ሀቢታት አጥቢያ ቃ/ ሕ/ ቤ/ያን

ሀቢታት አጥቢያ ቃ/ ሕ/ ቤ/ያን “እኛም በክርስቶስ ፍጹም የሚሆን ሰውን ሁሉ እናቀርብ ዘንድ ሰውን ሁሉ እየገሠጽን ሰውንም ሁሉ በጥበብ ሁሉ እያስተማርን የምንሰብከው እርሱ ነው፤”
ቆላስይስ 1፥28
👉ገጻችንን Follow በማድረግ በቅዱሳን ሕብረት ይቀላቀላሉ።

01/08/2026

በቤተክርስቲያናችን በተካሄደው ወጣቶች ሳምንት ከዘማሪት #ሰላም ደስታ ጋር ጌታን በዝማሬ ከፍ ከፍ ያደረግንበት፤ ድንቅ ጊዜ እንሆ በቪዲዮ ከስር ተለቋል።👇በመመልከት ተባረኩበት👇
Selam Desta

በቤተክርስቲያናችን ለ11ኛ ዙር የሚከበረው ወጣቶች ሳምንት በብዙ መከናወን፤ እግዚአብሔር ጉልበታችን ሆኖ በድል ተጠናቀቀ       ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ምየ2018 ወጣቶ...
27/07/2026

በቤተክርስቲያናችን ለ11ኛ ዙር የሚከበረው ወጣቶች ሳምንት በብዙ መከናወን፤ እግዚአብሔር ጉልበታችን ሆኖ በድል ተጠናቀቀ

ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም

የ2018 ወጣቶች ሳምንት "...ታገኙ ዘንድ ሩጡ " በሚል መሪ ቃል ለ11ኛ ዙር ከሐምሌ 13 እስከ 19 ድርስ ሲካሄድ የነበረው፤ ልዩ የወጣቶች ሳምንት በእግዚአብሔር እርዳታ በብዙ መከናወን በሰላም ተጠናቋል።

ልዩ የወጣቶች ሳምንት ማጠቃለያ መድረክ በሁለት ክፍለ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን፤ በመደበኛው አምልኮ ሙሉ የቤተክርስቲያኗ ጉባኤ በተገኙበት ከቤተክርስቲያናችን አምልኮ ሕብረትና ከዘማሪ ማርቆስ ጋር ጌታን በዝማሬ በማወደስ፤ እንዲሁም ከፓ/ር ዮሴፍ በቀለ ጋር በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ውድ የሆነውን የእግዚአብሔር ቃል እጅግ ደስ በሚል መንገድ ተከፋፍለናል።

➬ የተከፋፈልነው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ምሳሌ 31v10-31
➬ የተካፈልነው ሃሳብ ፦ ልባም ሰው ተፈልገዋል

እግዚአብሔርን መፍራት በምን ተገለጠ?

#1ኛ በመሰጠት (ቁ_12)
#2ኛ በመስጠት (ቁ_20
#3ኛ የሀኬት እንጀራ አትበላም (ቁ_27)
#4ኛ አፏን በጥበብ ትከፍታለች (ቁ_26)
#5ኛ ስራ ወዳድና ታታሪ (ቁ_19)

ከዚህች ሴት ምን እንማራለን?

#1ኛ ትጋት (ቁ-19)
#2ኛ ጥሩ መሪነት (ቁ_15)
#3ኛ ቁርጠኝነት (ቁ_17)
#4ኛ ሥራውን ትገመግማለች (ቁ_18፤27)

የመጡ ውጤቶች
።።።።።።።።።።።።።
✅ዋጋችን እጅግ ውድ መሆን (ቁ_10)
✅ ሰው የሚታመንበት ሰው መሆን
✅ የሚተርፍ መሆን (ቁ_14)
✅ ብርቱና የተከበረ መሆን
✅ በልጆች የሚመሰገን ሰው መሆን
✅ በትዳር አጋር የሚመሰገን መሆን

ከሰዓት በነበረን ማጠቃለያ ፕሮግራም ከዘማሪ ማርቆስ እና ከቤተክርስቲያናችን አምልኮ ህብረት ጋር ጌታን ከፋ ከፍ በማድረግ ድንቅ ጊዜ አሳልፈናል።

እንዲሁም ከፓ/ር ዮሴፍ በቀለ ጋር እንዲህ በሚል ዕርስ፦ በጸሎት፣ በቃሉና በመንፈስ ቅዱስ ሙላት የተለወጠ ህይወትና አገልግሎት።

ክፍል ሁለትን በመቀጠል... ስለ ጸሎት ምንነትና አንድ ክርስቲያን ጸሎትን እንዴት መጸለይ እንዳለበትና የእግዚአብሔር ቃል በምን መንገድ ማጥናት እንዳለበት ለወጣቱ አቅጣጫ በማሳየት።

የማይጸልይ ክርስቲያን ሕይወት ምን እደሚመስል በማስገንዘብ ለወጣቱ ጥልቅ መልዕክት በማስተላለፍ ተጠናቋል።

በዚህ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ተገኝቶ በሁሉ የረዳን እግዚአብሔርን በማመስገን፤ በተለያዬ መንገድ ሳምንቱን ሙሉ ያገለገሉ አገልጋዮችን፣ ወጣቶችን እና በየእለቱ እየመጡ የእግዚአብሔር ቃል የተማሩ ወጣቶችንና የቤተክርስቲያን ምዕመናን በሙሉ የቤተክርስቲያናችን ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አስራት ሎሃ አመስግነዋል።

በሌላ በኩል በተለያዬ መንገድ በወጣቶች ሳምንት ላገለገሉ አገልጋዮች ልዩ ስጦታ የተሰጠ ሲሆን፤ በወጣቶች ሳምንት ፕሮግራሙ እንዲሳካ የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ ወጣቶች የምስጋና ምስክር ወረቀት ተሰቷቸዋል።

እንዲሁም በ2018 የወጣቶች ሳምንት "ስፖርት ለወንጌል ዓላማ" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የመረብ ኳስ ጫወታ ሻንፒዮን ለሆነው ቤቴል ዞን የዋንጫ እርክብክብም በድምቀት ተካሂዷል።

በዕለቱ ያገለገላችሁ በሙሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ!

