የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ

የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ድምፅ!
በዚህ ፔጅ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፣ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ የቤ/ያን መረጃዎችን፣ስብከቶችንና መዝሙሮችን ያገኛሉ!!
👉ቤተሰብ ይሁኑ🙏 spritual news

20/05/2026

ተክለሐይማኖት ባህታዊ

Following  እንኳን ለጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ወቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን
19/05/2026

Following

እንኳን ለጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ወቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን

 #ሸር በማድረግ ለክርስቲያን ወገኖችና ለአንዳንድ መልካም ሰዎች አድርሱልን !!!ይህች ከታች በፎቶ የሚትመለከቷት ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በወላይታ ሀገረ ስ...
19/05/2026

#ሸር በማድረግ ለክርስቲያን ወገኖችና ለአንዳንድ መልካም ሰዎች አድርሱልን !!!

ይህች ከታች በፎቶ የሚትመለከቷት ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በወላይታ ሀገረ ስብከት ካዎ ኮይሻ ወረዳ ቤተክህነት ውስጥ በደሳሳ ጎጆ የነበረችው ኮይሻ ዋሙራ ሳጋዶራ በዓታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ስትሆን ዛሬ ግን በእግዚአብሔር ቸርነትና በእናንተ ደጋግ ሰወች እርዳታ ህንፃ ቤ/ያኑ እዝህ ደረጃ ላይ መድረስ ችሏል።
ከዚህ በፍት በተለያዩ ሚዲያ ስንለምን የነበረው ሳጋዶራ በዓታ ማርያም ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ፍቃድ በእናንተ ፀሎትና እርዳታ እየሰራን እያለ አንድ ትሁት ሰው እስከ ያለው ስራ እኔ እጨርሳለሁ (እፈጽማለሁ) በማለት ቃል ገብቶ እያሰራ ይገኛል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አሁን ግን ምንም አይነት ንዋዬ ቅዱሳት ስለሌለ አሁንም መልካም ስራችሁን እንድትቀጥሉ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን ።
↙️ለበለጠ መረጃ
🔹 0915536425
🔹 0916141439
↙️ድጋፍ ለማድረግ
EBC፦ 1000707796026
ሳጋዶራ በዓታ ማርያም ይላል።
🙏💖⛪

Following ወደ ጌታህ ደስታ ግባ!" (ማቴ. ፳፭፡፳፩)እሱም ወደ አባቶቹ ተሰበሰበየሊቀ ዲያቆን በላይ ባራና 12ኛው ቀን መታሰቢያ በታላቁ ገዳማችን በርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ መንክ...
18/05/2026

Following
ወደ ጌታህ ደስታ ግባ!" (ማቴ. ፳፭፡፳፩)
እሱም ወደ አባቶቹ ተሰበሰበ
የሊቀ ዲያቆን በላይ ባራና 12ኛው ቀን መታሰቢያ በታላቁ ገዳማችን በርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ መንክራት አቡነ ተክለሃይማኖት አድነት ገዳም አባቶች ገዳማዊያን፣ ገዳማዊያን እናቶች የገዳሙ ሕብረተሰብ በአጠቃላይ በተገኙበት የ12ኛው ቀን መታሰቢያ ስለሚደረግ እርስዎም በቦታው ተገኝቶ ለወንድማችን እንዲጸልዩ በታላቁ ገዳማችን ስም ጋብዘናችዋል!
ከኮሚቴዎች
ምስጋና
ከዕለተ ዕረፍቱ ጀምሮ
✅በርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደ/መ/አ/ተ/ሃ/አ/ገዳም
✅ደብረ ሊባኖስ ገዳም
✅ቦሮዳ ገዳመ ዮርዳኖስ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም
✅ሆምባ ቅዱስ በዓለወልድ ገዳም
✅አጠቃላይ በርዕሰ ከተማው ያሉት ገዳማትና አድባራት
እስከአሁን የኃይለ ጊዮርጊስን ነፍስ እንዲምርልን በቅዳሴያችሁ ፣በጸሎታችሁ እያወሳችሁ ስለሆነ ከልብ እናመሰግናለን።
ለወደፊትም ሳይቋረጥ በቅዳሴው፣በሰዓታቱ፣በጸሎቱ እንዲታሰቡ እንማፀናለን!
የኃይለ ጊዮርጊስን ነፍስ በተከፈተ ገነት በተነጸፈ ዕረፍት ያሳርፍል!

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በጊራራ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እየታነጸ ለሚገኘው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ማስፈጸሚ የገቢ ማሰባሰቢያ መ...
17/05/2026

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በጊራራ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እየታነጸ ለሚገኘው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ማስፈጸሚ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት አባታዊ ቡራኬ እና ቃለ ምዕዳን ከመስጠት ጋር የገንዘብ ስጦታ አበረከቱ፡፡
+++++++
ሚያዚያ ፳፭/፳፻፲፰ ዓ.ም
እጨጌ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በወላይታ ሀገረ ስብከት በዳሞት ወይዴ ወረዳ ቤተ ክህነት የጊራራ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እያስገነባ ለፍጻሜ ለደረሰው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ማስፈጸሚያ የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት፥ ግንቦት 09 ቀን 2018 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በተገኙበት ተከናውኗል።

