DNTakele Yemaryam

DNTakele Yemaryam https://youtube.com/?feature=shared
ቤተሰብ ይሁኑ🙏
(1)

‹‹ግንቦት 23››"ጰራቅሊጦስ" የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት አንዱ ነው።"ጲራቅሊጦስ"ማለት በልሳነ ጽርዕ “መጸናንዒ” ማለት ነው። ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪ...
31/05/2026

‹‹ግንቦት 23››"ጰራቅሊጦስ" የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት አንዱ ነው።

"ጲራቅሊጦስ"ማለት በልሳነ ጽርዕ “መጸናንዒ” ማለት ነው። ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ ናዛዚ (የሚናዝዝ)፣ መጽንዒ (የሚያጸና)፣ መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው፡፡

ከሦስቱ አካላት አንዱ ለሆነው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስም ነው፡፡

በዓለ ጰራቅሊጦስ ‘በዓለ ጰንጠቆስጤም’ እየተባለ ይጠራል፡፡ ይኸውም በግሪክ ቋንቋ ‘በዓለ ኀምሳ፣ የፋሲካ ኀምሳኛ ዕለት፣ በዓለ ሠዊት (የእሸት፣የመከር በዓል’) ማለት ነው፡፡

በዓለ ጰራቅሊጦስ ወይም በዓለ ጰንጠቆስጤ ከዘጠኙ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዐበይት በዓላት አንዱ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደበትን ቀን የምናስብበት በዓል ነው።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ፲፪ቱ ደቀ መዛሙርት፣ ፸፪ቱ አርድእት፣ ፭፻ው ባልንጀሮችና ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት በኢየሩሳሌም ከተማ በአንድነት ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር፡፡

በሚያርግበት ጊዜም “እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ” ሲል ለሐዋርያቱ በገባላቸው ቃል መሠረት ባረገ በ፲ኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል፡፡ (ሉቃ.፳፬፥፵፱)

በሐዋርያት ሥራ እንደ ተጻፈው በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማለዳ ሁሉም በአንድ ቦታ ተሰብስበው ሳሉ እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ መጥቶ የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ በመቀጠልም እንደ እሳት የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በሁሉም ላይ ሞላባቸው፡፡

በዚህ ጊዜ ሁላቸውም መንፈስ ቅዱስን ከተሞሉ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በየአገሩ ቋንቋዎች ሁሉ መናገር ጀመሩ፡፡ (ሐዋ.፪፥፩-፬) ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ በዓል ጰራቅሊጦስ ይባላል፡፡

የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነት፣ የቅድስት ድንግል ማርያም እና የቅዱሳን ሐዋርያት አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን አሜን 🙏

Big shout-out to my newest top fans! Werkitu Birku, ጌርሳም ጌርሳም, Abrehet Hagos, Gosa Tesa, Genet Genet, Make T Zalaqa, Mel...
30/05/2026

Big shout-out to my newest top fans! Werkitu Birku, ጌርሳም ጌርሳም, Abrehet Hagos, Gosa Tesa, Genet Genet, Make T Zalaqa, Melesech Fekadu, ሮማን አያሌው, Adisu Lende, Sadik Sulxi, Makdes Gaaddisa, Beneyam Tsegaye, Tsehay Mlualem Werkineh, ዘላለምካሳሁን ፌላቴ, Rigbey Berhanu, Sabi Abrham, Mane Mane, Meseret Gululat, Aregash Getu Aregash Getu, Emebet Endashaw, Balayanesh Masefen Kebede, Serawit Woldesenbet, Ase Dula, Belayneh Taye, Aynalem Bafa, Mastewal Bayines, Eyerus Asfaw, Girum Fitsum Fanos, Tariku Beyene, Ab Gb, Derge Bna, Mulugeta Dejene, Baryaw Tatek Nehene, Sami Rasta

‎ ❗‎ኑ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን፤ ለአምላክ ለመድኃኒታችን እልል እንበል።(መዝ 94:1)(95:1)‎"በካዎ ኮይሻ ወረዳ ቤተ ክህነት ላሾ ደብረ ታቦር ባለወልድ ቤተክርስቲያ ወጣቶች በጎ አ...
30/05/2026

‎ ❗

‎ኑ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን፤ ለአምላክ ለመድኃኒታችን እልል እንበል።(መዝ 94:1)(95:1)
‎"በካዎ ኮይሻ ወረዳ ቤተ ክህነት ላሾ ደብረ ታቦር ባለወልድ ቤተክርስቲያ ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበረ 1ኛ_ዓመት የምስረታ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ! ይህ ታላቅ መንፈሳዊ ጥምረት ከቀድሞ ሰንበት ት/ቤት አባላት ጀምሮ ለብዙ ዓመታት ወጣቶችን በሥነ-ምግባርና በሃይማኖት ኮትኩቶ ያሳደገበትን ዕለት ማሰብ ትልቅ በረከት ነው።