ይህን ድንቅ ጊዜ የሰጠን የእግዚአብሔር ስም ይባረክ።

📲በተለያዬ Social ሚዲያ አማራጮች የወጣቶች ሳምንት ፕሮግራም ስትከታታተሉ የነበራችሁ ቅዱሳን በሙሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ።

✍️️በወጣት፡ ብሩክ ሰይፉ

📲የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን‼️

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን ስድስት በቀጠለው፤ ጸሎት የክርስቶስ ህይወት ሲሆን፤ ምን ያህል በየእለቱ እየተለማመድን ይሁን          ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ18/2018 ዓ...
26/07/2026

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን ስድስት በቀጠለው፤ ጸሎት የክርስቶስ ህይወት ሲሆን፤ ምን ያህል በየእለቱ እየተለማመድን ይሁን

ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ18/2018 ዓ.ም

የማይጸልይ አማኝ ክርስቶስ ልመስል ይቸገራል፣ የማይጸልይ አማኝ ሴጣንን ልያሸንፍ ይቸገራል፣ የማይጸልይ አማኝ በተከፈተ ሰማይ ልያመልክ ይቸገራል።

ከዘማሪ ማርቆስ ጋር የጌታን መልካምነት እና ምህረቱን እያሰብን በዝማሬ ጌታን ያወደስንበት ድንቅ ጊዜ ነበር ጌታ ይባረክ።

በቃል ክፍለ ጊዜ ከፓ/ር ዮሴፍ በቀለ ጋር በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ድንቅ መልዕክት ተከፋፍለናል።

➬ የተከፋፈልነው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ሮሜ 8v29

👉የተከፋፈልነው ዕርስ ፦ በጸሎት፣ በቃሉና በመንፈስ ቅዱስ ሙላት የተለወጠ ህይወትና አገልግሎት።

#ኢየሱስን እንድንመስል ተወስኖብናል! ሮሜ 8v29
#ኢየሱስን ስንመስል ኢየሱስን መግለጥ እንችላለን።
#ኢየሱስን ስንገልጥ እግዚአብሔርን እናከብራለን።

✴ከላይ የተጠቀሱትን ለመሆን ከሚረዱን ውጥስ አንዱ የሆነው፤ የክርስቶስ ህይወት የጸሎት ህይወት ነው!

#1ኛበአገልግሎቱ መጀመሪያ

✅ሉቃ 3V22 ስጸልይም ሰማይ ተከፈተ
✅ ሉቃ 4V1-2 40ቀንና 40 ሌሊት ፆመ ጸለየ(ማቴ4)

#2ኛ በእለት ተዕለት ህይወቱ (የሁልጊዜ ህይወቱ ጸሎት ነው)
✅ሉቃ 5V15 ወደ ምረ ባደ ፈቀቅ ብሎ..
✅ሉቃ 9V18 ለብቻው ስጸልይ
✅ ሉቃ 9v28 ጴጥሮስ፣ዮሐንስ ፣ያዕቆብን ይዞ ወደ ተራራ ወጣ...

#3ኛ በትምህርቱ ውስጥ (አገልግሎት ውስጥ) ያላጣነው ነገር ጸሎት ነው።
✅ ሉቃ 11V1 በአንድ ስፍራ ይጸልይ ነበር በጨረሰም ጊዜ ከደቀመዛሙርቱ አንዱ ... እንጸልይ ዘንድ አስተምረን...
✅ ሉቃ 11V2 ስትጸልዩ እንዲህ ብላችሁ ጸልዩ...
✅ ሉቃV1 ሳይታክቱ ዘውትር መጸለይ እንሚገባቸው በምሳሌ ያስተምር ነበር።

#4ኛ ማሳሰቢያ (ኑዛዜ ውስጥ )
✅ ሉቃ 22V40 ወደ ፈተና እንዳትገቡ ... ከድንጋይ ውርወራ የሚያህል ርቆ ተንበርክኮ ይጸልይ ነበር...42-44
✅የኔ ፍቃድ አይሁን የአንተ እንጂ ...
✅ሉቃ 45-46..አፅንቶ ይጸልይ ነበር። ኃይል ሳትቀሉ ከኢየሩሳሌም አትውጡ።

🔥ሐዋሪያት የክርስቶስን የጸሎት ሕይወት ወርሰው ነበር..🔥

✅ሐዋ 1V1 4v25 በአንድ ልብ በጸሎት ይተጉ ነበር። ስጸልዩም

✅ሐዋ 3V1 ጴጥሮስ እና ዮሐንስ በጸሎት ጊዜ በዘጠኝ ሰዓት ወደ መቅደስ ይወጡ...

✅ሐዋ 4V31 ከጸለዩም በኃላ ተሰብስበው የነበሩበት ስፍራ ተናወጠ..

✅ሐዋ 6V3 እኛ ግን ለጸሎት እና ቃሉን ለማንበብ እንተጋለን

✅ ሐዋ 8V2 በጸሎት የተጉ አይሁድ እስጢፋኖስን ቀበሩት...

