የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ

የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ድምፅ!
በዚህ ፔጅ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፣ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ የቤ/ያን መረጃዎችን፣ስብከቶችንና መዝሙሮችን ያገኛሉ!!
👉ቤተሰብ ይሁኑ🙏 spritual news

👉‎በማላዊ 1900 ነፍሳት ወደ  ኦርቶዶክሳዊት በረት ተጨምረዋል እግዚአብሔር ይመስገን !!‎‎ቤተ ክርስቲያኑ የሚገኘው በማላዊ ዋና ከተማ በሆነችው ሊሎንግዌ (Lilongwe) ውስጥ ነው። ​በ...
16/09/2026

👉‎በማላዊ 1900 ነፍሳት ወደ ኦርቶዶክሳዊት በረት ተጨምረዋል እግዚአብሔር ይመስገን !!

‎ቤተ ክርስቲያኑ የሚገኘው በማላዊ ዋና ከተማ በሆነችው ሊሎንግዌ (Lilongwe) ውስጥ ነው። ​በቅዱስ ሚካኤል እና ሩፋኤል፣ የሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ እና የሰማዕቷ ቅድስት ማሪና የግብፅ (ኮፕቲክ) ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን (Coptic Orthodox Church) ነው ።

በዛሬው ዕለት 1900 ነፍሳት ተጠምቀው የእግዚአብሔር ልጅነት አግኝቷል እግዚአብሔር ይመስገን 👏

‎Via Ayu Princes

የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ

በስም ሦስት ሲሆን እንዲሁም በአካል🎤በግብርም ሦስት ነው ያለመቀላቀልፍጥረትን በመፍጠር በአምላክነትበባሕሪይ እና ደግሞም በመንግሥት አንድ አምላክ ነው እንጂ አይባልም ሦስት🙏💖†         ...
16/09/2026

በስም ሦስት ሲሆን እንዲሁም በአካል🎤
በግብርም ሦስት ነው ያለመቀላቀል
ፍጥረትን በመፍጠር በአምላክነት
በባሕሪይ እና ደግሞም በመንግሥት
አንድ አምላክ ነው እንጂ አይባልም ሦስት🙏💖
† † †
ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር
ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር (፪)
የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ
Tãkèlé TTTübê
Nebyu Zegedam Tube
Kune Demelash kassaye -Arba Minch

ዓባይ ባንክ በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ተማሪዎች በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይስተጓጎሉ የደብተር ድጋፍ አደረገ። መስከረም  ...
15/09/2026

ዓባይ ባንክ በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ተማሪዎች በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይስተጓጎሉ የደብተር ድጋፍ አደረገ።

መስከረም ፭ ቀን ፳፻፲፱ ዓ.ም

ዓባይ ባንክ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፡ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መልካም ፈቃድ ሶስት መቶ ሺ ብር የሚያወጣ ከአራት ሺ በላይ ደብተር በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አደረገ ።
አቶ አሰፋ ተፈራ የባንኩ ምክትል ፕሬዝዳንት ፣አቶ ማርቆስ ደመቀ የባንኩ የሀብት ማሰባበሰብ መምሪያ ዳይሬክተር፣ አቶ አሰግደው ሽመልስ የማርኬቲንግ መምሪያ ዳይሬክተር ፣ አቶ አበጀ ተስፋ የአራት ኪሎ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ እና ሌሎች የባንኩ የሥራ ኃላፊዎች በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ተገኝተው ስጦታውን የበረከቱ ሲሆን አቶ አሰግደው ሽመልስ የባንኩ የማርኬቲንግ መምሪያ ዳይሬክተር ባንኩ ቅድስት ቤተክርስቲያን በምታካሂዳቸው የልማት እንቅስቃሴዎች ቀዳሚ የድጋፍ አጋር በመሆን እየሠራ ይገኛል ብለዋል።
አክለውም በብፁዕነታቸው አማካኝነት በሸገር ከተማ የተገነቡት ትምህርት ቤቶችም የትውልድ ግንባታ አካል በመሆናቸው ባንኩ አጋርነቱን ማሳየቱን ገልጸዋል።

በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፡ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ድጋፉን ተረክበው በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት ልጆች ከት /ቤት እንዳይቀሩ ዓባይ ባንክ የበኩሉን ድርሻ በመወጣቱ አመስግነዋል።
ወገንን መርዳት ቀዳሚነው በማለት ልጆች እውቀትን የሚያገኙበትን መንገድ መደገፍ ደግሞ ከሁሉ የሚበልጥ ተግባር መሆኑንም ገልፀዋል። ብፁዕነታቸው ዘመኑ የበረከት እንዲሆንም በመመኘት አባታዊ ቡራኬ ሰጥተዋል።
©የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ
Tãkèlé TTTübê

