነን"
​ኢየሱስ ራሱ ስለ ማንነቱ ሲናገር የአባትነትና የልጅነት ሚስጥር በአንድነቱ ውስጥ እንዳለ ገልጿል፦
​"እኔን ያየ አብን አይቶአል፤ እንዴትስ፦ አብን አሳየን ትላለህ?" (ዮሐንስ 14:9)

​ይህ ቃል ኢየሱስ ከአብ የተለየ ሌላ አካል ሳይሆን፣ የማይታየው አባት በሥጋ የተገለጠበት ማንነት መሆኑን ያሳያል።

​እንደ ሰው (በሥጋ)፦ ልጅ ይባላል።
​እንደ አምላክ (በመንፈስ)፦ አባት ይባላል።

​ በሰይጣን እና በቅዱሳን እውቀት መካከል ያለው ልዩነት
​ጽንሰ ሐሳብህን አጠናክረን ስናየው፦ ሰይጣን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ብቻ ብሎ ያቆማል " ሐዋርያት ወይም ቅዱሳን የዘላለም አባት ነው ብለው ያምናሉ።

✍️​ኢየሱስን "ልጅ ብቻ ነው" ብሎ መገደብ፣ እርሱ ራሱ "እኔና አብ አንድ ነን" (ዮሐንስ 10:30) በማለት የገለጠውን ታላቅ ምስጢር አለመረዳት ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው፣ እግዚአብሔር አንድ ነው፤ እርሱም በሥጋ ተገልጦ ዓለምን ከራሱ ጋር አስታርቋል።

ስለዚህ ኢየሱስን እንደ ልጅነቱ ቤዛችን፣ እንደ አባትነቱ ደግሞ ፈጣሪያችንና አምላካችን አድርገን ማወቅ የሐዋርያት ትክክለኛ እውቀት ነው።

share ይደረግ 🙏

ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

YouTube link=https://www.youtube.com/

እውነተኛ አምላክ" (The True God)​በዮሐንስ 17:3 ላይ ኢየሱስ "እውነተኛ አምላክ የሆንህ አንተን..." ብሎ መጸለዩ፣ አብን ከእርሱ ለመለየት ሳይሆን፣ በምድር ላይ ያለውን የሰውነት...
22/02/2026

እውነተኛ አምላክ" (The True God)
​በዮሐንስ 17:3 ላይ ኢየሱስ "እውነተኛ አምላክ የሆንህ አንተን..." ብሎ መጸለዩ፣ አብን ከእርሱ ለመለየት ሳይሆን፣ በምድር ላይ ያለውን የሰውነት (የወልድነት) ሚና ለማሳየት ነው።

ነገር ግን ሐዋርያው ዮሐንስ በመጀመሪያው መልእክቱ ላይ እንዲህ በማለት ደምድሞታል፦
​1 ዮሐንስ 5፥20፦ "...እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።"
​English: "He [Jesus Christ] is the true God and eternal life."
​ማጠቃለያ ሐሳብ
​ኢየሱስን ከአብ ለይቶ "አብ አይደለም" የሚል ሰው፣ "እውነተኛ አምላክ" የሚለውን ስም ለኢየሱስ መስጠት ይከብደዋል። ምክንያቱም ከአብ ውጭ ሌላ እውነተኛ አምላክ የለም። ኢየሱስ እውነተኛ አምላክ ከሆነ ደግሞ፣ እርሱ ራሱ ያ የተገለጠው አብ መሆኑን መቀበል የግድ ይሆናል።

​ፊልጶስም የተረዳው ይህንን ነው፦ አብን በሰማይ ርቆ የሚኖር ሌላ አምላክ አድርጎ ሲጠብቅ፣ አብ ግን በእርሱ ፊት ቆሞ "አይታችሁትማል" አለው።........ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው ማርቆስ 12÷ 29...... አንድ ተስፋ .... አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለን ,,,,, ኤፍሶን 4÷4
!
ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

YouTube link=https://www.youtube.com/

ትንቢት ተነግሮ ተጽፎ እያለ በእርሱ መሰናክል ...።እግዚአብሔር መስተዋል ካልሰጠ ሰዎች አያስተውሉም በሥጋ ከመገለጡ በፊት የተናገረው እግዚአብሔር የራሱን አመጣጥ እንደዚህ በማለት ተናገራቸው...
20/02/2026

ትንቢት ተነግሮ ተጽፎ እያለ በእርሱ መሰናክል ...።

እግዚአብሔር መስተዋል ካልሰጠ ሰዎች አያስተውሉም በሥጋ ከመገለጡ በፊት የተናገረው እግዚአብሔር የራሱን አመጣጥ እንደዚህ በማለት ተናገራቸው።

👉አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል።
ዘካርያስ 9:9

ማነው ይህ ትሑት ሆኖ በአህያም በአህያይቱ ግልግል በውርጫይቱ ተቀምጦ የምመጣ ? ያ የ እሥራኤል አምላክ ንጉሣችን አዳኝ ነው ፈጣሪም ነው በ አህያይቱ ግልግል ላይ ተቀምጦ እንደሚመጣ ተነግሮናል እኛ አስተውለን አብዛኞቹ ማስተዋል ካለማደረግ በእርሱ ተሰናከሉ።

በ ነቢይ የተጻፈ ትንቢት ማስፈፀሚያ ግዜ ስድርስ እንዲህ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው :-

👉 እንዲህም አላቸው፦ “በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፥ በዚያን ጊዜም የታሰረችን አህያ ውርንጫም ከእርስዋ ጋር ታገኛላችሁ፤ ፈትታችሁ አምጡልኝ። ማንም አንዳች ቢላችሁ፦ ለጌታ ያስፈልጉታል፡ በሉ፤ ወዲያውም ይሰዳቸዋል።” “ለጽዮን ልጅ፦ ‘እነሆ፥ ንጉሥሽ የዋህ ሆኖ በአህያ ላይና በአህያይቱ ግልገል በውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል፡’ በሉአት፡” ተብሎ በነቢይ የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ።
ማቴዎስ 21:1_5

ለእኔ መሰናክል ስላልሆነ ንጉሤን አመሰግናለሁ 🙌🙏
በእርሱ ያልተሰናከላችሁ ሁለተኛ አካል ነው 1/2 ንጉሥ ነው ያላሉ ያመስግኑ።

አብዛኞቹ በእርሱ ተሰናከሉ እባካችሁ አትሰናከሉ እድል ያላችሁ
ግዜ ሳይበቃ ሰማይ ተቃጥሎ ሳያልፍ ምህረቱ ሳያልቅ በእርሱ በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻው አምላክ የሚሆነው በማመን በስሙ ተጠምቃችሁ የሰማያዊ ዘር በዳግመኛ ልደት ሁኑ።
እኛ በሸክም ወንጌልን እንሰብካለን አንድም ሰው በእሳት እንድቃጠል የኢየሱስ ክርስቶስ ፍላጎት አይደለም ዛሬም በ ትኩስ ደሙ ይጠራቸዋል።
#አሜን
ይሄን page ከምከታተሉት 90% Non followers ናችሁ እባካችሁ follow አድርጉ🙏 ብዙ ትማራላችሁ
ኢየሱስ ይባርካችሁ

ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

YouTube link=https://www.youtube.com/

Address

Areka
S**o
AREKA

Telephone

+251904828140

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Apostolic generation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share