ቡኢ ገነት ቤ/ክ Genet Church

ቡኢ ገነት ቤ/ክ Genet Church “በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ?

20/05/2026
04/02/2026

በኢትዮጵያ ገነት ቤተክርስቲያን የጥር ወርን የሚሽን ወር በማለት የሰየመች ሲሆን በዚህ ወር በብሔራዊ ደረጃ ሚሽንን በተመለከተ ግንዛቤ የሚፈጠርበት፣ የተለያዩ ትምህርቶች እና ስልጠና...

ውድ  ቤተሰቦቻችን እንደ ሚታወቀው ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚሆን ሚክሰር/ ማይክ/ እንዲሁም ኪቦርድ ለመግዛት የተጀመረ ቻሌንጅ እንዳለ ይታወቃል በእናንተ ብረታት ለጌታ ቤት ባላቹ ቅንሀት...
18/12/2025

ውድ ቤተሰቦቻችን እንደ ሚታወቀው ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚሆን ሚክሰር/ ማይክ/ እንዲሁም ኪቦርድ ለመግዛት የተጀመረ ቻሌንጅ እንዳለ ይታወቃል በእናንተ ብረታት ለጌታ ቤት
ባላቹ ቅንሀት ሚክሰር እና ማይክ ማሳካት ችለናል በእናንተ እግዛ ጌታ ይባረካቹ🙏 ማለት እንፈልጋለን አሁንም ትልቁ ስራ ይቀጥላል ኪቦርድ የመግዛት ቻሌንጅ እንቀጥላለን እስካሁን ያልተሳተፍቹ እንድትሳተፍ እየተሳተፍቹ ያላቹ ደግሞ አሁንም ከቤተክርስቲያን ጎን እንድትቆሙ በጌታ ፍቅር🥰 እንጠይቃለን ጌታ ዘመናቹን ይባረክ 🙏

ኪቦርድ እንገዛለን 🎹

1000711687417
Muluken and Solomon and kufa sisay

በቡኢ ገነት ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኘው  ኢቲ 208 ፕሮጀክት ለታቃፊ ህፃናትና ቤተሰቦች  ከ7 መቶ ሺህ ብር በላይ የሚገመት የእህል እና የአልባሳት  ድጋፍ አደረገ።ታህሳስ 8/2018 ዓ....
17/12/2025

በቡኢ ገነት ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኘው ኢቲ 208 ፕሮጀክት ለታቃፊ ህፃናትና ቤተሰቦች ከ7 መቶ ሺህ ብር በላይ የሚገመት የእህል እና የአልባሳት ድጋፍ አደረገ።

ታህሳስ 8/2018 ዓ.ም

በቡኢ ገነት ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኘው ኢቲ 208 ፕሮጀክት 2 መቶ 20 ለሚሆኑ የታቃፊ ህፃናት ከ7 መቶ ሺህ ብር በላይ የሚገመት የእህል፣የልብስ ፣የዘይት ፣የሳሙና እና የቅባት ድጋፍ አደረገ።

በድጋፉ ወቅት የተገኙት የቡኢ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባህሩ በቀለ ፕሮጀክቱ ለረጅም ጊዜ አቅም የለሌላቸው ህፃናትና ቤተሰቦች እና ለእርጉዝ እናቶች በብዙ መልኩ እየደገፈ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለትም መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ያደረገው የእህልና የህፃናት አልባሳት ድጋፍ ለተደረገላቸው ቤተሰቦች ጭንቀት የሚቀንስ ትልቅ ድጋፍ እንደሆነ አንስተዋል።

ድጋፉ ለእርጉዝ ሆነ ወላድ እናቶች እና ህፃናት ሥርዓተ ምግብን ለማስተካከል ተጨማሪ ዕድልና አቅም የሚሰጥ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ለዚህም ድጋፍ በተደረገላቸው ህፃናትና በከተማው አስተዳደሩ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የቡኢ ከተማ አስተዳደር የሴቶችና ህፃናት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ስመኝ ሻንቆ በበኩላቸው የአቅም ውስንነት ላለባቸው እና እርጉዝ እናቶች ጋር በተያያዘ በተለያዩ መስኮች በጋራ ተቀናጅተው የሚሰሩ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ፕሮጀክቱ በርካታ ህፃናትን ከስሩ አቅፎ በተለያየ መልኩ እየደገፈ እንደሚገኝ ገልፀው ከህፃናቱ በተጨማሪ ለእርጉዝ እናቶችም የተለያየ ድጋፍ ሲያደርግ እንደቆየ ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለትም መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ለህፃናቱና ለቤተሰቦቻቸው ያደረገው የእህልና የአልባሳት ድጋፍ እጅግ የሚያስደስት እንደሆነ ጠቁመዋል።