‎በዚህ መንገድ የእግዚአብሔር ቃል የተማርን ሲሆን፤ በወጣቶች ሳምንት "እስፖርት ለወንጌል ዓላማ" በሚል መሪ ቃል ስካሄድ የነበረው፤ የመረብ ኳስ ጫወታ እንሆ በዛሬው ቀን ፍፃሜውን አግኝቷል።

ዛሬ በተደረገው መረሃ-ግብር ለፍፃሜ የደረሱት የሮቦት ዞን እና የአምናው ሻንፒዮን ቤቴል ዞን የተጫወቱ ሲሆን፤ ሮቦት ዞንን1ለ2 የአምናው ሻምፒዮን ቤቴል ዞን በማሸነፍ የ2018 ወጣቶች ሳምንት በድጋሜ ሻምፒዮን በመሆን ጫወታው በድል ተጠናቋል።

🎇 እንኳን ደስ አላችሁ ቤቴል ዞን🎇
‎🏆ሻምፒዮን ቤቴል ዞን🏆

በዕለቱ ያገለገላችሁ በሙሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ !!

ይህን ድንቅ የአምልኮ ጊዜ የሰጠን የእግዚአብሔር ስም ይባረክ።

✍️️በወጣት ብሩክ ሰይፉ

🔥።።።።።። #ነገ ይቀጥላል።።።።።።።🔥

የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን‼️

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን አምስት በቀጠለው፤ እደሚገባን የመንፈሳዊ ኋይል እንዲሰራ አልተለማመድንም        ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ18/2018 ዓ.ምእንደሚገባ መንፈስዊ ...
25/07/2026

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን አምስት በቀጠለው፤ እደሚገባን የመንፈሳዊ ኋይል እንዲሰራ አልተለማመድንም

ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ18/2018 ዓ.ም

እንደሚገባ መንፈስዊ ኋይል እንዲሰራ አልተለማመድንም፤ አምነናል፣ ድነናል፣ መንፈስ ቅዱስን እንደ ጌታ ፍቃድ ተቀብለናል። ነገር ግን መንፈሳዊ ኋይል መጠቀም በሚገባን ልክ አልተጠቀምንም።

ከዘማሪ ማቲዎስ ጋር በአምልኮ ጌታን በእልልታ በሆታ ከፍ ከፍ በማድረግ በአምልኮ ወደ ሰማይ ሰማያት የነጎድንበት ድንቅ ምሽት ነበረ ጌታ ክብሩን ይውሰድ።

በቃል ክፍለ ጊዜ እጅግ ከምንወዳቸው አባታችን ፓ/ር ዶ/ር ዮሐንስ ባሰና ጋር በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ድንቅ መልዕክት ተከፋፍለናል።

የተከፋፈልነው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ኤፌሶን 3፥20-21
²⁰ እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው፥
²¹ ለእርሱ በቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ኢየሱስ እስከ ትውልዶች ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።

👉 የተከፋፈልነው ሃሳብ፦ "እደሚገባ ያልተጠቀምነው፤ መንፈሳዊ ኋይል"።

አልተጠቀምነውም እንጂ ይህ ኋይል ብዙ ነገር ይሰራል።
➬ የመንፈስ ቅዱስ ኋይል ምን ይሰራል?
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

#1ኛ በምድር ላይ ሆነን የሰማይን ዙፋን እንድንዳስስ የሚያደርግ ኋይል ነው።

#2ኛ ከተፈጥሮ ሕግ በላይ የሆነ ሥራ ለመስራት የሚያስችል ኋይል ነው።
“እግዚአብሔርም በእስራኤል ልጆች እጅ አሞራውያንን አሳልፎ በሰጠ ቀን ኢያሱ እግዚአብሔርን ተናገረ፤ በእስራኤልም ፊት እንዲህ አለ፦ በገባዖን ላይ ፀሐይ ትቁም፥ በኤሎንም ሸለቆ ጨረቃ፤”
— ኢያሱ 10፥12

#3ኛ የሴጣን ሥራ መቋቋም የሚያስችል ኋይል ነው።
2ኛ ቆሮ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ በሰው ልማድ ምንም እንኳ የምንመላለስ ብንሆን፥ እንደ ሰው ልማድ አንዋጋም፤
⁴ የጦር ዕቃችን ሥጋዊ አይደለምና፥ ምሽግን ለመስበር ግን በእግዚአብሔር ፊት ብርቱ ነው፤
⁵ የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥

#4ኛ ከእግዚአብሔር ጋር በህብረት መስራት የሚያስችል ኋይል ነው።

‎👉ይህን ኋይል እንዴት እንለማመዳለን (መለማመድ ) አለብን።
‎========================

‎✅ የጾም ጸሎት ጊዜ በወር ውስጥ እንወስን
‎✅ ተንበርክከን እንጸልይ
‎✅ የእግዚአብሔር ቃል ሳንሰለች እናንብብ
✅ያነበብነውን የእግዚአብሔር ቃል እናሰላስል
‎✅ የተጣናላቸው ካሉ ይቅርታ እናድርግ (ይቅር እንባባል) በፍቅር እንኑር !

‎በዚህ መንገድ የእግዚአብሔር ቃል የተማርን ሲሆን፤ በሌላ በኩል "እስፖርትን ለወንጌል ዓላማ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው የመረብ ኳስ ውድድር ዛሬም በሁለት ምድብ የተካሄደ ሲሆን፤ በዚህም ረፋድ 4፡00 ሰዓት በተካሄደው ጫወታ ኢየሩሳሌም ዞንን 1ለ2 ሮቦት ዞን በማሸነፍ ወደ ፍፃሜ ተሸጋግሯል።

ከሰዓት 8:00 ሰዓት በነበረው መረሃ-ግብር መሐል ዞንን 0 ለ 2 ቤቴል ዞን በማሸነፍ ወደ ፍፃሜ ተቀላቅለዋል። ‎

ዛሬ 8:00 ሰዓት ሮቦት ዞን ከቤቴል ዞን ጋር እጅግ አጓጊ በሆነ መንገድ የዋንጫ ጫወታ ፍጹም በእስፖርታዊ ጨዋነት በተላበሰ ግሩም ጫወታ ያስመለክቱናል።

🏆ለሁለቱም ዞን መልካም እድል!🏆

በዕለቱ ያገለገላችሁ በሙሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ !!