በዚህም መርሐ ግብሩም ላይ ከብፁዕነታቸው በተጨማሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ቦኪቻ ኤንጋ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ፣ የወረዳ ቤተ ክህነቱ የሥራ ሓላፊዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ መምህራን እና በርካታ ምዕመናን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የዛሬውንም የገቢ ማሰባሰብ መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የተለመደ የገንዘብ ስጦታ በማበርከት ያስጀመሩ ሲሆን በመልዕክታቸውም ይህን ለፍጻሜ የበቃውን ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ ለሙሉ ለፍጻሜ ለማብቃት የሁሉም አካላት ርብርብ የሚያስፈልግ በመሆኑ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም የጠዋቱ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብሩ በብፁዕነታቸው ጸሎት እና ቡራኬ ተጠቅቋል።
++++++++
ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ከቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተመልሰው በዛሬው ዕለት  በድንገት ከዚህ ዓለም በሥጋ የተለየ የሊቀ ዲያቆን በ...
17/05/2026

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ከቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተመልሰው በዛሬው ዕለት በድንገት ከዚህ ዓለም በሥጋ የተለየ የሊቀ ዲያቆን በላይ ባራና ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ተገኝተው ጸሎት በማድረግ እና አባታዊ ምክር በመስጠት አጽናኑ።

የብፁዕነታቸው ቡራኬ ይደርብን!

ዓ.ም

ሰላም ለኪ ቅድስት  ቤተክርስቲያን አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት🙏በወላይታ ሀ/ስብከት ካዎ ኮይሻ ወረዳ ቤተክህነት ጫውካሬ ደብረ ሲና ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስትያንለደጁ ያብቃችሁ🙏💖⛪
16/05/2026

ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተክርስቲያን አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት🙏

በወላይታ ሀ/ስብከት ካዎ ኮይሻ ወረዳ ቤተክህነት ጫውካሬ ደብረ ሲና ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስትያን
ለደጁ ያብቃችሁ🙏💖⛪

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  የሰሜን ካሊፎርኒያ  ኔቫዳ አሪዞና ሀገረ ስብከት ከቤተክርስቲያን መዋቅራዊ አሠራር ውጪ  የተፈጸመ ሕገ ወጥ እና ኢቀኖናዊ ድርጊትን አስመልክቶ የ...
15/05/2026

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ካሊፎርኒያ ኔቫዳ አሪዞና ሀገረ ስብከት ከቤተክርስቲያን መዋቅራዊ አሠራር ውጪ የተፈጸመ ሕገ ወጥ እና ኢቀኖናዊ ድርጊትን አስመልክቶ የተላለፈ መልዕክት ።

የቅዱስ ፓትርያርኩ እና የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የፕሮጀክት ጉብኝት  በፎቶ።ፎቶ አዳነ ሲሳይ🙏⛪💖
14/05/2026

የቅዱስ ፓትርያርኩ እና የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የፕሮጀክት ጉብኝት በፎቶ።

ፎቶ አዳነ ሲሳይ
🙏⛪💖

ሰበር ዜና Kune Demelash kassaye -Arba Minch   ተፈቷል። ቤተክርስቲያን እንኳን ደስ አለሽ።ያለ ዋጋ ለገጠሪቱ ቤተክርስቲያን የሚደክመው ትጉኁ ወጣት ተፈቷል።አጽራረ ቤተክር...
14/05/2026

ሰበር ዜና
Kune Demelash kassaye -Arba Minch ተፈቷል። ቤተክርስቲያን እንኳን ደስ አለሽ።

ያለ ዋጋ ለገጠሪቱ ቤተክርስቲያን የሚደክመው ትጉኁ ወጣት ተፈቷል።
አጽራረ ቤተክርስቲያን በቤተክርስቲያን ላይ የሚያርጉትን የስም ማጥፋት ዘመቻ ግምባር ቀደም ሆኖ የሚመክተው የዘመኑ ድንቅ ወጣት ተፈቷል።
የወጣትነት ጉልበቱን በተለይ ለገጠሪቱ ቤተክርስቲያን የሰጠው ፣ የተዘጉትን አብያተክርስቲያናት የሚያስከፈተው ፣ የጉደሉ ንዋያተ ቅዱሳትን ፈጥኖ የሚያሟላው ፣ በዝናብና በጭቃ በሞተር እየተጓዘ መብዓ ለቤተክርስቲያን የሚያድለው መንፈሳዊ አርበኛ ተፈቷል ።
ስብከተ ወንጌልን ፣አብነት ት/ቤትን ፣ሰንበት ት/ቤትን ለማጠናከር ራዕይ ሰንቆ ማኅበር መሥርቶ ደፋ ቀና እያለ ያለው ወጣት በተለይ ክብር ርዕሰ መስተዳድሩ በስቅለት ዕለት በቤተክርስቲያን ተገኝተው ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን መወጣታቸውን እንደ ነውር የቆጠሩ አካላትን በብርቱ የታገለውና በቂ ምላሽ የሰጠው ኩነ ደመላሽ ካሳዬ ተፈቷል ።
ዝ ውእቱ ጊዜ ባርኮት ።
የምስጋና ጊዜ አሁን ነው ቤተክርስቲያን ሆይ አመስግኚ ልጅሽ ወዳጅሽ ተፈቷል ።
እንኳን ደስ አለን ።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።

የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጉብኝት በፎቶ🙏💖⛪
14/05/2026

የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጉብኝት በፎቶ
🙏💖⛪

Address

Wolayta Sodo
Sodo
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ:

Share