ፕሮጀክቱ እያደረገ ለሚገኘው ድጋፍ በተቋማቸው ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የፕሮጀክቱ አስተባባሪ የሆኑት አቶ መሀመድ ዋርጋ የቡኢ ገነት ቤተ ክርስቲያን በትምህርት፣በጤና፣በኢኮኖሚያዊ እና በሌሎች ማህበራዊ ዘርፎች የሚሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለትም መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በፕሮጀክቱ ለታቀፉ 2 መቶ 20 ለሚሆኑ ህፃናት የእህል፣የዘይት ፣ልብስ፣የሳሙና እና የቅባት ድጋፍ ማድረጉን ገልፀዋል።

በዛሬው ዕለትም የተደረገው ድጋፍ ፕሮጀክቱ በማህበራዊ ዘርፍ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ እንደሆነ ተናግረዋል።

በዚህ ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን በአጠቃላይ ከ 7 መቶ 50 ሺህ በላይ የሚገመት እንደሆነ አመላክተዋል።

ፕሮጀክቱ ስራዎቹን ሲሰራ ከመንግስት ጋር ተቀናጅቶ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን መንግስት ለሚያደርግላቸው አስፈላጊውን ትብብር በድርጅቱ ስም አመስግነዋል።

በመጨረሻም ለህፃናቱና ለቤተሰቦቻቸው እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሲሉ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክቶቻቸው አቅርበዋል።

የዘገባው ምንጭ የቡኢ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

ጠዋት ወደ ቤተክርስቲያን ኑ ⛪ ከ 4:00 ጀምሮ
14/12/2025

ጠዋት ወደ ቤተክርስቲያን ኑ ⛪
ከ 4:00 ጀምሮ

ከ ከጥቅምት 28 እስ 30/2018 ዓ.ም በነበረን ኮንፈረንስ ጌታ ድንቅ ጊዜ ሰጥቶናል እግዚአብሔር ይመስገን🔥🔥🔥
10/11/2025

ከ ከጥቅምት 28 እስ 30/2018 ዓ.ም በነበረን ኮንፈረንስ ጌታ ድንቅ ጊዜ ሰጥቶናል እግዚአብሔር ይመስገን🔥🔥🔥

አይቀርም 🔥ከ ጥቅምት 28 እስከ 30/2018በቡኢ ገነት ቤ/ክ
03/11/2025

አይቀርም 🔥ከ ጥቅምት 28 እስከ 30/2018
በቡኢ ገነት ቤ/ክ

ቡኢ ገነት ቤተክርስቲያን ኢት-208 ህፃናት ልማት ፕሮጀክት በሰርቫይቫል ፕሮግራም ለታቀፉ እርጉዝና ወላድ እናቶች የተለያዩ ድጋፎችን አደረገ።ጥቅምት 7-2018 ዓ.ም ××××××ቡኢ××××የቡኢ...
17/10/2025

ቡኢ ገነት ቤተክርስቲያን ኢት-208 ህፃናት ልማት ፕሮጀክት በሰርቫይቫል ፕሮግራም ለታቀፉ እርጉዝና ወላድ እናቶች የተለያዩ ድጋፎችን አደረገ።

ጥቅምት 7-2018 ዓ.ም
××××××ቡኢ××××

የቡኢ ገነት ቤተክርስቲያን ህፃናት ልማት ፕሮጀክት በስሩ ለሚገኙ 56 በኑሮአቸው በዝቅተኛ ደረጃ ለሚገኙ ቤተሰቦች በተለይም ለእርጉዝና ለወላድ እናቶች ብርድልብስ ፣ ፍራሽ፣ አልሚ ምግቦች ፓስታ፣መኮረኒ፣እሩዝ፣ዘይት፣ሳሙና እንዲሁም በቆሎ ድጋፍ አድርጓል።

የቡኢ ገነት ቤተክርስቲያን ኢቲ-208 ህፃናት ልማት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ መሀመድ ዋርጋ ፕሮጀክቱ በየጊዜው በስሩ ላቀፍቸው ቤተሰቦች የተለያየ ድጋፎችን እንደሚያደርግ ገልፀው የዛሬውም ከ170,000 (አንድ መቶ ሰባ ሺ) ብር በላይ ወጪ በማድረግ በሰርቫይቫል ፕሮግራም ለተለዩ እርጉዝና ወላድ እናቶች ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።

በድጋፍ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የቡኢ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ፅ/ቤት ተወካይ ወ/ሮ መንበረ ቦጋለ ፕሮጀክቱ በተለያየ ጊዜ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ዘርፈ ብዙ ድጋፎችን እንያደረገ እንደሚገኝ ገልፀው የዛሬው ድጋፍም ወላድና ነብሰጡር እናቶች ላይ ትኩረት ያደረገና በማህበረሰቡ ውስጥም ጤናማና የተስተካከል የጤና ስርዓት እንዲፈጠር የሚደረገውን የመንግስት ፕሮግራም የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።

የዘገባው ምንጭ የቡኢ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት

🌼2018 እግዚአብሔር በማመስገን ጀምረነዋል 🌼
11/09/2025

🌼2018 እግዚአብሔር በማመስገን ጀምረነዋል 🌼

Address

Ho
S**o
00

Telephone

+251975757528

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቡኢ ገነት ቤ/ክ Genet Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share