ይህን ድንቅ የአምልኮ ጊዜ የሰጠን የእግዚአብሔር ስም ይባረክ።

✍️️በወጣት፡ ብሩክ ሰይፉ

🔥።።።።። #ዛሬ ይቀጥላል።።።።።።።🔥

📲 የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን‼

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን አራት በቀጠለው፤ አንድ ሰው ዓላማ ያልሳተ ሕይወት ለመኖር በእግዚአብሔር መንፈስ ውስጥ ልኖር ያስፈልጋል         ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ17/...
24/07/2026

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን አራት በቀጠለው፤ አንድ ሰው ዓላማ ያልሳተ ሕይወት ለመኖር በእግዚአብሔር መንፈስ ውስጥ ልኖር ያስፈልጋል

ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ17/2018 ዓ.ም

የእግዚአብሔር ዓላማ እስራኤላውያንን ከፍልስጥኤማውያን እጅ ነፃ ማውጣት ነው፤ ለዚህም ዓላማ የተላከው ሰው ሳምሶን ነው። ነገር ግን እግዚአብሔር ያየለትን ትልቅ ዓላማ ስስት እንመለከታለን።

በየትኛውም ሕይወት ብንኖር እግዚአብሔር በኛ ላይ ዓላማ አለው ያንን ዓላማ ሳንስት እንኑር።

ከቤተክርስቲያናችን አሳፍ አምልኮ ህብረት እና ከዘማሪ ጥበቡ ዳንኤል ጋር በሕይወታችን ምህረት ያበዛልን፤ ሳንወደው የወደደንን ውለታውን እያሰብን ይህን ድንቅ ጌታችን በእልልታ፣ በልዩ ቅኔ አወድሰናል።

በቃል ክፍለ ጊዜ ከቤተክርስቲያናችን መጋቢ ፍቃዱ ፋንታ ጋር "ዓላማ ያልሳተ ሕይወት መኖር" በሚል ሃሳብ የእግዚአብሔር ቃል ተከፋፍለናል፤ የተከፋፈልነው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል መሳፍንት 13V1-5 ተጨማሪ ክፍል እዛው ምዕራፍ 14V4

የሳምሶን ሕይወት በጥልቀትና በስፋት በመቃኘት ፦ ዓላማ ያልሳተ ሕይወት ለመኖር ዋነኛውና ወሳኙ ነገር ፦

#1ኛ እግዚአብሔር በኛ ላይ ያስቀመጠውን ዓላማ መረዳትና ማወቅ ያስፈልጋል። ምዕራፍ 6V14
➯ሳምሶን፦ የእግዚአብሔር ዓላማ በሱ ላይ ምን እንደሆነ ያውቅ ነበረ ግን የእግዚአብሔር ዓላማ ስቱዋል። ምዕ 16V17

#2ኛ በእግዚአብሔር መንፈስ እስከመጨረሻው መመራት። ወይም የእግዚአብሔር መንፈስ ይመራናል። ምዕራፍ 13V24-25
➯ሳምሶንን፦ የእግዚአብሔር መንፈስ ስመራው እንመለከታለን፤ ነገር ግን እስከ መጨረሻው አልተመራም።

#3ኛ ከመለኮታዊ ዓላማ ከሚያስቱ ነገሮች መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
➯ሳምሶን ፦ በመጀመርያ የወላጆችን ምክር ባለ መስማት ለውድቀት ተጋልጧል። ምዕራፍ 14V1 ጀምሮ እና 16V1

#4ኛ በጥበብ መመላለስ ያስፈልጋል።
➯ሳምሶን፦ በጥበብ ባለ መመላለሱ ምክንያት ዓላማውን ስቱዋል። ምዕራፍ 16V13

#5ኛ እንደገና ለመነሳት መጣር ያስፈልጋል።
➯ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ጴጥሮስ ነው።
ሌላው ሳምሶን እራሱ በእግዚአብሔር ሃሳብ በይሆንም አንድ ልመና ስለምን እንመለከታለን።

✅ ጠላቶቻችሁ እንዳይደፍሯችሁ በጥበብ ተመላለሱ!🙏

በዚህ መንገድ የእግዚአብሔር ቃል የተማርን ሲሆን፤ በሌላ በኩል "እስፖርትን ለወንጌል ዓላማ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው የመረብ ኳስ ውድድር ዛሬም በሁለት ምድብ የተካሄደ ሲሆን፤ በዚህም ረፋድ 4፡00 ሰዓት በተካሄደው ጫወታ ቤቴል ዞን 2ለ0 ሮቦት ዞንን አሸንፏል።

በዚህ ምድብ ቀድሞው ባስመዘገቡት ወጤት ሮቦት ዞን ወደ ግማሽ ፍፃሜ ስቀላቀል፤ ቤቴል ዞን በዚህ ምድብ አንደኛ በመሆን አልፈዋል።

ከሰዓት8:00 ሰዓት በነበረው መረሃ-ግብር መሐል ዞን 1ለ 2 በኢየሩሳሌም ዞን ተሸንፏል። በዚህ ምድብ ኢየሩሳሌም ዞን ከምድቡ አንደኛ በመሆን ያለፈ ሲሆን መሐል ዞን በዚህ ምድብ ሁለተኛ በመውጣት አልፈዋል።

በዕለቱ ያገለገላችሁ በሙሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ !!

