Kekalu tube - ከቃሉ ቲዩብ

Kekalu tube - ከቃሉ ቲዩብ መንፈሳዊ ትምህርቶች

የአባቶች ወግ (ማር 7÷1-13)ከዚህ ምንባብ ስለ አይሁድ ወግ ስናጠና  የእግዚአብሔርን ቃል  እንደ ፈለገ የሚሽር ነበር፡፡በቃል ሲተላለፍ ከነበረዉ ብዙ የአባቶች ወግ  መካከል አንዱ ኮርባን...
04/01/2025

የአባቶች ወግ (ማር 7÷1-13)

ከዚህ ምንባብ ስለ አይሁድ ወግ ስናጠና የእግዚአብሔርን ቃል እንደ ፈለገ የሚሽር ነበር፡፡በቃል ሲተላለፍ ከነበረዉ ብዙ የአባቶች ወግ መካከል አንዱ ኮርባን ብለዉ በዕብራይስጥኛ የሚጠሩት ነዉ፡፡ትርጉሙም ለእግዚአብሔር የተለየ ስጦታ ማለት ነዉ፡፡
ከልጁ እርዳታ የሚፈልገዉ ወላጅ ልጁን አግዘኝ ቢለዉ ወላጆቹን መጦር የማይፈልገዉ ልጅ የአባቶችን ወግ ምክንያት በማድረግ በሙሴ በኩል ለወላጆቻችሁ ታዘዙ የሚለዉን የእግዚአብሔርን ቃል ይተላለፋል፡፡በዚህም ምክንያት አንድ ልጅ በተፃፈዉ ህግ መሰረት ለወላጆቹ ማድረግ የሚገባዉን ግዴታ በመሸሽ በእጄ ያለዉ ንብረት ለእግዚአብሔር የተለየ ስጦታ ነዉ በማለት ዉጫዊ ስርአት ብቻ ይፈፅማል፡፡ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ወጋቸዉን በእግዚአብሔር ቃል ሲመዝነዉ ግብዝነት የሞላበት እንደሆነ መስክሯል፡፡

ዛሬም ቢሆን የቤተክርስቲያናችን ወግና ባህል በእግዚአብሔር ቃል ሲመረመር ከልብ በሆነ እዉነተኛ አምልኮ ላይ የተመሰረተ ሆኖ ካልተገኘና በሰዉ ስርአት ላይ ብቻ ከተንጠለጠለ የእግዚአብሔር ቃል የሚለዉን እንስማ፡፡‹‹ጌታም፦ ይህ ሕዝብ በአፉ ወደ እኔ ይቀርባልና፥ በከንፈርቹም ያከብረኛልና፥ ልቡ ግን ከእኔ የራቀ ነውና፥ በሰዎች ሥርዓትና ትምህርት ብቻ ይፈራኛልና›› (ኢሳ 29÷13)

ሁሉን ቻዩ ጌታ (ማር 6÷45-56) በቅፍርናሆም ኢየሱስ አምስት ሺ ወንዶችን በተአምራቱ ከመገበ በኋላ ህዝቡ በግድ ሊያነግሱት አሰቡ፡፡ኢየሱስ መንግስቱ  ከዚህ አለም አይደለምና ደቀ መዛሙርቱ...
25/12/2024

ሁሉን ቻዩ ጌታ (ማር 6÷45-56)

በቅፍርናሆም ኢየሱስ አምስት ሺ ወንዶችን በተአምራቱ ከመገበ በኋላ ህዝቡ በግድ ሊያነግሱት አሰቡ፡፡ኢየሱስ መንግስቱ ከዚህ አለም አይደለምና ደቀ መዛሙርቱ በጀልባ ሆነዉ ወደ ማዶ እንዲሻገሩ አዟቸዉ እርሱ ደግሞ ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ፡፡
ደቀ መዛሙርቱም ከዚህ ረጅም የአገልግሎት ቀን በኋላ የኢየሱስን ትዕዛዝ ለመፈፀም ወደ ቤተ ሳይዳ በጀልባ ሲሻገሩ ማዕበል አጋጠማቸዉ፡፡ሁሉን ቻዩ ጌታም ከሌሊቱ በዘጠኝ ሰአት ላይ ባስጨነቃቸዉ ማዕበል ላይ እየተራመደ ወደ እነርሱ መጣ፡፡ደቀመዛሙርቱም ምትሃት መስሏቸዉ በፍርሃት ጮኹ፡፡ኢየሱስም እኔ ነኝ አትፍሩ አላቸዉ፡፡ወደ ታንኳቸዉም በገባ ጊዜ ማዕበሉ ፀጥ አለ፡፡እጅግም ተገረሙ፡፡ከዚህ በፊት በቅፍርናሆም የሰራዉን ተአማራት ቢያስተዉሉ ኖሮ የኢየሱስ በዉሃ ላይ መራመድ ባላስገረማቸዉም ነበር፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስም ለደቀመዛሙርቱ ሁሉንቻይነቱን ከተፈጥሮ ስርዓት በላይ የሆነ ተአምራት በማድረግ ያሳየ ሲሆን የተራቡትን በመመገብ፣ለእነርሱ የእረፍት ጊዜ በማሰቡና ለዳሰሱት ሁሉ ፈዉስ በመስጠቱ ቸርነቱን አሳይቷቸዋል፡፡
ዛሬም ቢሆን ይህ ሁሉን ቻይ ጌታ አይዟችሁ እኔ ነኝ አትፍሩ በማለት ከችግራችንና ከፍርሃታችን ሊያወጣን ይችላል፡፡ነገር ግን እኛም እንደ ደቀ መዛሙርቱ ትላንት በእኛ ህይወት የሰራዉን ተአምራት በመዘንጋት ልባችን እንዳይደነዝዝ ያስፈልጋል፡፡ምክንያቱም ወደኋላ ዘወር ብለን ብናስብ ይህ ሁሉን ቻይ ጌታ ከዛሬዉ ከከፋ ችግር አላቆናልና፡፡ለዛሬዉም ይታመናል፡፡