ከአሜሪካ የተመለሱ 17 የኢትዮጵያ መንፈሳዊ የብራና መጻሕፍት ለሰባት ተቋማት ተከፋፈሉ።በመቅደላ ጦርነት የተዘረፈውን ወንጌል ጨረታ ለማስቆም ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ተገልጿል።መስከረም ...
15/09/2026

ከአሜሪካ የተመለሱ 17 የኢትዮጵያ መንፈሳዊ የብራና መጻሕፍት ለሰባት ተቋማት ተከፋፈሉ።
በመቅደላ ጦርነት የተዘረፈውን ወንጌል ጨረታ ለማስቆም ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ተገልጿል።
መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም
በኢትዮጵያ የቅርስ ባለስልጣን አዳራሽ በተካሄደ ደማቅ ሥነሥርዓት፣ ከአሜሪካ የተመለሱ 17 ውድ የኢትዮጵያ መንፈሳዊ የብራና መጻሕፍት ለሰባት የኢትዮጵያ ተቋማት በስጦታ ተላለፉ። በዚህ ታሪካዊ የርክክብ መርሐ-ግብር ላይ የባለስልጣኑ የሥራ ኃላፊዎች፣ ከአሜሪካ የመጡ የአጥኝዎች ቡድን አባላት፣ ታዋቂ አርቲስቶችና የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ የቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረ/ፕ አበባው አያሌው ባደረጉት ንግግር፣ እነዚህ የሀገር ባሕልና ታሪክ መገለጫ የሆኑ ቅርሶች ቀደም ባሉት ጊዜያት በተለይም ከ1970ዎቹ ጀምሮ በሕገ-ወጥ መንገድና በምስጢር ከሀገራችን ወጥተው የቆዩ መሆናቸውን አስታውሰዋል። ቅርሶቹን ወደ እናት ሀገራቸው ለመመለስ የተደረገው ጥረት ውጤት ማምጣቱን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ለተቋማቱ መተላለፋቸው ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ቅርሶቹን ጠብቆ ለትውልድ ለማቆየት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው አክለው ገልጸዋል።

የተመለሱት 17ቱ የብራና መጻሕፍት እንደየይዘታቸውና ለጥናትና ምርምር ካላቸው ጠቀሜታ አንጻር ለሚከተሉት ሰባት የሀገሪቱ ተቋማት ተከፋፍለዋል፦

-ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት፦ 7 መጻሕፍት

-ለኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር)፦ 2 መጻሕፍት

-ለኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን፦ 2 መጻሕፍት

-ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም (IES)፦ 2 መጻሕፍት

-ለማኅበረ ቅዱስ 2 መጻሕፍት
- ለኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ እና ለኃይሌ ሚነስ አካዳሚ የቀሩት መጻሕፍት በስጦታ አንዳንድ መጻሕፍት ተበርክቶላቸዋል ።

በተለይም ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከተመለሱት መጻሕፍት መካከል አርባዕቱ ወንጌል፣ የዓመቱ መጀመሪያ አጋማሽ ስንክሳር እና ውዳሴ ማርያም እንደሚገኙበት በሥነሥርዓቱ ላይ ተገልጿል።

በሌላ በኩል፣ በ1860 ዓ.ም. በመቅደላ ጦርነት ወቅት በእንግሊዝ ጦር የተዘረፈውንና በአጼ ቴዎድሮስ እጅ የነበረን ውድ የኢትዮጵያ የወንጌል የብራና መጽሐፍ፣ በአሁኑ ወቅት በአቡ ዳቢ ለጨረታ ያቀረበውን የኦስትሪያውን ኢንሊብሪስ (Inlibris Gilhofer Nfg) ድርጅት ሽያጭ ለማስቆም ሰፊ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እየተደረገ መሆኑ በዕለቱ ተጠቁሟል።

ድርጅቱ ለዚህ ታሪካዊ ቅርስ 250 ሺህ ዩሮ (በኢትዮጵያ ብር ወደ 47 ሚሊዮን ገደማ) የመነሻ ዋጋ ጠይቆ ለሽያጭ አቅርቦታል። ይህንን ሕገ-ወጥ የቅርስ ሽያጭ ሙሉ በሙሉ ለማስቆም እና ቅርሱን ወደ ሀገሩ ለመመለስ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋራ በመሆን የሕግና የዲፕሎማሲ ሂደቶችን እያከናወኑ እንደሚገኙ ተገልጿል። ይህ ታሪካዊ የቅርስ መመለስ መርሐ-ግብር በሕገ-ወጥ መንገድ የጠፉና የተዘረፉ ሌሎች የሀገራችን ቅርሶችን ለማስመለስ ለሚደረገው አገራዊ ጥረት ትልቅ ማበረታቻና ማሳያ መሆኑ ተመልክቷል።

የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል   ዛቢ ጎይድ ቀበሌ   ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ‎የፊታችን መስከረም 23 /2019 ዓ.ም ይመረቃል።‎‎እግዚአብሔር ይመስገን 🙏⛪‎
15/09/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዛቢ ጎይድ ቀበሌ ህንፃ ቤተ ክርስቲያን
‎የፊታችን መስከረም 23 /2019 ዓ.ም ይመረቃል።

‎እግዚአብሔር ይመስገን 🙏⛪

15/09/2026

ገብረ ሕይወት

 #53 ዓመታትን ያስቆጠረው የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የአስኳላ ትምህርት ቤት የ2019 ዓ/ም ትምህርት ዘመን የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ብፁዓን አበውሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት እየተከ...
15/09/2026

#53 ዓመታትን ያስቆጠረው የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የአስኳላ ትምህርት ቤት የ2019 ዓ/ም ትምህርት ዘመን የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ብፁዓን አበውሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት እየተከናወነ ይገኛል!

በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር አህጉረ ስብከት እንዲሁም የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ መልአከ ሕይወት አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ፣ መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የገዳሙ አስተዳዳሪ ሊቀ ኅሩያን አባ ኤልያስ በልሁ ፣ የትምህርት ቤቱ መምህራን እና ተማሪዎች ተገኝዋል።

©አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ፤

የጻድቁ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ የቃል ኪዳን ጸሎትና ምልጃ ከሁላችን ጋር ይሁን!🙏❤️     የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ
15/09/2026

የጻድቁ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ የቃል ኪዳን ጸሎትና ምልጃ ከሁላችን ጋር ይሁን!🙏❤️


የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ

ታቦቱን ከመንበሩ ፥ ካህኑን ከደብሩ ያቆይልን!ምእመኑን ይጠብቅልን!ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን!መልካም ቀን!🙏⛪
15/09/2026

ታቦቱን ከመንበሩ ፥ ካህኑን ከደብሩ ያቆይልን!
ምእመኑን ይጠብቅልን!
ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን!

መልካም ቀን!🙏⛪

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተ...
14/09/2026

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች ርእሰ ዓውደ ዓመት በማስመልከት ከቅዱስነታቸው ቡራኬና የሥራ መመሪያ ተቀበሉ።

በመርሐ ግብሩ የሁለቱ የሥራ ክፍሎች ተወካይ ባደረጉት ንግግር የዓመቱን ሥራ በቅዱስነታቸው ቡራኬ መጀመራቸው ታላቅ ዕድል መሆኑን አስታውሰው፤ "የቅዱስነትዎን የዕለት ከዕለት አባታዊ የሥራ መመሪያ እየተቀበልን በማገልገል፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ከነሙሉ ክብሯ ለማሻገር እንችል ዘንድ ቡራኬዎና ጸሎትዎ አይለየን…" ሲሉ በመንፈሳዊ የልጅነት አክብሮት ጠይቀዋል።

ብፁዕ ወቅዱስነታቸውም "ዘመነ ማርቆስ ከነበርካታ ችግሮቹ በማለፉ እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፤ የጀመርነውን ዘመነ ሉቃስ መልካም ዓመት ያድርግልን፤ እናንተም ይህንኑ አስባችሁ እንኳን አደረስዎ ለማለት በመቅረባችሁ አመሰግናለሁ፤ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ ሰላም፣ ፍቅር፣ መተሳሰብና መከባበር የሰፈነበት መሆኑ የሚያስደስት ሲሆን በአዲሱ ዘመንም ይህንኑ የሥራ መንፈስ አጠናክራችሁ በመቀጠል፤ የተሰጣችሁን ታላቅ የቤተክርስቲያን ሓላፊነት በሐቀኝነት፣ በቅንነትና በታማኝነት እየተናበባችሁ ልትወጡ ይገባል…" ሲሉ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጭ ጉዳይ መምሪያ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ዐበይት ተግባራት የሚከናወኑባቸው ታላላቅ የቅድስት ቤተክርስቲያናችን ተቋማት መሆናቸው ይታወቃል።
ያረካል አድማሱ


የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ

Address

Wolayta Sodo
Sodo
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደቡብ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ድምፅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share