ይህን ድንቅ የአምልኮ ጊዜ የሰጠን የእግዚአብሔር ስም ይባረክ።

✍️️በወጣት፡ ብሩክ ሰይፉ

🔥።።።።። #ዛሬ ይቀጥላል።።።።።።።🔥

📲 የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን‼

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን ሶስት  በቀጠለው፤ እጅግ ከምንወደው ፓ/ር ዶ/ር ዘውዱ ዘለቀ ጋር "መንፈሳዊ መታወር" በሚል ሃሳብ ውድ የሆነውን የእግዚአብሔር ቃል ተምረናል     ...
22/07/2026

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን ሶስት በቀጠለው፤ እጅግ ከምንወደው ፓ/ር ዶ/ር ዘውዱ ዘለቀ ጋር "መንፈሳዊ መታወር" በሚል ሃሳብ ውድ የሆነውን የእግዚአብሔር ቃል ተምረናል

ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም

ጌታ አምላካችንን በአምልኮ ከፍ ከፍ በማድረግ በልዩ ዜማ እና ቅኔ ከቤተክርስቲያናችን አረኤል ህብረት ጋር እና እጅግ ከምንወዳት ከዘማሪት ሰላም ደሰታ ጋር ጌታ ድንቅ ጊዜ ሰቶን ሰማይ በአንጻራችን ክፍት ሆኖ ይህን ድንቅ ጌታችን አወድሰናል።

በቃል ክፍለ ጊዜ ከፓ/ር ዶ/ር ዘውዱ ዘለቀ ጋር በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ለዚህ ዘመን ክርስቲያን እራሱን ወይም ያለበትን ሕይወት የሚፈትሽበትን ድንቅ መልዕክት ይዞ ቀርበዋል።

በዚህም የተከፋፈልነው የእግዚአብሔር ቃል ክፍል የሉቃስ ወንጌል 9V45 - 56 እና የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 9V35-41

የሉቃስ ወንጌል መነሻ በማድረግ የዮሐንስ ወንጌል ዳሰሳ አድርገን እንዲህ በሚል ዕርስ ፦ መንፈሳዊ መታወር 👁️👁️ በሚል ተምረናል።

በዚህ ክፍል ውስጥ አንድ ዕውር ሆኖ የተወለደውን ሰው👁️ጌታ ኢየሱስ አይኑ የከፈተለትን ሰው በመግለጽ፤‎ በዛው ስፍራ በአካል ማየት የሚችሉት ፈሪሳውያን ከእነርሱ ፊት የቆመውን መሲህ (ኢየሱስን) ማወቅ አለመቻላቸው አስረድተዋል።

ዛሬ በቤተክርስቲያን በተለያየ መንገድ እያገለገልን መንፈሳዊ መታወር ልያጠቃን ይችላል።

ስራት በመፈጸም ብቻ ወንበር እያሞቅን፣ መጸለይ ስገባን ሳንጸልይ፣ በትቢት ተወጥረን፣ በክፋት፣ በተንኮል፣ በዘረኝነት ተወጥረን፤ በቤተክርስቲያን ውስጥ በንጽሕና፣ በቅድስና መመላለስ እያለብ አለመመላለስ።

‎👉በእውነት ጌታ👁️ዓይኖቻችን👁️እንዲህ ከፍት (እውነትህን) እንድናይ በለን እራሳችን በሱ ፊት አዋርደን፣ ዝቅ ብለን ከጸለይን የሚሆኑ ነገሮች ፦

✅ ደንዳናው ልባችን ይሰበራል
✅ አለማመን ከኛ ላይ ይርቃል
✅ ወደ ኢየሱስ ወይም ወደ ክብሩ እንጠጋለን
✅ ቃሉን እየተማርን ዓይኖቻችን ይበራሉ።

በዚህ መንገድ የእግዚአብሔር ቃል የተማርን ሲሆን፤ በሌላ በኩል "እስፖርትን ለወንጌል ዓላማ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው የመረብ ኳስ ውድድር ዛሬም በሁለት ምድብ ተካሂዷል።

ረፋድ 4፡00 ሰዓት በተካሄደው ጫወታ መሐል ዞን ወደ ጥሎ ማለፍ ስሸጋገር አቤኔዘር ዞን በሁለት ተከታታይ ሽንፈት ከውድድሩ ተሰናብተዋል።

ከሰዓት8:00 ሰዓት በነበረው መረሃ-ግብር ትንሳኤ ዞን በሁለት ተከታታይ ሽንፈት እሱም በተራው ስሰናበት፤ ሮቦት ዞን በተሻለ እንቅስቃሴ ወደ ጥሎ ማለፍ ተሸጋግሯል።

የቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ተወካይ እና የመሐል ዞን ቡድን አስተባባሪ ወጣት አማኑኤል ዳና እንደገለፀው፤ እስፖርት ለወንጌል ዓላማ ብለን፣ በወጣቶች ሳምንት በምናካሂደው ውድድር ላይ በሕይወታችን በኑሯችን፣ ክርስቶስ ለመግለጥ ነው ግባችን።

በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ለ36ኛ ዙር "ስፖርት ለወንጌል ዓላማ" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ውድድር ላይ እግዚአብሔር አርባ ሁለት ሺህ የሚሆኑ አዳዲስ ነፍሳትን ጨምሯል።

በቤተክርስቲያናችንም በዚህ "ስፖርት ለወንጌል ዓላማ" በለን፤ በምናካሂደው ውድድር ላይ አዳዲስ ነፍሳትን እናገኛለን ለዚህም ጌታ ይረዳናል።