ሩህሩህ ጌታ (ማር 6÷30-44)የኢየሱስ ደቀመዛሙርት እንደ ወትሮዉ ከስብከተ ወንጌል ተመልሰዉ የአገልግሎት ሪፓርታቸዉን ለኢየሱስ አቀረቡ፡፡በኢየሱስ ለመገልገል የመጡ ሰዎች ብዙዎች ስለነበሩ ...
14/12/2024

ሩህሩህ ጌታ (ማር 6÷30-44)

የኢየሱስ ደቀመዛሙርት እንደ ወትሮዉ ከስብከተ ወንጌል ተመልሰዉ የአገልግሎት ሪፓርታቸዉን ለኢየሱስ አቀረቡ፡፡በኢየሱስ ለመገልገል የመጡ ሰዎች ብዙዎች ስለነበሩ ከአገልግሎት ደክሟቸዉ ተመልሰዉ የመጡት ደቀመዛሙርቱ የሚበሉበትን ጊዜ እንኳን አላገኙም ነበር፡፡
ኢየሱስ በህይወቱ ለእረፍት የሚሰጠዉ ስፍራ ትልቅ ስለነበር ደቀመዛሙርቱን ይዞ ለብቻቸዉ እንዲሆኑና እንዲያርፉ ፈለገ፡፡ነገር ግን ህዝቡ ተከተሏቸዉ፡፡ኢየሱስም ሰዎች ቃሉን ለመስማት ያላቸዉን ረሃብ በማየቱና እረኛ እንደሌላቸዉ በጎች መበተናቸዉን አይቶ አዘነላቸዉ፡፡
ስለዚህ የመጣዉን ህዝብ ከመበተን ይልቅ ሩህሩህ የሆነዉ ጌታ ከራሱና ከደቀመዛሙርቱ እረፍት አስቀድሞ ቃሉን ተርበዉ የመጡትን ህዝብ ማገልገል ጀመረ፡፡ብዙ ነገር ያስተምራቸዉና ድዉዮችንም ይፈዉስ ነበር፡፡ለነፍሳቸዉ ምግብ የሆነዉን ቃሉን ካስተማራቸዉ በኋላ ለስጋቸዉ የሚያስፈልጋቸዉን ምግብ በተአምራት መገባቸዉ፡፡በዚህም በተደረገዉ ተአምራት የሐዋርያት ድርሻ ኢየሱስ ያበዛዉን ምግብ ለህዝቡ ማደል ነበር፡፡
እኛም ብንሆን ሁል ጊዜም ለሰዎች ጥቅም ቅድሚያ ከሚሰጠዉ ሩህሩህ ጌታ ተምረን እንደ እርሱ እንድንመላለስ ጳዉሎስ በመልዕክቱ እንዲህ እያለ ያሳስበናል፡፡‹‹እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ።በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።››
(ፊሊ 2÷4-5)

ክፉ ህሊና (ማር 6÷14-29)ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላና ዙሪያዉ በሚያደርገዉ ተአማራት ዝናዉ እየጨመረ በመምጣቱ  የሰዎች መነጋገሪያ ሆኗል፡፡አንዳንዶች ነብዩ ኤልያስ ነዉ ሲሉ ሌሎች ደግሞ ከ...
23/11/2024

ክፉ ህሊና (ማር 6÷14-29)

ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላና ዙሪያዉ በሚያደርገዉ ተአማራት ዝናዉ እየጨመረ በመምጣቱ የሰዎች መነጋገሪያ ሆኗል፡፡አንዳንዶች ነብዩ ኤልያስ ነዉ ሲሉ ሌሎች ደግሞ ከብሉይ ኪዳን ነቢያት አንዱ ነው ይላሉ፡፡የገሊላ አዉራጃዉ ገዢ ሄሮድስና ሌሎች ደግሞ አጥማቂዉ ዮሐንስ ከሞት ተነስቷል ይላሉ፡፡በዚያን ዘመን የነበሩ ሰዎች የሙት ሰዉ መንፈስ ሰዉየዉ በህይወት እያለ ከነበረዉ ኃይል የሚልቅ ኃይል አለዉ ብለዉ ያምኑ ስለነበር ከሞት የተነሳዉ አጥማቂዉ ዮሐንስ ነዉ ይህን ተአምራት እያደረገ መሆን ያለበት አሉ፡፡
ሄሮድስ ዮሐንስ ጻድቅና ቅዱስ ሰዉ እንደሆነ በማወቁ ይፈራዉና የሚናገረዉንም በደስታ ይሰማ ነበር፡፡ነገር ግን ለሚሰማዉ የእግዚአብሔር ቃል ተገቢ የሆነ ምላሽ አይሰጥም ነበር፡፡በዚህም ምክንያት ወደ ክፉ ህሊና የሚያደርገዉን ጉዞ ቀጠለ፡፡ከወንድሙ ቀምቶ ያገባት ሚስቱ ሄሮድያዳ ባገኘችዉ መልካም እድል አጥማቂዉ ዮሐንስን እንዲያስገድል መራችዉ፡፡እርሱም ለራሱ ክብር ሲል ህሊናዉ የማይፈቅድለትን ስራ ሰራ፡፡በስተመጨረሻም የበደለኝነት ስሜት የተሞላ አእምሮ ስላለዉ ስለ ኢየሱስ ዝና ሲሰማ የአጥማቂዉ ዮሐንስ መንፈስ እርሱን ለመበቀል ተመልሶ የመጣ ስለመሰለዉ ፈራ፡፡‹‹ኀጥእ ማንም ሳያሳድደው ይሸሻል ጻድቅ ግን እንደ አንበሳ ያለ ፍርሃት ይኖራል።››(ምሳ 28÷1)
እኛም ለክፉ ህሊና ተላልፈን እንዳንሰጥ ለምንሰማዉ የእግዚአብሔር ቃል ተገቢ የሆነ ምላሽ በመስጠት የሰራነዉን ጥፋት በማመን ወደ እግዚአብሔር በንስሃ መመለስ አለብን፡፡

ተሰናከሉበት (ማር 6÷1-13)ኢየሱስ በዮሐንስ እጅ ተጠምቆ አገልግሎት ከመጀመሩ በፊት እንደማንኛዉም ሰዉ ቤተሰቦቹን እየታዘዘና እያገዘ በአካባቢዉም ያለዉን ማህበረሰብ ባለዉ የፀራቢነት ሙያ ...
03/11/2024

ተሰናከሉበት (ማር 6÷1-13)

ኢየሱስ በዮሐንስ እጅ ተጠምቆ አገልግሎት ከመጀመሩ በፊት እንደማንኛዉም ሰዉ ቤተሰቦቹን እየታዘዘና እያገዘ በአካባቢዉም ያለዉን ማህበረሰብ ባለዉ የፀራቢነት ሙያ እየጠቀመ ኖሯል፡፡ለአገልግሎት ወደ አገሩ በመጣ ጊዜ ግን ምንም እንኳ የእግዚአብሔር ልጅ ቢሆንም፣ለብዙ ትዉልዶች ሲጠበቅ የነበረዉ መሲህ ቢሆንም በመካከላቸዉ በማደጉ ናቁት፡፡ይህም ትልቁ የናዝሬት ከተማ ሰወች ስህተት ነበር፡፡ስለዚህም ተሰናከሉበት፡፡ ‹‹ኢየሱስም፦ ነቢይ ከገዛ አገሩና ከገዛ ዘመዶቹ ከገዛ ቤቱም በቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው።››
ምንም እንኳ የአገሩ ሰዎች ባያምኑትም በመንደሮች እያስተማረ ይዞር ነበር፡፡ በእርሱ አምነዉ የተከተሉትንም ሐዋርያት በርኩሳን መናፍስት ላይ ስልጣንን ሰጣቸዉ፡፡እነርሱም በተላኩበት ስፍራ ሁሉ የእግዚአብሔር መንግስት እንደቀረበች እየሰበኩ፣ብዙ አጋንንትን ከሰዎች በማዉጣትና ድዉዮችን በመፈወስ ብዙዎች በንስሃ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱ አድርገዋል፡፡ጴጥሮስም በመልዕክቱ የነገረን ይህንኑ ነዉ፡፡‹‹እንግዲህ ክብሩ ለእናንተ ለምታምኑት ነው፤ ለማያምኑ ግን አናጢዎች የጣሉት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ የዕንቅፋትም ድንጋይ የማሰናከያም ዓለት ሆነ፤›› (1ኛ ጴጥ 2፥7)
የአገሩ ሰዎች በኢየሱስ እንደተሰናከሉበትና የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ለመቀበል ባለመቻላቸዉ ከክብሩ ጎድለዋል፡፡ከሴቶች ከተወለዱት እንደርሱ ያለ ነብይ አልተነሳም የተባለለት መጥምቁ ዮሐንስ በአንድ ወቅት ኢየሱስን ‹‹የሚመጣው አንተ ነህን? ወይስ ሌላ እንጠብቅ? አለው፡፡ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦… በእኔም የማይሰናከለው ሁሉ ብፁዕ ነው።›› (ማቴ 11፥3-6)
ዛሬም እኛ ይህንን ብፅዕና የምናገኘዉ በኢየሱስ ክርስቶስ ባለመሰናከል የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ስናምን ነዉ፡፡