‎ ሕፃኑን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።" (ምሳሌ 22:6)
‎የሁላችን ተተኪ ትውልድ መፍለቂያ፣ የቅድስና እና የዕውቀት አውድማ የሆነው ላሾ ደብረ ታቦር ባለወልድ ቤተክርስቲያን ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር 1ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ለመደረስ 7 ቀን ብቻ ቀርቷል።
‎እነዚህ 1 ዓመታት ቀላል አልነበሩም፤ የስንት አባቶች ድካም፣ የስንት ወጣቶች ትጋትና የቅዱሳን ጥበቃ የተገለጠበት ታላቅ ጉዞ ነው። ስንቱ ወጣት ከዓለም ወጥመድ አምልጦ የክርስቶስ ምስክር የሆኑበት፣ ስንቱ መዝሙርና ቅኔ ተምሮ መቅደሱን ያደመቀበት
‎ዛሬም እኛ ታደልንና በዚህ ታላቅ ታሪክ ውስጥ ፍሬ ሆነን ለመቆም በቃን። ይህ በዓል ያለፈውን የምስጋና፣ የዛሬውን የአንድነት፣ የነገውን ደግሞ የበለጠ የሥራ ትጋት የምናድስበት ልዩ ቀን ነው።
‎ የእግዚአብሔር ጥበቃ፣ እስከ ዘላለም ይኑርበት ።
‎ለሶስት ቀናት የሚቆይ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤው ላይ ታላላቅ የቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት እና የተዋሕዶ ዘማርያን ይገኛሉ። እርሶም መጥተው በረከት እንዲካፈሉ በክብር ተጠርተዋል! ስለተዘጋጀ ሁላችሁም በእግዚአብሔር ስም ተጋብዛችኋል።

‎ግንቦት 28-30/ 2018 ዓ/ም
ካዎ ኮይሻ ወረዳ ቤተክህነት ላሾ ደብረ ታቦር ባለወልድ ቤተክርስቲያን እንገናኝ።
‎ 🤲🤲 በሰላም ያድርሰን🤲

ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስትያን ሃዋሳ🙏♥⛪💖
30/05/2026

ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስትያን ሃዋሳ🙏♥⛪💖

ዛሬ ቤዛዊተ ዓለም ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓሏ ነው በእናትነቷ በአማላጅነቷ ትጎብኘን አሜን🙏♥⛪💖
29/05/2026

ዛሬ ቤዛዊተ ዓለም ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓሏ ነው
በእናትነቷ በአማላጅነቷ
ትጎብኘን
አሜን
🙏♥⛪💖

የወላይታ ሀገረ ስብከት የካህናት ማሰልጠኛ 2018 ዓመት ትምህርት ማስጀመሪያ መርሐግብር በምስል
28/05/2026

የወላይታ ሀገረ ስብከት የካህናት ማሰልጠኛ 2018 ዓመት ትምህርት ማስጀመሪያ መርሐግብር በምስል

28/05/2026

Big shout-out to my newest top fans! Werkitu Birku, ጌርሳም ጌርሳም, Abrehet Hagos, Gosa Tesa, Genet Genet, Make T Zalaqa, Melesech Fekadu, ሮማን አያሌው, Adisu Lende, Sadik Sulxi, Makdes Gaaddisa, Beneyam Tsegaye, Tsehay Mlualem Werkineh, ዘላለምካሳሁን ፌላቴ, Rigbey Berhanu, Sabi Abrham, Mane Mane, Meseret Gululat, Aregash Getu Aregash Getu, Emebet Endashaw, Balayanesh Masefen Kebede, Serawit Woldesenbet, Ase Dula, Belayneh Taye, Aynalem Bafa, Mastewal Bayines, Eyerus Asfaw, Girum Fitsum Fanos, Tariku Beyene, Ab Gb, Mulugeta Dejene, Baryaw Tatek Nehene, Sami Rasta

19 አብሳሪው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል🪽ደስ እምትሰኙበትን ዜና ያብስራችሁ🤲⛪♥
27/05/2026

19 አብሳሪው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል🪽
ደስ እምትሰኙበትን ዜና ያብስራችሁ🤲⛪♥

አድርገኸልኛልና ለዘላለም ክበርልኝአምላከ ቅዱሳን🙏🌹🌹🙏   💖💖💖
23/05/2026

አድርገኸልኛልና ለዘላለም ክበርልኝ
አምላከ ቅዱሳን
🙏🌹🌹🙏
💖💖💖

ዕርገተ ክርስቶስ“አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ”                  /መዝ ፵፮ ፥ ፭/።   እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ አደረሳችሁ !!! የጌታችን አምላካችን መድ...
21/05/2026

ዕርገተ ክርስቶስ

“አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ”
/መዝ ፵፮ ፥ ፭/።
እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ አደረሳችሁ !!!

የጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ በተከበረ በዐርባኛው ቀን የሚውለው ዐቢይ በዓል “ዕርገት” ይባላል፡፡ ዕርገት ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ዐበይት በዓላት አንዱ ነው፡፡
ጌታችን ከትንሣኤው በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያት ለአርባ ቀናት እየተገለጸ፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት መጽሐፈ ኪዳንን፣ ትርጓሜ መጻሕፍትን፣ ምሥጢራትን፣ ሕግጋትንና ቀኖናተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተምር ቆይቶ ወደ ቀደመ ዙፋኑ ወደ ሰማይ በክብር በምስጋና ማረጉን በደስታ የምንዘክርበት ዐቢይ በዓል ነው፡፡

Address

Sodo

Telephone

+251919404792

Website

http://tiktok.com/@take132116, https://t.me/takezw1321ttt, https://youtub

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DNTakele Yemaryam posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to DNTakele Yemaryam:

Share