አያይዘውም በዚህ ወጣቶች ሳምንት ወጣቱ በተለያዬ ስፍራ ጊዜውን እንዳያጠፋ ወደ ቤተክርስቲያን በመምጣት የእግዚአብሔር ቃል እንዲሰሙ በማድረግና ሀላፊነትም እየሰጠን፤ በተለያዩ ዘርፍ ገብቶ እንድያገለግሉ አድርገናል። ለአብነትም፦ በጸሎት ህብረት ፣ በወንጌል መስካሪያን ቡድን፤ በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት እንዲቀላቀሉ በማድረግ ሰርተናል።

እንዲሁም የ6ቱ ዞናት መሪዎች በየዞናቸው ያሉ ወጣቶችን አስተባባሪው ወደ ቤተክርስቲያኗ እንዲያመጧቸው እያደረግን እንገኛለን ብለዋል።

በሌላ በኩል የወጣቶች ሳምንት ምክንያት በማድረግ በበጎ የምንገነባው ቤት ስላለ፤ "አንድ ሰው አንድ ብሎኬት" ብለን እየተንቀሳቀስ ስለሆነ በዚህ ተግባር የድርሻቸውን ለመወጣት ወይም መደገፍ ለምትፈልጉ። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት 1000018264278 ኤልያስ ሉሴሶ በሚለው ደስ ያላችሁን በማስገባት የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ!🙌

በዕለቱ ያገለገላችሁ በሙሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ !!

ይህን ድንቅ የአምልኮ ጊዜ የሰጠን የእግዚአብሔር ስም ይባረክ።

✍️️በወጣት፡ ብሩክ ሰይፉ

🔥።።።። #ነገ ይቀጥላል።።።።።🔥

📲 የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን‼

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን ሁለት በልዩ ዝግጅት፤ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ተካሄደ          ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ14/2018 ዓ.ምዛሬ በቀጠለው የወጣቶች ሳምንት ሙሉ ፕ...
21/07/2026

በቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሳምንት ቀን ሁለት በልዩ ዝግጅት፤ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ተካሄደ

ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ14/2018 ዓ.ም

ዛሬ በቀጠለው የወጣቶች ሳምንት ሙሉ ፕሮግራም ከዩኒቨርስቲ በመጡ ተማሪዎች አዘጋጅነት በተለያዩ ሁነቶች ደምቆ የተካሄደ ሲሆን፤ ከነሱ ጋር እጅግ ደስ በሚል መንገድ የክርስቶስን ውለታና ፍቅሩን በማሰብ በልዩ ዜማ አምላካችንን አክብረናል።

በቃል ክፍለ ጊዜ ከወጣት፡ አቤነዘር ዘካርያስ ጋር የእግዚአብሔር ቃል የተከፋፈልን ሲሆን፤ የተካፈልነው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ሆሴዕ 3V1-5

➬ የተማርነው ዕርስ ፦ የተወደድንበት ፍቅር ✝

በሌላ በኩል "እስፖርት ለወንጌል ዓላማ" በሚል መሪ ቃል በቤተክርስቲያናችን በወጣቶች ሳምንት የሚካሄደው፤ የመረብ ኳስ ጫወታ በሁለት ምድብ ረፋድ 4:00 ሰዓት እና ከሰዓት8:00 የተካሄደ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ምድብ ኢየሩሳሌም ዞን 2 ለ 1 አቤኔዘር ዞን በማሸነፍ ተጠናቋል።

በምድብ ሁለት ከሰዓት በተደረገው ውድድር ቤቴል ዞን ትንሳኤ ዞን በመግጠም ቤቴል ዞን 2ለ0 በማሸነፍ የዛሬው ምድብ ተጠናቋል።

የኢየሩሳሌም ዞን ቡድን አስተባባሪ አቶ አዲሱ አሽኮ እንደገለጹት፤ ጫወታ ነውና ቀላል አልነበረም እስፖርት ስለሆነ በጥሩ ፉክክር ተጋጣሚዎቻቸውን ማሸነፍ ችለናል።

በርግጥ ግባችን ኳስ ማሸነፍ ወይም መሸነፍ አይደለም የኛ ዓላማ በወጣቶች ሳምንት ምክንያት፤ በምናደርገው ውድድር መካከል ጫወታ ለማየት ለሚሰበሰቡ ወጣቶች የምስራቹን ቃል ለትውልድ ማካፈል ነው።

በመሪ ቃላችን መሰረት "እስፖርት ለወንጌል ዓላማ" እንደተባለው በሜዳ ውስጥ በምናደርገው እንቅስቃሴ እነዚህ ወጣቶችን የምንማርክበት፤ ቀርበናቸው እንድናወራ እድሉን የምናገኝበት ለነሱ አራያ የምንሆንበት ፍጹም ሰላማዊ የሆነ ጫወታ ነው።

አያይዘውም ይህ ዘመን እግዚአብሔር እየመሰሉ ለመኖር ለሚወዱ በጣም አስቸጋሪ ዘመን ነው፤ ወጣትነት በራሱ ስሜታዊነት ያለበት እያሳሳቀ የሚወስድ ጎርፍ ነው።

የሚጣፍጥ በውስጡም ከረሜላ ያለበት መርዝ ስለሆነ ወጣትነት በእግዚአብሔር ቃል መሰረት በመምራት ከዓለምና ከክፉ ምኞት መሸሽ አለበት።

ወጣት ሆነ ሌላው ሰው ዓለምን፣ ፋሽንን አሸንፎ ወደ ክርስቶስ እንዲመለሱ ምክንያቱም ይህች ምድር ካንቱ ነች፤ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ እንዲቀበሉ ብለዋል።

የቤቴል ዞን ቡድን አስተባባሪ ወጣት ወድማገኝ ሴታ በበኩሉ፤ ጠንካራ ዞን ነው የገጠምነው ነገር ግን በጫወታ መሐል ማሸነፍ መሸነፍ ያለ ነው። ምንም እንኳን ጠንካራ ቡድን ብንገጥምም ማሸነፍ ችለናል።