ብቻ በኢየሱስ እንመን (ማር 5÷21-43)በወንጌላት ዉስጥ ባነበብናቸዉ ታሪኮች ሁሉ ዉስጥ እምነታቸዉን በኢየሱስ ላይ ያደረጉ ሰዎች ሁሉ ያመኑት ጌታ አሳፍሯቸዉ አያዉቅም፡፡በዚህም የምንባብ ክ...
28/10/2024

ብቻ በኢየሱስ እንመን (ማር 5÷21-43)

በወንጌላት ዉስጥ ባነበብናቸዉ ታሪኮች ሁሉ ዉስጥ እምነታቸዉን በኢየሱስ ላይ ያደረጉ ሰዎች ሁሉ ያመኑት ጌታ አሳፍሯቸዉ አያዉቅም፡፡
በዚህም የምንባብ ክፍል ደም ይፈሳት የነበረችዉ ሴት የኢየሱስን የልብሱን ጫፍ እንኳ እንደ ምንም ብዬ ብነካ እፈወሳለሁ የሚል እምነት ነበራት፡፡በብሉይ ኪዳን ህግ መሰረት ግን ርኩስ ስለሆነች በህዝብ መካከል መገኘት አትችልም ነበር፡፡ (ዘሌ 15፥19-25) ኢየሱስ በብዙ ህዝብ ተከቦ የነበረ በመሆኑ በቀላሉ ወደ እርሱ ለመድረስ መንገድ ባታገኝም፤ስቃዩ ለብዙ ዘመናት ስለበረታባትና የሚፈዉሳትም ባለማግኘቷ ህግ ባይፈቅድላትም በብዙ ትግል ዉስጥ አልፋ ልብሱን ዳሰሰች፡፡ከኢየሱስ ዉስጥም የወጣዉ ኃይል የደምዋን ምንጭ በማድረቅ ከስቃይዋ አዳናት፡፡‹‹ እርሱም፦ ልጄ ሆይ፥ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ ከሥቃይሽም ተፈወሽ አላት።››
ኢያኢሮስ የሚባለዉም የምኩራብ አለቃ ከኢየሱስ እግር ስር ተደፍቶ የታመመችዉን ሴት ልጁን እንዲፈዉስለት ለመነዉ፡፡ ኢየሱስም አብሮት እየሄደ ሳለ ብላቴናይቱ በመሞቷ የሰፈር ሰዉ ተሰብስቦ ማልቀስ ጀመረ፡፡ለአባቷም መልዕክት ደረሰዉ፡፡ወደ ኢያኢሮስ የመጡ መልዕክተኞች ‹መምህሩን አታድክመዉ› ያሉት ኢየሱስ የታመመን እንደሚፈዉስ እንጂ የሞተን እንደሚያስነሳ ገና ስላላመኑበት ነበር፡፡‹‹ኢየሱስ ግን የተናገሩትን ቃል አድምጦ ለምኵራቡ አለቃ። እመን ብቻ እንጂ አትፍራ አለው።›› ሶስቱንም ሐዋርያት እስከትሎ ከአባቷ ጋር ሲደርስ ህይወት ሰጪ በመሆኑ ለቀስተኞችን ብላቴናይቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችምና አታልቅሱ አላቸዉ፡፡የአስራ ሁለት አመቷንም ብላቴና ከሞት አስነሳት፡፡ ብላቴናይቱንም ከሞት ሲያስነሳት የነበሩት የሶስቱ ሐዋርያትና የብላቴናይቱ ወላጆች እምነት በኢየሱስ ላይ ፀና፡፡
ስለዚህ ኢየሱስ መልካምና ሁሉን ቻይ በመሆኑና ትላንትናም ዛሬም እስከዘለአለም ህያዉ በመሆኑ እምነታችን በእርሱ ላይ ሊፀና ይገባል፡፡

ሃይል ያለዉ (ማር 5÷1-20)በዚህ ክፍል አጋንንት ከእግዚአብሔር የሆነዉን የመለየት እዉቀት እንዳላቸዉ፣እግዚአብሔር ያዘጋጀላቸዉን ጥልቁን እንደሚፈሩት፣ በዚህች ምድር እየገዙ መኖር እንደሚመ...
15/10/2024

ሃይል ያለዉ (ማር 5÷1-20)

በዚህ ክፍል አጋንንት ከእግዚአብሔር የሆነዉን የመለየት እዉቀት እንዳላቸዉ፣እግዚአብሔር ያዘጋጀላቸዉን ጥልቁን እንደሚፈሩት፣ በዚህች ምድር እየገዙ መኖር እንደሚመኙና እግር ብረት የማያስረዉ ኃይል እንዳላቸዉ መማር እንችላለን፡፡
በጌርጌሴኖን የሚኖረዉ ሰዉ ከኢየሱስ ጋር ከመገናኘቱ በፊት በአጋንንት ጭፍራ እየተመራ በመቃብር ስፍራ፣ከሰዉ ተለይቶ በከባድ መከራ ይኖር ነበር፡፡ኢየሱስን ካገኘ በኋላ ግን አጋንንቱ ወጥተዉለት፣ወደ አእምሮዉ ተመልሶ፣ልብሱንም ለብሶ በህዝቡ መካከል ተቀላቅሎ ኢየሱስ ያደረገለትን ያወራ ጀመር፡፡ለምን ይሆን? ኢየሱስ በሃይሉ አጋንንት በከባድ ሁኔታ ሲያሰቃዩት የነበረዉን ሰዉ ፈዉሶ ሰዎቹ ግን ከከተማቸዉ እንዲወጣላቸዉ የለመኑት፡፡ ምናልባትም ከከተማዉ አጋንንት ያደረበትን ሰዉ በሃይሉ አጋንንት እያወጣ አንደ አሳማዎቹ ወደ እንስሳቸዉ በማስገባት የእንስሳ ሃብታቸዉን የሚጨርስ መስሏቸዉ ወይም ደግሞ ሰዎች አልታዘዝ ካሉት አጋንንትን ጠርቶ የሚያስገባባቸዉ ጨካኝ ሰዉም መስሏቸዉ ይሆናል፡፡ያም ሆነ ይህ ግን ከአጋንንት ጭፍሮች የሚብለጥ ሃይል ስላለዉ ፈርተዉታል፡፡
ኢየሱስም ከአጋንንት እስራት የተፈታዉ ሰዉዬ ከእርሱ ጋር እንዲሄድ ባለመፍቀድ ስለ እርሱ የተሳሳተ ምልከታ ባላቸዉ በእነዚህ ሰዎች መካከል እርሱ እንዳሰቡት ጨካኝ ሳይሆን መልካምና ሩህሩህ ጌታ መሆኑን እንዲመሰክር ወደ ቤተሰቡ ላከዉ፡፡‹‹ሄዶም ኢየሱስ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገለት አሥር ከተማ በሚባል አገር ይሰብክ ጀመር፥ ሁሉም ተደነቁ።››
እኛስ ዛሬ ሃይል ያለዉ ኢየሱስ ከምን አይነት ጉድ ዉስጥ ይሆን ጎትቶ ያወጣን? የተደረገልንንስ መልካምነት እንደዚህ ሰዉ ለሌሎች እየመሰከርን ይሆን?

ይህ ማን ነዉ? (ማር 4÷35-41)ኢየሱስ የገሊላን አካባቢ ትቶ ከደቀመዛሙርቱ ጋር ወደ ጌርጌሴኖን ሃገር በታንኳ እየሄደ ሳለ ቀኑን ሙሉ በማስተማሩ እንደ ማንኛዉም ሰዉ ስጋዉ ስለደከመ በታን...
07/10/2024

ይህ ማን ነዉ? (ማር 4÷35-41)

ኢየሱስ የገሊላን አካባቢ ትቶ ከደቀመዛሙርቱ ጋር ወደ ጌርጌሴኖን ሃገር በታንኳ እየሄደ ሳለ ቀኑን ሙሉ በማስተማሩ እንደ ማንኛዉም ሰዉ ስጋዉ ስለደከመ በታንኳይቱ ዉስጥ ተኛ፡፡ከደቀመዛሙርቱ ቢያንስ አራቱ ባህሩን በደንብ የሚያዉቁ አሳ አጥማጆች ነበሩ፡፡ነገር ግን የተነሳዉ ማዕበል ከአቅማቸዉ በላይ በመሆኑና ሊያሰጥማቸዉ በመድረሱ ወደ ኢየሱስ ጮኹ፡፡አይሁዳዉያን ንፋስና ማዕበል የሚታዘዙለት ለእግዚአብሔር እንደሆነ ያምናሉ፡፡ (መዝ 65÷7)
ኢየሱስ ምንም እንኳ እኛን ለማዳን ሰዉ ቢሆንም ደቀመዛሙርቱ እርሱ አምላክ መሆኑን እንዲያምኑ ስለሚፈልግ ማዕበሉን ፀጥ በል ብሎ በስልጣን በማዘዝ ዝም አሰኝቶታል፡፡ይሄኔ ነበር የኢየሱስን ሁሉን ቻይነት ገና ያላመኑት ደቀመዛሙርቱ በመገረምና በመደነቅ ተሞልተዉ‹‹እጅግም ፈሩና። እንግዲህ ነፋስም ባሕርም የሚታዘዙለት ይህ ማን ነው? ተባባሉ።››
በመዝሙር መፅሐፍም እግዚአብሔር የንፋሱና የሞገዱ ጌታ በመሆኑ ሰዎች ስለተአምራቱና ምህረቱ እንዲያመሰግኑት በማነሳሳት እንዲህ ተፅፏል፡፡ ‹‹ተናገረ፥ ዐውሎ ነፋስም ተነሣ፥ ሞገድም ከፍ ከፍ አለ።ወደ ሰማይ ይወጣሉ ወደ ጥልቅም ይወርዳሉ ነፍሳቸውም በመከራ ቀለጠች። ደነገጡ እንደ ስካርም ተንገደገዱ፥ ጥበባቸውም ሁሉ ተዋጠች። በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፥ ከመከራቸውም አዳናቸው። ዐውሎንም ጸጥ አደረገ፥ ሞገዱም ዝም አለ።ዝም ብሎአልና ደስ አላቸው ወደ ፈለጉትም ወደብ መራቸው።›› (መዝ 107÷25-30)
ይህ ማን ነዉ? ኢየሱስ ካደረገዉ ተአምር የተነሳ ለዚህ ጥያቄ ተገቢ የሚሆ ነዉ መልስ‹እርሱ በእዉነት የእግዚአብሔር ልጅ ነዉ›የሚለዉ ይሆናል፡፡