እኛ ክርስቲያኖች ክርስቶስን መምሰል አለብን ኳስ በባህሪው የአንድን ሰው ውስጣዊ ማንነትን የሚገልጥ ነው። ነገር ግን ወደ ሜዳ ስንገባ፤ የገባንበትን ዓላማ ሳንዘነጋ የመንፈሳዊ ማንነትን የምንገልጥበትና እራሳችን የምናይበት መንገድ ነው።

አክለው በውጭ ያሉ ሰዎች በተለያዬ መንገድ ነገሮችን ልያስኬዱ ይችላሉ እኛ ግን ብንሸነፍም፤ ብናሸንፍም ዋናው ዓላማችን ክርስቶስን መግለጥ እርሱን መስበክ ነው።

የዘንድሮው መሪ ጥቅሳችን "ታገኙ ዘንድ እሩጡ" የሚል ነው በዚህ ዘመን ሰው ብዙ ነገር ለማግኘት ይሮጣል እኛ ግን የሰማያዊ አክሊልን ለማግኘት የምንሮጥ ዜጎች ነን።

ሰለሆነም ወጣቱ በወጣትነት እግዚአብሔርን ማገልገል ለዓለማዊም፤ ለመንፈሳዊ ሕይወትም እጅግ ወሳኝ እንደሆነ አምኖ ሙሉ ጊዜ ሰቶ ማገልገል አለበት በማገልገል መባረክ እንዳለም ገልጿል።

በዕለቱ ያገለገላችሁ በሙሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ !!

ይህን ድንቅ የአምልኮ ጊዜ የሰጠን የእግዚአብሔር ስም ይባረክ።

✍️️በወጣት፡ ብሩክ ሰይፉ

🔥።።።።። #ነገ ይቀጥላል።።።።።።።🔥

📲 የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን‼

በሀቢታት አጥብያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ለ11ኛ ዙር የሚከበረው ልዩ የወጣቶች ሳምንት የ2018 ተጀመረ             ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ13/2018 ዓ.ም            ...
21/07/2026

በሀቢታት አጥብያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ለ11ኛ ዙር የሚከበረው ልዩ የወጣቶች ሳምንት የ2018 ተጀመረ

ሀ/አ/ቃ/ሕ/ቤ/ያን፣ ሐምሌ13/2018 ዓ.ም

የዘንድሮው ወጣቶች ሳምንት ከሐምሌ 13 እስከ 19 ድረስ "...ታገኙ ዘንድ ሩጡ። 1ኛ ቆሮንቶስ 9፥24" በሚል መሪ ጥቅስ የሚካሄደው ይህ የወጣቶች ሳምንት እጅግ በማረ መልኩ እንሆ ተጀመረ ።

በወጣቶች መክፈቻ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቤተክርስቲያናችን ምክትል ሰብሳቢ አቶ ጌታቸው ባልቻ እንደገለጹት፤ በሕይወት ኖረን እንዲህ ባለ ማማር የወጣቶችን ሳምንት ለማክበር፤ እግዚአብሔር ሰላም፣ ጤና ሰቶ ለእያንዳዳችን ጥበቃ አብዝቶ በዚህ መልክ የወጣቶች ሳምንት ለማክበር በቅተናል።

አንድ ሳምንት ሙሉ በሚካሄደው በወጣቶች ፕሮግራም ከእሩቅም ከቅርብም የተጋበዙ አገልጋዮችና በወጣቶች የተዘጋጀ የተለያዬ ፕሮግራም እንዳለም ገልጿል።

በቤተክርስቲያናችን ከኬጂ ጀምሮ በተለያዬ ዩኒቨርስቲ የሚማሩትን ዓመት ሙሉ በምህረቱ ጠብቆ፤ በክረምት የወጣቶች ሳምንት ለማክበር እንኳን በሰላም አደረሳችሁ።

አክለውም በወጣቶች ሳምንት በበጎ ተግባር በመሰማራት የምንገነባው ቤት ስላለ ወጣቱ በጉልበት፣ በምክር፣ በገንዘብ በመረዳት አሻራቸውን እንድያኖሩ አሳስበዋል።

ሌላው በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የቤተክርስቲያናችን ዋና መጋቢ ፍቃዱ ፋንታ እንደገለጹት፤ በወጣቶች ሳምንት ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ብዙ ነገር የምናገኝበት፤ እግዚአብሔርን ከተጋባዥ አገልጋዮች ጋር አብረን የምናመልክበት ድንቅ ጊዜ ይኖረናል።

በነዚህ ሳምንታት ወጣቱ ሌላ ቦታ ላይ ጊዜውን ሳያጠፋ ወደዚህ ስፍራ ከሮጠ ብዙ ነገር ያጭዳል።

አያይዘውም ይህ ፕሮግራም የተዘጋጀው ለወጣቶችና ለተወሰኑ ሰዎች ሳይሆን ለሁሉም ሰው ስለሆነ የቤተክርስቲያናችን ምዕመናን በሙሉ እንዲካፈሉ ጋብዘዋል።

ሌላው በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የቤተክርስቲያናችን የወጣቶች ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ኤልያስ ሉሴሶ በበኩላቸው፤ በደቡብ፣ በሰሜን፣ በምራብ፣ በምስራቅ ያለን፤ እግዚአብሔር ዓመቱን ሙሉ በሰላም ጠብቆ ለ11ኛ ዙር ለሚከበረው ለወጣቶች ሳምንት እንኳን በሰላም አደረሳችሁ/ አደረሰን ብለዋል።