የመንግስቱ ቃል (ማር 4÷21-34)የመንግስቱ ቃል የራሱ የሆነ ኃይል አለዉ፡፡ምንም እንኳን ቃሉ የሚያርፍበት የልብ አይነት የተለያየ ቢሆንም ኢየሱስ በዚህ ክፍል በተናገረዉ ምሳሌ መሰረት የመ...
27/09/2024

የመንግስቱ ቃል (ማር 4÷21-34)

የመንግስቱ ቃል የራሱ የሆነ ኃይል አለዉ፡፡ምንም እንኳን ቃሉ የሚያርፍበት የልብ አይነት የተለያየ ቢሆንም ኢየሱስ በዚህ ክፍል በተናገረዉ ምሳሌ መሰረት የመንግስቱ ቃል ከተዘራ በኋላ ዘሪዉ እንዴት እንደሚበቅል ሳያዉቅ በመሬት በተመሰለዉ የሰዉ ልብ ዉስጥ ጊዜዉን ጠብቆ እንደሚያድግ ያሳያል፡፡እንዲህም ተብሎ ተፅፏል፡፡‹‹ዝናብና በረዶ ከሰማይ እንደሚወርድ፥ ምድርን እንደሚያረካት፥ ታበቅልና ታፈራ ም ዘንድ እንደሚያደርጋት፥ ዘርንም ለሚዘራ እንጀራንም ለሚበላ እንደሚሰጥ እንጂ ወደ ሰማይ እንደማይመለስ፥ከአፌ የሚወጣ ቃሌ እንዲሁ ይሆናል የምሻውን ያደርጋል የላክሁትንም ይፈጽማል እንጂ ወደ እኔ በከንቱ አይመለስም።››(ኢሳ 55÷10-11)
ከእኛም የሚጠበቀዉ በመንገድ የተመሰለዉን የሰዉ ልብ ማረስ፣ጭንጫ ማዉን መሬት በቃሉ መዶሻ መፈረካከስ፣ፍሬ እንዳያፈራ እንቅፋት በመሆ ን እንደ እሾህ ያነቀዉን የዚህን አለም ሃሳብ፣የሃብት ፍቅርና ሌላዉንም ከንቱ ምኞት በቃሉ ሰይፍ መመንጠር ነዉ፡፡‹‹በውኑ ቃሌ እንደ እሳት፥ ድንጋዩንም እንደሚያደቅቅ መዶሻ አይደለችምን? ይላል እግዚአ ብሔር›› (ኤር 23÷29)
ሰዉ የመንግስቱን ቃል እጅግ በጥንቃቄና በማስተዋል መስማት አለበት፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ ሲያስተምር የሰማዉን እዉነት በማስተዋል ለሚተገብር ሰዉ ወደ ፊት የሚበልጥ የእግዚአብሔርን እዉነት ይቀበላል ሲል፤ ነገር ግን እንደ አቅሙ የተቀበለዉን እዉነት ስራ ላይ ባያዉለዉ ያለዉ የሚመስለዉ እዉነት እንኳን እንደሚወሰድበትና የሚያተርፈዉ አንዳችም እንደማይኖር አስጠንቅቋል፡፡‹‹ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል።›› (ማቴ 25÷28-29)

ዘሩ የእግዚአብሔር ቃል ነዉ (ማር 4÷1-20)ጌታችን ኢየሱስ በብዙ አይነት ምሳሌ ያስተምር ነበር፡፡በዚህም ክፍል ስለ አንድ ዘር ስለሚዘራ ገበሬ በምሳሌ ህዝቡን ካስተማራቸዉ በኋላ ለደቀመዛሙ...
23/09/2024

ዘሩ የእግዚአብሔር ቃል ነዉ (ማር 4÷1-20)

ጌታችን ኢየሱስ በብዙ አይነት ምሳሌ ያስተምር ነበር፡፡በዚህም ክፍል ስለ አንድ ዘር ስለሚዘራ ገበሬ በምሳሌ ህዝቡን ካስተማራቸዉ በኋላ ለደቀመዛሙርቱ ሲተረጉምላቸዉ እንዲህ አለ፡፡ዘሩ የእግዚአብሔር ቃል ነዉ፤የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስተምረዉ ሰዉ ደግሞ በዘሪዉ ይመሰ ላል፡፡በዚህ ክፍል የተዘረዘረዉም አራት የመሬት አይነት የሰዎችን ልብ ይወክ ላል፡፡በመንገድ ዳር የተመሰለዉ ለቃሉ ተገቢዉን ምላሽ ላለመስጠት የደነ ደነ የሰዉን ልብ ሲሆን በጭንጫማ ቦታ የተመሰለዉ ደግሞ ቃሉን ሲሰሙ ወዲያዉ በደስታ የሚቀበሉ ነገር ግን በቃሉ ምክንያት ችግር ወይም መከራ ሲመጣባቸዉ ቃሉ በልባቸዉ ስር ካለመስደዱ የተነሳ ተሰናክለዉ የሚወድ ቁ ሰዎችን ይወክላል፡፡እንዲሁም በእሾህ መካከል የተባለዉ ቃሉን ቢሰሙት ም የዚህ አለም አሳብ፣የሃብት ፍቅርና ሌላዉም ከንቱ ምኞት ወደ ልባቸዉ ገብቶ ቃሉን ስለሚያንቀዉ ያለፍሬ በሚቀሩ ሰዎች ይመሰላል፡፡በስተመጨ ረሻም አራተኛዉና መልካም መሬት የተባለዉ ቃሉን ሰምተዉ በማስተዋል የሚቀበሉትና ቃሉን በእምነት በህይወታቸዉ በማዋሃድ ለቃሉ ተገቢ ምላ ሽ በመስጠት ፍሬ የሚያፈራ የሰዉን ልብ ያመለክታል፡፡
የኢየሱስ ትምህርት በብዙ አድማጮች ዘንድ ፍሬ ያላፈራዉ ከእንደዚህ አይነት የሰዉ ልቦች የተነሳ ነዉ፡፡እኛም የእግዚአብሔርን መንግስት ለማስፋ ፋት ማድረግ ያለብን በዘር የተመሰለዉን የእግዚአብሔርን ቃል ማስተማር ነዉ፡፡የወንጌል ሰባኪም ስኬቱን ሊለካ የሚገባዉ ቃሉን ሰምተዉ በማስተ ዋል በሚቀበሉት ሰዎች ልክ ነዉ፡፡(1ኛ ተሰ 1÷6)
አሁንስ በእኔና በእናንተ ህይወት በዘር የተመሰለዉ የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ፍሬ እንዳያፈራ ምን እንቅፋት ይኖር ይሆን?

ቤተሰብ (ማር 3÷20-35)ኢየሱስ ምንም እንኳ ብዙ ሰዎችን ቢፈዉስ፣አጋንንት ቢያወጣና ቢያስተምርም ፤ተልዕኮዉን እንዲተዉ ለማድረግ አብዷል፣ አጋንንት አድሮበታል እያሉ ስሙን በማጥፋት ከኢየሩ...
19/09/2024

ቤተሰብ (ማር 3÷20-35)

ኢየሱስ ምንም እንኳ ብዙ ሰዎችን ቢፈዉስ፣አጋንንት ቢያወጣና ቢያስተምርም ፤ተልዕኮዉን እንዲተዉ ለማድረግ አብዷል፣ አጋንንት አድሮበታል እያሉ ስሙን በማጥፋት ከኢየሩሳሌም የመጡ ፀሃፍቶች ተቃዉመዉታል፡፡ ኢየሱስም ለተቃዋሚዎቹ የሃሳባቸዉን አለመያያዝ በምሳሌ በማስረዳት ኃይለኛ የተባለዉን ሰይጣንን የማሰር ስልጣንና ኃይል እንዳለዉም ተናግሯል፡፡እንደ ፀሃፍት ላሉ የእግዚአብሔር ስራ የሆነዉን በግልጥ እያዩ ሆን ብለዉ የአጋንንት ስራ ነዉ በማለት ለሚክዱና መንፈስ ቅዱስን ለሚሳደቡ የኃጢያት ስርየት እንደሌላቸዉም አስተምሯል፡፡የስጋ ዘመዶቹ የሆኑት የራሱ ቤተሰብም ተልዕኮዉን አልተረዱትም ነበር፡፡ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማድረግ ከአፉ የሚወጣዉን ቃል ለመስማት የተሰበሰበዉ ህዝብ ግን የኢየሱስን ተልዕኮ አወቀ፡፡ኢየሱስም ሲመሰክ ርላቸዉ የእኔ ቤተሰብ እነኚህ ናቸዉ በማለት ነበር፡፡‹‹የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፥ እርሱ ወንድሜ ነው እኅቴም እናቴም አለ።››
እኛም በስጋ ዘመዶቻችን ለሆነዉ ቤተሰብ ኃላፊነታችንን የምንወጣዉ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በመታዘዝ ሲሆን ከማይጠፋዉ ዘር ከእግዚአብ ሔር ቃል በመንፈሱ አማካኝነት ዳግም በመወለድ የተዛመደንን መንፈሳዊ ቤተሰብ ደግሞ በተሰጠን የፀጋ ስጦታ እያገለገልናቸዉ አብረን ህብረት ማድረግ ይኖርብናል፡፡በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን ዳግም ለተወለዱት የኤፌሶን ቅዱሳን ጳዉሎስ በመልዕክቱ ስለ ተቀላቀሉት ትልቅ ቤተሰብ ሲገልፅ እንዲህ ይላል፡፡‹‹እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም።›› (ኤፌ 2÷19)