ከተጋባዥ አገልጋዮች መካከል የሆኑት እጅግ የምንወዳቸው ዘማሪ እንዳሻው ዱንዳ እና በቃል አገልጋይ ዳዊት ጌታቸው፤ በወጣቶች ሳምንት መክፈቻ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው አግልለዋል።

በዚህ ቀን ከቤተክርስቲያናችን አምልኮ ህብረት ጋርና ከዘማሪ እንዳሻው ጋር ድንቅ የአምልኮ ጊዜ የነበረን ሲሆን፤ በቃል አገልጋይ ዳዊት ጌታቸው ውድ የሆነውን የእግዚአብሔር ቃል አካፍለዋል።

👉የተከፋፈልነው የእግዚአብሔር ቃል📖 ክፍል ኤፌሶን 1V1-14
✅የተከፋፈልነው ሃሳብ ፦ በክርስቶስ የተገኘ በረከት🌺

በዕለቱ ያገለገላችሁ በሙሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ !!

ይህን ድንቅ የአምልኮ ጊዜ የሰጠን የእግዚአብሔር ስም ይባረክ።

✍️️በወጣት፡ ብሩክ ሰይፍ

🔥።።።።። #ነገ ይቀጥላል።።።።።።።።🔥

📲 የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን‼️

"...ታገኙ ዘንድ ሩጡ። 1ኛ ቆሮንቶስ 9፥24" #መቼ ፦ ከሐምሌ 13 -19 ድረስ 🎇በሀቢታት አጥብያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ልዩ የወጣቶች ሳምንት ከፊታችን ሰኞ እስከ ዕሁድ ለተከታታይ ...
17/07/2026

"...ታገኙ ዘንድ ሩጡ። 1ኛ ቆሮንቶስ 9፥24"
#መቼ ፦ ከሐምሌ 13 -19 ድረስ 🎇
በሀቢታት አጥብያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ልዩ የወጣቶች ሳምንት ከፊታችን ሰኞ እስከ ዕሁድ ለተከታታይ ቀናት በታላቅ ድምቀት ይካሄዳል።

በነዚህ ተከታታይ ቀናት እጅግ ተወዳጅ ከሆኑ አገልጋዮች ጋር የእግዚአብሔር ቃል በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የምንማርበት፤ እንዲሁም ጌታን በዝማሬ፣ በእልልታ፣ በሆታ ከፍ ከፍ እያደረግን ወደ ሰማይ ሰማያት የምንፈልስበት ድንቅ ጊዜ ይኖራል።

“ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል፥ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል።” እንደሚል ቃሉ 📖
በበጎነት ከፍ ብለን የምንታይበት፤ የአረጋውያን እንባ የምናብስ ይሆናል።

➬ምን ይሄ ብቻ "እስፖርት ለወንጌል ዓላማ" በሚል መሪ ቃል የቤተክርስቲያናችን ዞናት ከዞናት ጋር የምያደርጉት፤ የመረብ ኳስ ጫወታ በጉጉት የምጠበቅ ሲሆን፤ ሌሎች የተለያዩ አዝናኝ ፕሮግራሞችም ተሰናዷል።

ኑ! ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!🙏

ማሳሰቢያ፦ መቅረት ፈፅሞ የተከለከለ ነው። እንዲሁም ስትመጡ አንዳንድ ወዳጆቻችሁን👬 መጋበዝ እና መጽሐፍ ቅዱስ መያዛቸውን እንዳትዘነጉ።

📢 ይህን መልዕክት ለወዳጆቻችሁ ሼር አድርጉ፤ እንዲሁም ለዚህ ገጽ አዲስ ከሆናችሁ በማድረግ በቅዱሳን ሕብረት ላይ ይቀላቀሉ።

📍አድራሻ ፦ ከማረሚያ ጀርባ ይገኛል።

📲 የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን‼️

ነገ💡በቤተክርስቲያናችን በኤልካዶሽ ሕብረት የተሰናዳ ልዩ የአምልኮ ምሽት ከተጋባዥ ዘማሪ ንጋቱ ጋር ይኖረናል።     🗓ሐምሌ 01/10/2018 ዓ.ም (ዕሮብ)     ⏰ሰዓት ከ11:30 ጀምሮ ...
07/07/2026

ነገ💡
በቤተክርስቲያናችን በኤልካዶሽ ሕብረት የተሰናዳ ልዩ የአምልኮ ምሽት ከተጋባዥ ዘማሪ ንጋቱ ጋር ይኖረናል።

🗓ሐምሌ 01/10/2018 ዓ.ም (ዕሮብ)
⏰ሰዓት ከ11:30 ጀምሮ

“በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤”
ኤፌሶን 5፥19

ኑ! ቅኔ ለሚገባው በቅኔ፣ በዜማ አብረን እናወድሳለን🙌 ማርፈድ ያስቆጫል።

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!🙏

ማሳሰቢያ፦ መቅረት ፈፅሞ የተከለከለ ነው። እንዲሁም ስትመጡ አንዳንድ ወዳጆቻችሁን👬 መጋበዝ እና መጽሐፍ ቅዱስ መያዛቸውን እንዳትዘነጉ።

📢 ይህን መልዕክት ለወዳጆቻችሁ ሼር አድርጉ፤ እንዲሁም ለዚህ ገጽ አዲስ ከሆናችሁ በማድረግ በቅዱሳን ሕብረት ላይ ይቀላቀሉ።

📍አድራሻ ፦ ከማረሚያ ጀርባ ይገኛል።

መልካም ቀን ይሁንላችሁ !!🙏

📲 የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን ስለሚከታተሉ ከልብ እናመሰግናለን‼️

Address

S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሀቢታት አጥቢያ ቃ/ ሕ/ ቤ/ያን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category