የአገልግሎት ስፋት (ማር 3÷7-19)በዚህ ክፍል ኢየሱስ በሽተኞችን እንደሚፈዉስ፣ርኩሳን መናፍስትን በስልጣን እያዘዘ እንደሚያስወጣ እና ታላላቅ ነገሮችን እንደሚያደርግ ዝናዉን የሰሙ ከቅፍርና...
09/09/2024

የአገልግሎት ስፋት (ማር 3÷7-19)

በዚህ ክፍል ኢየሱስ በሽተኞችን እንደሚፈዉስ፣ርኩሳን መናፍስትን በስልጣን እያዘዘ እንደሚያስወጣ እና ታላላቅ ነገሮችን እንደሚያደርግ ዝናዉን የሰሙ ከቅፍርናሆምና ከአካባቢዋ ብቻ ሳይሆን ከእስራኤልና ከአጎራባች አገሮች ጭምር ብዙ ሰዎች ይመጡ ነበር፡፡ኢየሱስም አገልግሎቱ እየሰፋ በመሄዱ ከእርሱ ጋር በመሆን እንዲያገለግሉ ከደቀመዛሙርቱ 12ቱን ለየ፡፡ሐዋርያትም ብሎ ሰየማቸዉ፡፡
የአስራ ሁለቱን ሐዋርያት አገልግሎትና ስልጣን ከኢየሱስ አገልግሎትና ስልጣን ጋር ስናነፃፅረዉ ተመሳሳይ ነዉ፡፡ምክንያቱም ኢየሱስ እንደሚያስ ተምር እንዲያስተምሩ፣እርሱ አጋንንት እንደሚያስወጣ እንዲያስወጡ በስሙ ስልጣንና ኃይል ነዉና የተላኩት፡፡እነዚህ ሐዋርያት ለአገልግሎት እንዲዘጋጁ ግን የሚያስፈልጋቸዉ ስልጠና፣ልዩ ልዩ ትምህርትና የአገልግሎት ልምምዶች ብቻ ሳይሆን ከኢየሱስ ጋር ዘወትር መዋልና የጠበቀ ህብረት ማድረግ ነበረባቸዉ፡፡
ዛሬም ቢሆን አገልግሎታችን እንደ ኢየሱስ እየሰፋ በመጣ ቁጥር ስልጣንና ኃላፊነት እየሰጠን ሌሎችም የሚያገለግሉበትን መንገድ መፍጠር ይኖርብ ናል፡፡ሙሴ ከስድስት መቶ ሺ እግረኛ በላይ ለሆነዉ የእስራኤል ህዝብ ብቻ ዉን እየፈረደ እንዳይደክምና ህዝቡም እንዳይጉላላ አማቱ ዮቶር የመከረዉ ምክር እንዲህ ነበር፡፡‹‹የሙሴም አማት አለው። አንተ የምታደርገው ይህ ነገር መልካም አይደለም።ይህ ነገር ይከብድብሃልና አንተ ከአንተ ም ጋር ያለው ሕዝብ ትደክማላችሁ አንተ ብቻህን ልታደርገው አትች ልም። አሁንም እመክርሃለሁና ቃሌን ስማ፥ እግዚአብሔርም ከአንተ ጋር ይሆናል አንተ በእግዚአብሔር ፊት ለሕዝቡ ሁን፥ ነገራቸውንም ወደ እግዚአብሔር አድርስ ሥርዓቱንም ሕጉንም አስተምራቸው፥ የሚሄዱበትን መንገድ የሚያደርጉትንም ሥራ ሁሉ አሳያቸው። አንተም ከሕዝቡ ሁሉ አዋቂዎችን፥ እግዚአብሔርን የሚፈሩትን፥ የታመኑ፥ የግፍንም ረብ የሚጠሉትን ሰዎች ምረጥ ከእነርሱም የሺህ አለቆችን፥ የመቶ አለቆችን፥ የአምሳ አለቆችን፥ የአሥርም አለቆችን ሹምላቸው።በሕዝቡ ላይ ሁልጊዜ ይፍረዱ አውራውን ነገር ሁሉ ወደ አንተ ያምጡት፥ ታናሹንም ነገር ሁሉ እነርሱ ይፍረዱ እነርሱም ከአንተ ጋር ሸክሙን ይሸከማሉ፥ ለአንተም ይቀልልልሃል። ›› (ዘጸ 18÷17-22)

Address

Sodo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kekalu tube - ከቃሉ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Kekalu tube - ከቃሉ ቲዩብ:

Share